Saturday, 16 March 2024 19:50

“ክሶቹ የተቋረጡት ለህዝብ ጥቅም ሲባል ነው”

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በሽብርና በሙስና ወንጀሎች ክስ ቀርቦባቸው በእስር ላይ በነበሩት  በእነ አብዲ ሞሃመድ ኡመር (አብዲ ኢሌ) እና በእነ ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው መዝገቦች ቀርበው የነበሩ ክሶች እንዲቋረጡ መወሰኑን  ፍትህ ሚኒስቴር አስታወቋል ።
ክሶቹ እንዲቋረጡ የተደረጉትም  ለህዝብ ጥቅም ሲባል እንደሆነም ገልጿል ።
የሶማሌ ክልል የቀድሞ ርዕሰ መስተዳድር አብዲ ሞሃመድ ኡመር (አብዲ ኢሌ) በ2011 ዓ.ም በክልሉ የተፈጠረውን ሁከት ተከትሎ፣ በቁጥጥር ስር ውለውና ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው  በ1ኛ የህገ-መንግስትና የሽብር ወንጀል ጉዳዮች ችሎት ሲታይ  መቆየቱ የሚታወቅ ነው። ይኸው በፍርድ ሂደት ላይ የነበረው ክስ እንዲቋረጥ መወሰኑ ተገልጿል። የክስ መቋረጡን ተከትሎም ከስድስት ዓመታት በፊት ነሐሴ 21 ቀን 2010 ዓ.ም. አዲስ አበባ  ከተማ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውለው አስካሁን በእስር ላይ የቆዩት አቶ አብዲ ኢሌ ከእስር  መለቀቃቸውም ታውቋል።የቀድሞ የኢትዮጵያ ብረታ ብረት እና ኢነጅነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር የነበሩት  ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው ከኮርፖሬሽኑ ሥራ ጋር በተያያዘ በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው  በምዕራባዊ ትግራይ በኩል ባታር በተሰኘው አካባቢ  በህዳር 2011 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሙስና ወንጀል ክስ ክርክር ሲካሄድበት  የቆየ ሲሆን፤ ከራዳር እቃዎች የግዥ ሒደት ጋራ ተያይዞ በቀረበባቸው ክስ ጥፋተኛ ተብለው የ3 ዓመት ከ7 ወር የእስራት ቅጣት ተወስኖባቸውም ነበር።




Read 949 times