Saturday, 30 March 2024 20:09

በአዲስ አበባ 1 ሚ. ብር የሚያሸልም የቴኳንዶ ውድድር ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከተለያዩ ክልሎች የተውጣጡ 500 ተሳታፊዎች ይወዳደራሉ  

የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ከሳኦል ኩነቶች አዘጋጅ ጋር በትብብር  ለሚያዘጋጁት የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ኦፕን ቶርናመንት የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረሙ ሲሆን፤ ውድድሩ ከሚያዚያ 19  እስከ ሚያዚያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ይካሄዳል ተብሏል፡፡

ለውድድሩ አሸናፊ የ1 ሚሊዮን ብር ሽልማት  መዘጋጀቱ ተነግሯል፡፡

አዘጋጆቹ ትላንት አርብ መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም በአራት ኪሎ ስፖርት ትምህርት ስልጠና ማዕከል የስብሰባ አዳራሽ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ከሳኦል ኩነቶች አዘጋጅ ጋር በትብብር የሚያዘጋጁት የአዲስ አበባ ወርልድ ቴኳንዶ ኦፕን ቶርናመንት በተለያየ የእድሜ እርከን እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡

ለውድድሩ አሸናፊዎች  የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት መዘጋጀቱ የተገለጸ ሲሆን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሁሉም ክልሎች እንዲሳተፉ እንደሚደረግና ከክልል ለሚመጡ ተወዳዳሪዎች የማረፊያ ቦታ ለማዘጋጀት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸል፡፡

 በዚህ ቶርናመንት እስከ 500 ተወዳዳሪዎች ይሳተፉበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ተወዳዳሪዎች እንድ የእድሜ  እርከናቸው ለመመዝገቢያ ከ300 ብር እስከ 1000 ብር  እንዲከፍሉ ይጠበቃል ተብሏል፡፡



የሳኦል ኩነቶች አዘጋጅ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ደረጄ በመግለጫው ላይ እንደተናገሩት፤ ውድድሩን ለማዘጋጀት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማጠናቀቅ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ለዝግጅቱ ማስኬጃ እስከ 700ሺ  ብር እንደመደቡ ገልፀዋል።

Read 402 times