Friday, 05 April 2024 20:12

አሚጎስና ኢትዮፒካር የኤሌክትሪክ መኪኖችን በብድር ለማቅረብ ተስማሙ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

•  የመጀመሪያውን ዙር የመኪና ርክክብ አድርገዋል

አሚጎስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበርና ኢትዮፒካር፣. የኤሌክትሪክ መኪኖችን በብድር ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ዛሬ ጠዋት መጋቢት 27 ቀን 2016 ዓ.ም  የፈፀሙ ሲሆን፤ የብድር መስፈርቱን ላሟሉ ሰባት የ“ምሰሶ የታክሲ ማህበር” አባላት የመኪና ርክክብ አድርገዋል።

ስምምነቱን የፈፀሙት የአሚጎስ ም/ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘላለም ይልማና የኢትዮፒካር ባለቤት አቶ ሳሙኤል አዲስዓለም  ናቸው።

በስምምነቱ መሰረት፣ የ"ሆን ዞ" አውቶ ፋክተሪ የኢትዮጵያና ምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ ወኪል የሆነው ኢትዮፒካር፣ የአሚጎስ አባላት የሚፈልጓቸውን የኤሌክትሪክ መኪኖች ምቹና ቀልጣፋ በሆነ መልኩ በብድር እንደሚያቀርብ ታውቋል፡፡

 ኢትዮጵያ እንደ ሃገር የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ብሎም የአየር ንብረትን ለመጠበቅ ይረዳ ዘንድ የኤሌክትሪክ መኪናን እንደ አማራጭ የመጠቀም ፖሊሲን እየተገበረች ሲሆን፤ በሃገራችን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ፍላጎትም እያደገ መምጣቱ ተነግሯል፡፡

የአለማችን ተጠቃሽ የኤሌክትሪክ መኪኖች አምራች የሆነው የ"ሆን ዞን" አውቶ ፋክተሪ የኢትዮጵያና ምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ ወኪል ኢትዮፒካር ብራንድ፣ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ወደ ኢትዮጵያ በማስገባት ለተጠቃሚዎች እያቀረበ ይገኛል፡፡

የዜጎችን ኑሮ ባማከለ መልኩ በባንክ ብድር አማራጭ የሚቀርቡት እነዚህ የኤሌክትሪክ መኪኖች፣ የፋብሪካ ዋስትና እንዳላቸው የተገለጸ ሲሆን፤ድርጅቱ መኪኖቹን መቶ በመቶ በብድር ብቻ ለተጠቃሚዎች ለማቅረብም እየሰራ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 728 times Last modified on Friday, 05 April 2024 20:17