Saturday, 26 October 2013 13:50

የአዳማ ጉዞ ማስታወሻ!

የጉዞዬ ማስታወሻ -አጄ!
በአባ ገዳ ሥርዓት ላይ የተመሰረተው የአጄ ማህበር!
“ወፍጮ ካለ ህይወት አለ!”
ድሮ ናዝሬት እያለን ከሻሸመኔ ለከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት የሚመጡ የሻሸመኔ ልጆች ነበሩ። በቀላሉ ከሰው ይግባባሉ፤ ናዝሬት በወሬ ደረጃው የምናውቀው ሻሸመኔ ከአዋሳ ወደ አ.አ ለሚመጣ ሰው ዋና የገበያ ቦታ መሆኗን፣ ኮረዶች የሴትኛ አዳሪነት ኑሮ ለመጀመር ከናዝሬት ወደ ሻሸመኔ ይጐርፉ እንደነበርና ሲያድጉ ወደ አዲሳባ እንደሚሄዱ ነው፡፡ አጄ የምትባለው ከተማ አለች፡፡ በቅሎ አላት… ጤፍ አላት፡፡ በተለይ ሻላ የምትባለው አካባቢ የተፈጥሮ ፀጋ አለው፡፡

የኡታ ዋዩ ማህበር ሰብሳቢው አቶ አማን አሊ -እንዲህ ይላሉ፡- አመሰራረቱ ፤ቀደም ሲል በነበረው የአባ ገዳ ስርዓትና ልምድ መሰረት ነው፡፡ በየ15 ቀን የኡታ ዋዩ ኮሚቴ አባላት ይሰበሰባሉ፡፡ የማህበረሰቡን ችግር እየጠየቁ ይፈታሉ፡፡ 2001 ዓ.ም ላይ በማህበር መልክ ማደራጀትና ማቋቋም አለብን፡፡
በተለይ ጎጂ ባህልን ማስወገድ ትኩረታችን ነበር። ከእየሩሳሌምና ሲዲአይ ጋር ተደራጀን፡፡ 40 ቀበሌ ማህበራት አሉን። የነዚህን ሁለት ሁለት ተወካዮች ጠርተን ፤ (ያኔ ሻላ ወረዳና ሲራሮ ወረዳ አንድ ላይ ነበሩ) 80 አባላት ያሉት ማህበር ሆነ-አባገዳዎች አሉት። ከእነመራሮቹ 93 ማለት ነው፡፡ ሃያ ሃያ ብር መዋጮና እስከ አንድ ሺህ ብር አክሲዮን ሂሳብ አደረግን፡፡ ሁሉም እንዳቅሙ!
በጎጂ ልምድ ማስወገድ ዙሪያ እናትና አባት የሌላቸው ህፃናትን እንርዳ የሚል መርህ ላይ ተመርኩዘን፣ ከ40 ቀበሌ ገበሬ ማህበር (ወደ 60 ኪ.ሜ የሚራራቁ) ትንሽ ቀረብ ቀረብ ከሚሉ 80 ህፃናትን መልምለን፤ወይ አባት ወይ እናት ወይም ሁለቱንም የሌላቸውን፤ የመጨረሻ ደካማ ቤተሰቦች (ከሁለቱ ወረዳዎች ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎች (የወረዳው ቀበሌ ፤የከተማ አባላት፣ የሴቶች ጉዳይ ከአስተዳደር ከፖለቲካ ጋር በመስማማት) ተመልምለው እንዲመጡ አደረግን። (የወረዳው ቀበሌ፣ የከተማ አባላት፣ የሴቶች ጉዳይ፤ ከአስተዳደር፣ ከፖለቲካ ጉዳይ ወዘተ...) የተቀናጀ ስራ ነው፡፡
የእኛ ወረዳ ልዩ የሚያደርገው የፀጥታ ጉዳይ ነው። አጎራባች ቦታዎች ግጭት ነበራቸው፡፡ ይህን የሚፈቱ አባገዳዎች (የኮሚቴ አባላት ናቸው) ችግሩን ፈቱት፡፡
“ከነሱ ጋር ምን ሰራችሁ?”
“ብዙ የልማት ስራዎችን ! 60 ኪ.ሜ ርቀት ግሪሳ ላይ ት/ቤት ሰርተናል፡፡ 200 ተማሪዎች እስከ 3ኛ ክፍል አስተማሪ ቀጥረንላቸው በመማር ላይ ናቸው፡፡ (2002 ዓ.ም ነው)፡፡ ጥሪባ ቀበሌም እንደዚያው፡፡ ደጆ ቀርጠፋም እንደዚያው፡፡
“ሌላስ?”
“ግምባታ! ከከተማ መስተዳደር ጋር በመተባበር 2000 ካ.ሜ ቦታ ጠይቀን አግኝተናል፡፡ 95 ቆርቆሮ ገዝተን፣ ቤት ሰርተን ሁለት ወፍጮ ተክለናል፡፡ ሆኖም ትራንስፎርመር ባለመገኘቱ ስራው አልተጀመረም!...
15 ስሪ አጦችን ራሳቸው ስራ ፈልገው እንዲይዙ አድርገናል- በስልጠና!
የዶሮ እርባታና ቁጠባ ለ15 ሰው ሰው ሰጥተናል
በሊስትሮነት 10 ልጆች ሰልጥነዋል!
10 ኮረዶች በግድ ሊዳሩ የነበሩ፣ ትምህርት ያቋረጡ፣ ለኛ ባመለከቱት መሰረት እንዲማሩ ት/ቤት አስገብተናል (ከ2ኛ -10ኛ ክፍል ደርሰዋል)
በሹፍርና ስራ 3 ልጆች ሰልጥነው አስተምረን ስራ አግኝተዋል!
የፋክስ ማሽን ኮምፒውተር፣ ካዝና አደራጅተናል። የቢሮ ዕቃ አሟልተናል! ዘመናዊ ሂሳብ እየተጠቀምን ነው!
ያለበትን ቦታ ይሄን ጊቢ የሰጠን መዘጋጃ ነው!
ወ/ሮ ማሚና ደቻሳ፤ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል አስገራሚ አቅም ይታይበታል፡፡ ይህን ትላለች፡- “የኡታ ዋዩ ማህበር አባል ነኝ፡፡ ከተለያዩ ቀበሌዎች ተውጣጥተን ነው የመጣነው !ልናለማ! አባ ገዳዎች ስራ ሰርተዋል! የተመደብኩት ቀበሌ ሄጄ ልጆቹ እመለምላለሁ፡፡ በየቤቱ እየዞርኩ፤ በበጎ ፈቃደኝነት! ሁላችንም በጎ ፈቃደኞች ነን! ዘመዴ፣ወገኔ ሳንል እናት የሌላቸውን ህፃናት፤ በእኩል ዐይን፤ የዐርባ ቀበሌ ህፃናት። ትምህርት እንዲያገኙ እናደርጋለን፡፡
መኪና የሚገባበት በመኪና፣ በእግር በሚደረስበት በእግር እየሄድን እንሰራለን፡፡ በግል ኪሳችን፡፡ በበጎ ፈቃደኝነት ነው የምንንቀሳቀሰው፡፡
“ኡታ ዋዩ ምን ማለት ነው?”
“ኡታና ዋዩ ሁለት ወንድማቾች ናቸው! ታላቅና ታናሽ! በትውልድ የዘር ግንድ ናቸው!”
“ሁላችሁም ኡታ ናችሁ?” አልኳቸው፡፡
“አዎ፡፡ ዋይዎችም አሉ”
ቡሽራ ኡኩሌ ናቸው የቁጥር ኮሚቴ ሰብሳቢ። “ከጄክዶ ሲዲአይ ጋር ሆነን ህፃናትን ረዳን፤ የደከሙ አረጋዊያንን አግዘናል፡፡ ወላጅ ልጆች ያጣ ቤተተሰብ ፍየል እየሰጠን ፍየል እንዲገዙ፣ እንዲጠቀሙ አመቻቸን።
ዋናው ነገር ትምህርት ነው- ልጆቹ የሚማሩት በላስቲክ ቤት ነው! ዳስ ውስጥ ናቸው! ት/ቤት አልተሰራም - ት/ቤት ለላጆ አስረክበናል!
ችግሩን ህዝቡ ለእኛ ያለቅሳል-ልጆቹን ማየታችሁ ጥሩ! ግን እኛ አንታያችሁም? ረዳን፡፡ እኛ ራሳችን፤ ራሳችንን መርዳት አለብን!
ወፍጮ ካለ ህይወት አለ! ትራንስፎርመር ካገኘን አገር ይለወጣል! (ከ2002 ጀምሮ - ብር ይዞ ወፍጯችን ተቀምጧል) ጄክዶ እንኳን ቢሄድ መንግሥትንም ባለሃብቶችንም አማክረን - ከአላህ ጋር ብዙ እንሠራለን… መጋዘን እንገነባለን፤ የእህል ግዢ አካሂደን ብዙ እናተርፋለን/ህብረተሰቡን እናግዛለን፡፡ ራሳችን ኤን.ጂ.ኦ (NGO) እንሆናለን ነገ!
በስብሰባችን ውስጥ የባህልና ቱሪዝም ኃላፊው ተገኙ፡፡ ትልቅ ምሥራች ነው! ተጋግዘው እንደሚሠሩ አይቻለሁ፡፡ የባህልና ቱሪዝም ኃላፊው፤ በቅርብ ተባብረው እንደሚሠሩና አብረው ለውጥ እያመጡ መሆኑን አረጋግጠዋል! “ኡታ ዋዩ ከተቋቋመ በኋላ ጐጂ ባህልን በማስቀረት ረገድ ብዙ ሥራ ተሠርቷል፡፡ ግርዛት፣ ጥልፊያና ውርስ ላይ ድንቅ ሠርተዋል፡፡ Remote (ሩቅ) ቦታ በመሆኑ ሥራ-አጥ ይበዛል! ኃይልም የለም፡፡ የማህበሩ ጠቀሜታ እዚህ ጋ ነው!”
“ገበሬውስ እንዴት ያየችኋል?”
“ገበሬው፤ የሚያስፈልገውን አወያዩን ጐናችሁ ነን!” ነው የሚለን፡፡
“ህዝቡ እናንተ ላይ እምነት አለው?”
“ልክ እንደ መንግሥት ነን እኛ!! መንግሥት እኛን ይዞ ነው ያለው-ወረድ ብሎ!”
አንዷን የሥራ አመራር ኮሚቴ አባል፤ “እናንተ ናችሁ ለመንግሥት የምትሠሩት፣ ወይስ መንግሥት ነው እየሠራላችሁ ያለው?” ብዬ ጠየኳት፡፡
“በእኩል ነው ያለነው … በመተባበር እየሠራን ነው”
የቱሪዝምና ባህሉ ኃላፊ፤ ሥራ አጦችን እንድናደራጅ ታስቧል የሚለውን አፅንዖት ሰጥተውታል - እጅ ለእጅ ተያይዞ መጓዝ ይቻላል ማለት ነው! አሉኝና ቢሮ ውስጥ ያሉትን የባህል ዕቃዎች አሳዩኝ- ሾሌ፣ ጭኮ እሚበላበት፣ ጡንጦ-ጮጮ ነው፣ ሞንቃ - የቀንድ ማንኪያ ነው፡፡
ጉራቲ-ትራስ ነው-200 ነው በጉራጊኛ፤ የሙሽራና ሙሽሪት መተሻሻ የቅቤ ቅመም፣ አልባሳትና ጌጣጌጥ … በመገረም አየሁ፡፡
በመጨረሻ፤ “አባት አንድ ነገር ከሠራ ልጁ ያባቱን ፈለግ መከተል አለበት፡፡ በጎ-ፈቃደኝነትን በተማሩት ልጆች መተካት እንፈልጋለን! በዚህ ሥራ አመራር ኮሚቴ እንዲገቡ እንሻለን-እንዲረከቡን!” ያሉኝ ሰብሳቢው ናቸው፡፡ በዚያው ተሰነባበትን፡፡
ቀጣዩ ጉዞዬ ወደ ደብረ ብርሃን ነው!
                                              * * *
የደብረ ብርሃን ጉዞዬ ማስታወሻ
የደብረ ብርሃን ጉዞዬን ልዩ እሚያደርገው ከሌሎች ለእየሩሣሌም ድርጅት ጥናትና ምርምር ከሚያደርጉ ሁለት ሰዎች ጋር መሄዴ ነው - ሆኖም የሚያስገርም አጋጣሚ በመከሰቱ ሁለተኛው ልዩ የሚያደርገው ነገር ፊቴ ድንቅ አለ! እነሆ፡-
የላፍቶው አቶ መንግሥቴ የዘመኔ (የ60ዎቹ ሰው ነው)
የዱሮው የዕድገት በህብረት የዕድገትና የሥራ ዘመቻ ጓዴ፣ አብሮ ዘማቼ፤ ተድላ ነው፡፡
ወደ ደብረ ብርሃን ስገባ የተቀበለኝ የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ ደግሞ አቶ ዓለማየሁ ኃይሌ-የናዝሬት አፄ ገላውዴዎስ ት/ቤት ዩኒት-ሊደሬ!
እንዴት ያለ ጊዜ እንዳሳለፍኩ እንደምትገምቱ ባውቅም፤ አሳምሬ እተርክላችኋለሁ!! ደሞ ወደ ደብረ ብርሃን ዞሬ ልተኛ!!
(ጉዞዬ ይቀጥላል)

Published in ባህል

ዶ/ር ስንታየሁ፣ በነካ አፋቸው እንድንቆጥብ እንደነገሩን፣ “እንዳንሞሳስን” በመከሩን!
ባለፈው ሳምንት በዚሁ ጋዜጣ ላይ ከወጡ መጣጥፎች መካከል፣ በ”ነፃ አስተያየት” አምድና በ “ፖለቲካ በፈገግታ” አምድ የወጡ ሁለት ጽሑፎች በማዕከላዊ ጭብጣቸው ይመሳሰላሉ፤ እርግጥ ነው፣ በርዕዮተ ዓለም ምርጫቸውም አንድ ይመስላሉ። ሁለቱም፣ በመንግስት የፖለቲካዊ ኢኮኖሚ አስተሳሰብና አተገባበር ምርጫ ሳቢያ፣ የዜጐች ኑሮ እየኮሰሰና ቅጥ ያጣ መስዋዕትነት እያስከፈለ እንደሆነ፣ አንደኛው ዝርዝር ማስረጃ አቅርቦ በማስማረር፣ አንደኛው በቀልድ አለዝቦ በማሸሞር ጭብጣቸውን አስረድተዋል፡፡

አንደኛው በንጽጽር ይሟገታል፤ ሌላኛው በፍጥርጥር ይሟገታል። የሁለቱም ጽሑፎች አገራዊ ንበት፣ ሌላ ሶስተኛ ጽሑፍ በመንግስት መጽሔት ላይ እንድማትር አንቅቶኛል፡፡ የዚህ ጽሑፍ የትኩረት አቅጣጫ ግን፣ የሁለቱን መጣጥፎች የርዕሰ ጉዳይ ምርጫ በስሱ አሳይቶ፣ ሦስተኛውን ጽሑፍ በመጠኑ አብዝቶ መጠየቅ ላይ ያተኩራል፡፡ ተተኳሪው ጽሑፍ፣ “በመንግስት የፋይናንስ ድርጅቶች ኤጀንሲ የሕዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ” ባሳተማት፣ “ዐውደ ፋይናንስ” (ቅጽ 1፣ ቁ.1፣ ሚያዚያ 2005 ዓ.ም) መጽሔት ውስጥ፣ ከዶ/ር ስንታየሁ ወ/ሚካኤል ጋር የተደረገው አጭር ቆይታ ነው፡፡ 

በነፃ አስተያየቱ አምድ፣ “ዜጐችን እያቀጨጨ የሚፈረጥም መንግስት…ብዙ አይራመድም፤ ስንት እድሜ ይኖረዋል?” በሚል ርዕስ በቀረበው መጣጥፍ፣ የንግድ ማኒስቴርን መረጃ ጠቅሶ፣ “የውጭ ንግድ ፈቀቅ አላለም፤ ባለበት ደንዝዞ ቆሟል” ይላል። በአይኤምኤፍ መረጃ ላይ ተመስርቶም፣ “የግል ኢንቨስትመንት ተዳክሟል፤ ድርሻው በግማሽ ቀንሷል” ብቻ ብሎ ለፍረጃ አልፈጠነም፤ ባይሆን፣ የአለም ባንክን ሪፖርትም መሠረት አድርጐ፣ “የአገሪቱ የባንክ ብድር፣ 90% ወደ መንግስት ይሄዳል” በማለት በማስረጃ ይሞግታል እንጂ!!
የፀሐፊው ስም ባልተገለፀበት በዚህ ሞጋች መጣጥፍ፣ “የመንግስት ፕሮጀክት ድርሻ እያበበ፣ የግል ኢንቨስትመንት ድርሻ እየተደፈጠጠና እየቀጨጨ የመጣው፣ በተለያዩ ምክንያቶች ቢሆንም፣ ትልቁና ዋናው ሰበብ ግን ከባንክ ብድር ጋር የተያያዘ ነው” በማለት፣ የባንኮች ብድር በየጊዜው ከግል የኢንቨስትመንት ተቋማት እየራቀ፣ ወደ መንግስት ተቋማትና ፕሮጀክቶች እየጐረፈ እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡

መጣጥፉ፣ በአንዳንድ የመንግስት ጽንፈኛ ካድሬዎች፣ “የኒዮ ሊበራሊስቶች የተሳሳተ አስተያየት፣ ወይም የልማታዊ መንግስት አቆርቋዦች ጭፍን ዕይታ” ተብሎ የመፈረጅ እድሉ የሚበዛ ይመስለኛል፡፡ በዚህ የፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ሂሣዊ ትንተና፣ “መንግስት ራሱን በራሱ ጠልፎ አልጣለም ትላላችሁ?” በማለት የኢህአዴግ ታህታዊ ሥሪትና ላዕላዊ ተክለ ሰውነት ሊሸከመው የማይችለውን ከባድ ጥያቄ ይሰነዝራል፡፡ የሚገርመው ግን፣ የኢህአዴግ ድንገተኛ ህፀጽ ላይ ተመሥርተው፣ አንዳንድ ጊዜ እነርሱም ወደ ሥልጣን ቢመጡ ሊያስወግዱት ቀርቶ ሊቀርፉት የማይቻላቸውን ሀገራዊ ችግሮች በማራገብ ላይ ሃይላቸውን የሚያባክኑት አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ እንደዚህ በመረጃ ላይ እየተደገፉ ሲሞግቱ አይታይም - ከአንድ የተቃዋሚ ድርጅት በቀር፡፡

ብዙዎቹ ብዙ ጊዜ፣ “ኢህአዴግ ሠፍሮ የሰጣቸውን አጀንዳ ነው የሚያራግቡት” የሚባሉትም፣ እንደዚህ መንግስት ሊደብቀው የማይችለውን ስህተቱን አንጥረው አውጥተው ስለማይሟገቱ ይመስለኛል፡፡
የ “ፖለቲካ በፈገግታ” አምድ ፀሐፊው አቶ ኤልያስ ያስነበቡን ሁለተኛው ተጠቃሽ መጣጥፍ፣ “ዲሞክራሲያችን በስንት ዲጂት እንዳደገ ይነገረን!” ይላል በርዕሡ፡፡ አምደኛው፣ “ለልማት የሚከፈለው መስዋዕትነት በ‘ደብል ዲጂት’ መቀነስ አለበት! ልማትና ትዕግስት ያላቸው ቁርኝት ዘንድሮ ገባኝ!” በማለት ያሸሞሩት፣ በምፀታዊ ገለፃ ፈገግታን ለማጫር ብቻ አልነበረም፤ ይልቁንም፣ የልማትንና በልማት ስም የሚደረግ መስዋዕትነትን በማነፃፀር፣ ሁለቱ ጉዳዮች በተቃርኖ ጽንፍ ላይ የሚቀመጡ፣ የአያዎ /Paradox/ አኗኗር ዘይቤያችን ወይም የአያዎ ፖለቲካችን ማናበቢያ ተምሣሌት መሆናቸውን ለመግለጽ እንጂ፡፡
መጣጥፉ፣ በምፀታዊና አሽሙራዊ አቀራረቡ፣ ፖለቲካዊ ምሬቶችን አለዝቦ የማህበራዊ ሂስ መልክ ቢያጐናጽፋቸውም፣ “የሰለጠኑ አገራት እኮ እንኳን ለልማት፣ ለጦርነት የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመቀነስ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡ ሰው አልባ ተዋጊ ጀቶችን ለምን የፈጠሩ ይመስላችኋል?” የሚል የመረረ ጥያቄ ከማንሳት ያገደው የለም፤ በመቋጫ አረፍተ ነገሮቹ፣ “እኛም የልማት መስዋዕትነታችንን ‘ደብል ዲጂት’ መቀነስ አለብን!! (ሞትን እኮ!)” በማለት መንግስት በአሀዝ ላይ የተደገፈ የልማት ፕሮፖጋንዳ አብዝቶ ከሚለፍፍበት ማዕዘን በትይዩ፣ የዜጐችን “ልማታዊ መስዋዕትነት” በአሀዝ ተደግፎ እንዲገለፅለት ይጠይቃል፡፡ የዜጐችን መከራ አጉልቶ የማሣየቱ መራር እውነት የሚመነጨው ግን፣ የልማትን እና ለልማት ሢባል የሚደረግ መስዋዕትነትን፣ ያውም፣ በአህዛዊ ስሌት ተደግፎ እንዲገለጽ ከተፈለገበት፣ ምፀታዊ አቀራረቡ ነው ማለት ይቻላል፡፡ እናም፣ የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ፣ “መስዋዕትነት በደብል ዲጂት ይቀነስ ቢሉ፣ ጦም እያደሩ መቆጠብ ትዝ አለኝ…” እስከ ማለት ደረሠ። አብዛኛው ዜጋ ከድህነት ወለል በታች በሆነ የቁልቁለት ኑሮ ውስጥ እንደሚዳክር እየታወቀ፣ “በአለፉት 37 ዓመታት አማካይ የቁጠባ መጠን ሲታይ 7 በመቶ አካባቢ ነው፡፡

እንደዚሁም ይህን አሀዝ ከአፍሪካና ከሌላው የዓለም ክፍል ጋር ስናወዳድረው ከአማካይ በታች ሆኖ እናገኘዋለን” የሚል ግርድፍ መረጃ ሢቀርብ ማየት ስሜት ውስጥ የሚከት ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም፣ የዜጐችን የገቢ መጠንና የመንግሥትን ሥራ የመፍጠር አቅም ያልነካና ያልገለፀ በመሆኑ፣ በግልባጩ “ዜጐች ጦማችሁን እያደራችሁ፣ ያላችሁን ጥሪት በእኔ ቋት ውስጥ አስገቡና እኔ ለፈለግሁት ተግባር ላውለው” የሚል የፈርጣማ ጡንቸኛ መንግስት መገለጫ ይመስላልና፡፡
ቀደም ሲል በተጠቀሰው መጽሔት፣ “የእንግዳችን ዐምድ” ላይ የመጀመሪያው እንግዳ ሆነው የቀረቡት፣ የመንግስት የፋይናንስ ድርጅቶች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር ስንታየሁ ወ/ሚካኤል ናቸው፡፡ ዶክተሩ የመንግሥታቸውን አቋም በሚያስረግጠው መግለጫቸው፣ “በቅርብ ጊዜ ታሪካችን፣ ከድህነት ባሻገር የከፋ ችግር የዲሞክራሲና መልካም አስተዳደር ዕጦት እንደነበረ … ይህን ድህነትና ያልተመጣጠነ የሀብትና የገቢ ክፍፍል ከሥር መሠረቱ በመናድ በምትኩ በየጊዜው ዕድገት እየተመዘገበና ይህ ዕድገት ደግሞ ተመጣጣኝና ዜጐች በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆኑበት ሥርዓት ለመፍጠር … የልማት እንቅስቃሴውን በታሰበበት ለማስኬድ ትክክለኛ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል” ይላሉ፡፡
በዋና ዳይሬክተሩ ንግግር ውስጥ “ትክክለኛ አቅጣጫ” የሚለውን ልኬት ጠቋሚ፣ ሚዛን ሠፋሪ ገለፃ ሣንረሣ፣ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ 4 ዋነኛ ግቦች መብራራታቸውን ልብ ይሏል፡፡ “የአገራችን የኢኮኖሚ እድገት በከፍተኛው የእድገት አማራጭ (Scenario) 14.9 በመቶ ዕድገት ላይ “መድረስ እና “የተረጋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ” መፍጠር የሚሉት ሁለቱ ዋነኛ ግቦችን ለማሣካት ቁልፍ ጉዳይ፣ ቀጣይነት ያለው የቁጠባ ሥርዓት ሢዘረጋ እንደሆነ ዳይሬክተሩ በአፅንኦት ያስረዳሉ፡፡
የኢኮኖሚ እድገት (ያውም 14.9 በመቶ) ለማስመዝገብ ከሚያስፈልጉ ነገሮች አንዱ ኢንቨስትመንት መሆኑ ተገልጿል፡፡ “ኢንቨስትመንት ደግሞ የሚመጣው ቀጣይነት ያለው ቁጠባ ሲኖር ነው” ይላሉ፡፡ አስከትለውም፣ ሦስቱ የመንግስት ባንኮች ቁጠባን እንዴት እንደሚያሣልጡ ሢያብራሩ፣ የኢንቨስትመንቱን ጉዳይ በዝርዝር አላስተነተኑም፡፡ ይህ የሚያመለክተው ደግሞ፣ የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚና ኢንቨስትመንት ካልተሥፋፋ፣ ዜጐች ተቀጣሪና አምራች የሚሆኑበት ተጠያቂዊ ሥርዓት ለመፍጠር እንደሚከብድ ግምት ውስጥ አለመግባቱን ነው፡፡
በሌላ በኩል ዳይሬክተሩ “ትክክለኛ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል” ሲሉ፣ የግሉን ክፍለ ኢኮኖሚና ኢንቨስትመንት ከማበረታታት ይልቅ፣ የመንግሥትን ጡንቻ የሚያፈረጥም፣ አካሄድን ማሞገሳቸው ነው፤ የተሻለ የሥራ ፈጠራና ምርታማነት ማሣደግን ያላጤነ “ጦም እየታደረም ቢሆን ቁጠባ እንዲደረግ” ማለታቸውም ይመስላል፡፡ ለዚህ ደግሞ፣ “በዚህ የለውጥ እንቅስቃሴ ሊደረጉ ከሚገባቸው ነገሮች ውስጥ ቁጠባን ማሰባሰብና ለተገቢው ቦታ ማዋል … ሶስቱም ባንኮቻችን ይህንን እንደ ዋነኛ ተልዕኮ የሚረዱበትና የሚንቀሳቀሱበት ሁኔታ ላይ ነው ያለነው” የሚለውን መግለጫ ብቻ ማስተንተን ሊበቃ ይችላል፡፡
እዚህ ላይ ዳይሬክተሩ እንዳሉት፣ የቁጠባ ባህል መፍጠር የቆጠቡትንም ለተገቢው ቦታ ማዋል ተመራጭ መንገድ ነው፡፡ ጉዳዩ ግን፣ እንደሚባለው፣ “በትክክለኛ አቅጣጫ” ተግባራዊ እየሆነ ነው ወይ? ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው ምላሽ ፈታኝ መሆኑ ነው፡፡
ዶ/ር ስንታየሁ፣ “ቸር ተመኝ፤ ቸር እንድታገኝ” የሚለውን ሀገራዊ ብሂል ሠንቀው፣ በጐ አሣቢ ወይም “ባለ ራዕይ” ሊያሥብላቸው የሚችሉ፣ ግን መሠረት የሌላቸው የሚመስሉ ሀሣቦችን አንስተዋል፡፡ ለምሣሌ፡- “በወጣትነት ዘመናችን በአብዛኛው ከ18-25 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ለወደፊት የሚያስፈልገንን ቤት፣ መኪና፣ የልጆች ት/ቤት ወጪና ሌሎች ወጪዎች በተለይ የመንግስት ሠራተኛው በአንድ ጊዜ ሊያገኝ አይችልም፡፡ በመሆኑም ለእነዚህ የሚያስፈልገውን ገንዘብ ከወዲሁ በማስቀመጥ ለሚፈለገው ዓላማ ማድረግ ይቻላል” ይላሉ፡፡
አሁን ታዲያ፣ “ይኼ ማብራሪያ እንኳን ከኢትዮጵያ ጋር፣ ከአሜሪካ ጋርስ አብሮ ይሄዳል?” ብለን ብንጠይቅ ይፈረድብናል? ለመሆኑ ከ18-25 ዓመት ባለው የእድሜ ክልል ያለ የመንግስት ሠራተኛ ቀርቶ፣ በ40ዎቹ መጨረሻ እድሜ ላይ የሚገመቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከደመወዛቸው ቆጥበው፣ እንኳን ቤትና መኪና መግዛት ቀርቶ ልጆቻቸውን ከፍለው ማስተማር ይችላሉ!? (ማለቴ፣ አሁን ተጨምሮላቸው ካልሆነ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር “ለህዳሴው ግድብም፣ ለድርጅትም…” ተቆራርጦባቸው ከእጃቸው የሚገባው፣ ከ4ሺ 5መቶ ብዙም እንደማይበልጥ ወይዘሮ አዜብ የነገሩንን አስታውሼ ነው - ምን ላድርግ?)
በነገራችን ላይ፣ የሀገራችን ማዕከላዊ ስታስቲክሥ ኤጀንሲ በ2005 ዓ.ም ባወጣው መረጃ መሠረት፣ ከ15-29 ዓመት እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙት ወጣቶች በሀገሪቱ ውስጥ ከተንሠራፋው ሥራ አጥነት የ23.3% ድርሻ አላቸው፡፡ ወይም ከሀገሪቱ ሥራ አጦች መካከል ሩብ ያህሉ፣ ከ15-29 ዓመት ያሉ ወጣቶች ናቸው ማለት ነው፡፡ የእርሻው መሬት ተበጣጥሶ በተራቆተበት፣ ሥራ ፈጣሪ የኢንቨስትመንት አማራጮች በመንግስት ፈርጣማ ጉልበት ሣቢያ እየተቀዛቀዘ ባሉበት በአሁኑ ጊዜ የወር ደመወዝተኛ፣ በተለይ የመንግሥት ተቀጣሪዎች ከየት አምጥተው እንደሚቆጥቡም አልተገለፀም፡፡ የዋጋ ግሽበቱ ጥሬ ገንዘብ በባንክ ከማስቀመጥ፣ እንደ ወርቅ ባሉ ቁሦች ቀይሮ ሥለማስቀመጡ አማራጭ ጠቃሚነትና ጐጂነት አልተወሣም፡፡
የክቡር ዳይሬክተር መግለጫ፣ የቁጠባን ባህል አስፈላጊነት ለማስረዳት በተጨባጭ ማስረጃዎች ላይ ለመቆም ድፍረት ያነሰው ይመስላል፡፡ “ጦም እያደሩና እየተበደሩ” መቆጠብ ግድ የሚል ያህል በተሠበከበት በዚህ ንግግር፣ ዜጐች “ልማታዊ መስዋዕትነት” ከፍለው የቆጠቡት ገንዘብ “በተገቢው ቦታ ይውላል” ተባለ እንጂ እንዴት እየዋለ እንደነበረ ጥቂት አመላካች ማስረጃ ማቅረብ አልተቻለም፡፡ በዜጐች ላይ የመንግሥት ጡንቻ እንደሚፈረጥም እኛ ጠረጠርን እንጂ፣ የዶክተሩ ማብራሪያ ሰሞኑን በሙስና ክስ የተመሰረተባቸውን አይነት ትናንሽ የቡድን መንግሥታትን ረጅም እጆች ሊጠቁም አልቻለም፡፡
እናም ዶ/ር ስንታየሁ፣ ምን አለ ዛሬ እንኳን እንድንቆጥብ እንደነገሩን፣ “እንዳንሞሳስን” በመከሩን! “ሙስና እንዳንሠራ” የሚለውን፣ “እንዳንሞሳስን” እንዲል የኢትዮጵያዊያን ቋንቋ በአማርኛ፡፡

ኢሕአዴግም ተቃዋሚም “ኳሷ እኛ ጋ የለችም” ብለዋል

ባለፈው ሰሞን ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ በፓርላማ የተቃዋሚ ተወካይ ለሆኑት የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ ጥያቄና አስተያየት የሰጡትን ምላሽ ሰምታችሁልኛል? (ካልሰማችሁ አመለጣችሁ!) የተከበሩ አቶ ግርማ እንዲህ አሉ፡- (ሃሳባቸውንበጥቅሉ አቀርባለሁ) “መንግስት ከተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ምክክር ካላደረገ የውጭ ኢንቨስተሮችን መሳብ አይሞከርም” የሚል ነው - ሃሳቡ፡፡ ጠ/ሚኒስትሩ ሲመልሱም (ሌላውን ትተን አንኳሩን ብቻ) “እስካሁን የውጭ ኢንቨስተሮች ለመስራት ሲመጡ ሌላ ሌላውን እንጂ ከተቃዋሚዎች ጋር ትመካከራላችሁ ወይ? አላሉንም” ብለዋል (ጨዋታ ጨምረዋል ልበል!) 

እኔም ወግ ለመጀመር ያህል እቺን ካልኩኝ ወደ ቁምነገሩ ልግባ፡፡ እንግዲህ ዘመኑ የ “ልማት” ነውና የወጋችንም የመጀመርያ ማጠንጠኛ ልማት እንዲሆን ወድጄአለሁ፡፡ እርግጠኛ ነኝ … በዚህ “ቅዱስ” ሃሳቤ መቶ በመቶ ትስማማላችሁ፡፡ ምናልባት ቅሬታ ያለውም ካለ የአገሩን ተጨባጭ እውነታ የዘነጋ ነው ባይ ነኝ። እኔ ግን ቢያንስ መንግሥታችን “ልማታዊ መንግሥት” መሆኑን ላስታውሰው እወዳለሁ። በነገራችሁ ላይ ስለ ልማት ለማውራት የግድ “ልማታዊ ጋዜጠኛ” መሆን አያስፈልግም፡፡ (የሮኬት ሳይንስ እኮ አይደለም!)
እኔ የምለው ግን … አውራ ፓርቲያችን ኢህአዴግ “የልማት ዕቅድህ ካልተሳካ ህዝብ ይታዘብሃል” የሚል ሟርት በሰማ ቁጥር እኛ (ህዝብ ማለቴ ነው) ላይ መንጠልጠል አለበት እንዴ? (ጥያቄው ከጥላቻ ፖለቲካ የመነጨ አይደለም!)
ይሄውላችሁ … ሁለት አመት ቀርቶታል የተባለው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ እንደታሰበው ባይሳካ (አያድርገውና!) በምን ስሌት ነው የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ የመንግስት መሆኑ ቀርቶ የህዝብ ዕቅድ የሚሆነው? ራሱ ኢህአዴግ አመንጭቶ ተግባራዊ ያደረገውን ዕቅድ እንዴት ለህዝብ ይሰጣል? (የኢህአዴግ ደግነት በዛብን!) ትንሽ ጥርጣሬ ግን አድሮብኛል - በደግነቱ ላይ፡፡ ለምን አትሉም? የራስን የልማትና ፖሊሲ ለህዝብ አሳልፎ የሚሰጥ አፍሪካዊ ፓርቲ አይተን አናውቅማ፡፡ አቦይ ስብሃት፤ “ከአፍሪካ ፓርቲዎች የተለየ ፓርቲ ነው” ያሉት ለነገሩ ገባኝ! የኢህአዴግም ባህል እኮ አይደለም፡፡ (ፓርቲው ባህሉን ለወጠ እንዴ?) ለምሳሌ ተከታታዩ የኢኮኖሚ ዕድገት የልማታዊ መንግስቱን ትክክለኛ አቅጣጫ የሚያመላክት ነው ሲባል እንጂ “የህዝቡ ውጤት ነው” ሲባል አልሰማንም (በስህተት እንኳን!) ታዲያ አሁን ምን ተገኘ? (“ልቤ ጠረጠረ” አለ፤ አንዱ የፌስቡክ ፀሐፊ)
በቅርቡ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም በፓርላማ የተናገሩትን ስሰማ፤ ኢህአዴግ ስኬቱን በግሉ፣ ውድቀቱን ከህዝቡ ጋር ለመካፈል እንዳሰበ ጠርጥሬአለሁ፡፡ ቆይ በምን ተአምር ነው … የባቡሩ ፕሮጀክቱ እክል ቢገጥመው እኛ (ህዝቦች ማለቴ ነው) ተጠያቂ የምንሆነው? ከምሬ እኮ ነው…የልማት ፖሊሲው - የኢህአዴግ! እቅዱ - የኢህአዴግ! አተገባበሩ - የኢህአዴግ! በዚህ ውስጥ ታዲያ የእኛ ሚና የቱ ጋ ነው? ጠ/ሚኒስትሩ ግን “ልማቱ ባይሳካ … በህዝቡ ትፈተኑበታላችሁ” ለተባለው የአቶ ግርማ አስተያየት፤ “ልማቱ እኮ የህዝብ ነው፤ የሚሰራው ህዝቡ ነው፤ እኛ አስተባባሪ ነን” ሲሉ ከተጠያቂነት ለማምለጥ ሞክረዋል፡፡ እኔ የምለው… እኛ እኮ ኢህአዴግን የምንደግፈው በአስተባባሪነቱ አይደለም፤ በልማታዊ መንግስትነቱ እንጂ!! (ወዴት ሸርተት ሸርተት!) እናላችሁ … ልማቱና ትራንስፎርሜሽኑ እክል ሲገጥመው “የህዝቡ ነው” ምናምን አያዋጣም! በነገራችሁ ላይ … በ2002 አገራዊ ምርጫ ሌሊት ወጥተን ለአውራው ፓርቲ ድምፃችንን የሰጠነው እኮ ኢህአዴግ (ልማታዊ መንግስታችን ማለቴ ነው!) ይሄን ሃላፊነትና ተጠያቂነት መሸከሚያ በቂ ጫንቃ አለው ብለን ነው፡፡ ያለዚያማ ሌላ የተሻለ ትከሻ እናፈላልግ ነበር፡፡

(ከተቃዋሚዎችም ቢሆን!) ባይሆን ጠ/ሚኒስትሩ የሰጡት ሌላኛው ሰበብ የተሻለ ነው፡፡ “እቅዶቹሰፋፊ ናቸው፤ የተለጠጡ ናቸው፤ ወገብ የሚያጐብጡ ናቸው” ብለዋል- ጠ/ሚኒስትሩ። ባይሳካልንም ለጥጠን ስላቀድን ችግር የለም እንደማለት፡፡ (አሪፍ ማምለጫ ይሏል ይሄ ነው!) እናላችሁ … ሥራችን ይለይ፤ የኢህአዴግና የእኛ! እሱ ተመራጭ፤ እኛ መራጭ ነን፤ እሱ አገልጋይ፤ እኛ ተገልጋይ፤ እሱ መንግስት፤እኛ ህዝብ ነን!! እሱ ተጠያቂ፤ እኛ ጠያቂ!! “ልማቱን የሚሰራው ህዝብ ነው!”
እስቲ ደሞ ለአፍታ ወደ አፍሪካይቱ ሌላ አገር እንሂድ፡፡ ሰሞኑን በቢቢሲ አፍሪካ የሰማሁት መረጃ፣ ትንሽ አፅናንቶኛል፡፡ (የሚያፅናና ነገር አይጥፋ አቦ!) መረጃው ምን መሰላችሁ? ናይጄሪያም እንደኛ በመብራት መጥፋት መሰቃየቷ እንደቀጠለ የሚገልፅ ነው፡፡ በርግጥ የናይጄሪያ መንግሥት (እንደማንኛውም አፍሪካዊ መንግሥት) ብዙ ሚሊዮን ዶላሮች በማውጣት ናይጄሪያውያንን በመብራት ሊያንበሸብሻቸው እንደሆነ አብስሯል። (ሥራው ሳይሆን ችሮታ- አይመስልም?) የሚያሳዝነው ግን ማንም ያመነው አለመኖሩ ነው፡፡ በጉዳዩ ላይ ለቢቢሲ አስተያየቱን የሰነዘረ አንድ ናይጄሪያዊ፤ የናይጄሪያ ባለስልጣናትን በከባዱ ወርፏቸዋል - “Big liars!` በማለት (ባለ ከባድ ሚዛን ውሸታሞች! ማለቱ ነው!) እናላችሁ… በመብራት መቆራረጥና መጥፋት መከራችንን የምንበላው እኛ የጦቢያ ልጆች ብቻ እንዳልሆንን ስገነዘብ ነው ትንሽም ቢሆን የተፅናናሁት - መከራችንን የሚጋሩን አፍሪካውያን ወንድሞችና እህቶች አገኘን ብዬ!
እኔ የምላችሁ… አፍሪካ ህብረት (“የአፍሪካ መሪዎች ማህበር” ቢባል ይሻላል!) በቅርቡ በዓለም አቀፉ የወንጀል ፍ/ቤት (ICC) ላይ የጀመረውን ዘመቻ ሰምታችሁልኛል? ኧረ ከዘመቻም ያልፋል፡፡ አመፅ ወይም አድማ ነገር እኮ ነው የሚመስለው፡፡ (ለካስ መሪዎችም ያምፃሉ!)
ግን እኮ ለዘመቻም በሉት ለአመፃ ወይም ደግሞ ለአድማ መተባበር ይፈልጋል፡፡ ለአንድ ዓላማ በአንድ ልብ መቆም! …የአፍሪካ መሪዎች ያለመደባቸውን ትብብር ዘንድሮ ከየት እንዳመጡት ግርም ብሎኛል፡፡
አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ግን ትብብሩ የተፈጠረው “ነግ በእኔ” ከሚል የስጋት ስሜት ነው ብለዋል። አያችሁ … ዓለምአቀፍ ፍ/ቤቱ በተገኙበት ተይዘው እንዲመጡለት ማዘዣ የቆረጠባቸው የሱዳንና የኬንያ ፕሬዚዳንቶች ጉዳይ በ“አድማ” እልባት ካላገኘ እንደለመደው ነገ ወደ ማን ሊዞር እንደሚችል መገመት ከባድ ነው፡፡ (“ምን ያለበት ዝላይ አይችልም” አሉ!) እናም ዓለም አቀፉ ፍ/ቤት ኢ-ፍትሃዊ ነው፤ አፍሪካ የራሷን ችግር በራሷ ልትፈታ ይገባል” በሚል እየተሟገቱ ወደፊት በአፍሪካ ህብረት ስለሚቋቋመው የአፍሪካውያን ፍ/ቤት ማለም ጀምረዋል፡፡ (ሶማሊያ የሚመደብ አፍሪካዊ ሰላም አስከባሪ ኃይል ጠፍቶ እንደነበር ልብ ይሏል!)
ይኼውላችሁ… የአፍሪካውያን ፍ/ቤት መቋቋሙ ላይ ተቃውሞ የለኝም፡፡ እንደውም “እስከዛሬ የት ነበሩ?” ባይ ነኝ፡፡ እዚህ ጋ ግን (በኢህአዴግ ቋንቋ መናገር ይፈቀድልኝ) በቅርቡ ዘመቻ የከፈቱት የአፍሪካ መሪዎች ወይም ህብረቱ ማጥራት ያለባቸው አንኳር ጉዳዮች ያሉ ይመስለኛል፡፡ እኔም በግሌ (በአፍሪካዊነቴ ማለቴ ነው!) እርማቸውን በጋራ ለቆሙት የአፍሪካ መሪዎች የምወረውራቸው አንዳንድ ያልገቡኝ ጥያቄዎች አሉ፡፡ (ይቅርታ አድርጉልኝና… የአፍሪካ መሪዎች የማይፈቱ እንቆቅልሾች ይመስሉኛል!) እስቲ እነ ኢዲ አሚንን፣ እነ ሞቡቱን፣ እነ ጋዳፊን፣ እነ ሙባረክን፣ እነ ሙጋቤን እና ሌሎቹን የለየላቸው አምባገነን መሪዎች አስቧቸው! (ልማታዊ መንግስታትን አይመለከትም!) ቆይ… ምናቸው ይገባል? አንዳንዴ ሳስበውማ … የአፍሪካ ህዝቦች ፈጣሪያቸውን ክፉኛ በድለውት ለቅጣት የተላኩ ይመስሉኛል - አምባገነኖቹ የአፍሪካ መሪዎች!! (ግን ፈጣሪ እንዴት ቢጨክንብን ነው?!) አያችሁልኝ… የእኔ ነገር! የአምባገነኖችን ጉዳይ እያመነዠኩ ጥያቄዎቹን ዘነጋኋቸው፡፡ እናላችሁ… አፍሪካ ህብረትም ሆነ መሪዎቹ በሁለቱ ፕሬዚዳንቶች ጉዳይ አቋማቸው ምንድነው? (ስለተረሳሳ እኮ ነው!) ዓለም አቀፉ ፍ/ቤት የሚያቀርብባቸውን ውንጀላ አልፈፀሙም ነው? ወይስ “ጉዳዩ እሱን አይመለከተውም፤ ለእኛ ለአፍሪካውያን ይተውልን” ተብሎ ነው? አልታያችሁም … የአፍሪካ ፍ/ቤት አፍሪካውያን መሪዎች ላይ ሲፈርድ? በነገራችሁ ላይ ጠ/ሚኒስትራችንና የአፍሪካ ህብረት ሊ/መንበር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ “ጨፍጫፊዎችና ወንጀል የፈፀሙ የአፍሪካ መሪዎች አይከሰሱ” የሚል አቋም እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡ (ትንሽ ያፅናናል ልበል?)
ወጋችንን በአገራዊ ፖለቲካ ብንቋጨውስ? እንደኔ ታዝባችሁ ከሆነ … ብዙ ጊዜ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች “ኳሷ በኢህአዴግ ወይም በመንግስት እግር ስር ናት!” እያሉ ሲናገሩ እንሰማ ነበር፡፡ ሰሞኑን ደግሞ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ “ኳሷ በተቃዋሚዎች እግር ስር ናት!” ሲሉ ሰማሁ፡፡ ኳሷ ተሰውራለች ማለት እኮ ነው! አያችሁ … የፖለቲካ ኳሷ ጠፍታለች፤ የት እንዳለች ተቃዋሚም ሆነ ኢህአዴግ አያውቁም፡፡ ስለዚህ ኳስ አገኘን ብለው እግር ለእግር ሲማቱ የከረሙት ለዚህ እኮ ነው መቆሳሰልና ስብራት የበዛው፡፡ እናም ቀዳሚው ስራችን የፖለቲካ ኳሷን ፈልጐ ማግኘት ነው፡፡ ኢህአዴግና ተቃዋሚ ኳስ በሌለበት ሜዳ ላይ ተፋጥጠዋል፡፡ እቺን ኳስ አፈላላጊ ኮሚቴ በአፋጣኝ ማቋቋም አለብን (አንድዬ ይርዳና!)

በኢቴቪ የምናያቸው ቪዲዮዎችና ምስሎች፣ የተደፈጠጡና የተጣመሙ ሆነዋል - ስንት ወሩ? አልተስተካከለም።
በኢቴቪ የሚሰራጩ የተዛቡና የተሳሳቱ ዜናዎች ወይም ዘገባዎች ያሳፍራሉ፤ ደግሞም መላ ያለው አይመስልም።

አንዳንዴ፣ በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሰራጩ ዜናዎችን መስማት ያሳቅቃል፤ ወይም ያዝናናል። በሌላ በኩል ደግሞ ቀሽም ስህተት ስለሆነ ያዝናናል። ከግማሽ ምዕተ አመት በላይ እድሜ ያስቆጠሩ የአገሪቱ ብቸኛ የቴሌቪዥንና የሬድዮ አንጋፋ ድርጅቶች መረጃ ሲሳሳቱና ሲያዛቡ ማየት ያሳቅቃል።
ባለፈው ረቡዕ ምሽት የተሰራጨውን ዜና መጥቀስ እችላለሁ። በአፍጋኒስታን የተሰማራው ሰላም አስከባሪ ሃይል አገሪቱን ለቅቆ የሚወጣበትን የጊዜ ገደብ ለመቁረጥ እንዳልቻለ የሚገልፅ ነው ዜናው። ሰላም አስከባሪው ሃይል ወደ አፍጋኒስታን የተሰማራው፣ በእርስበርስ ግጭት መነሻነት እንደሆነም ዜናው ይጠቅሳል። የአሜሪካ እና የአጋሮቿ ጦር ሃይል ወደ አፍጋኒስታን ለምን እንደተሰማራ ተረሳ ማለት ነው? አስር አመት ያስቆጠረ ዘመቻ ስለሆነ ኢቲቪ አያስታውሰው ይሆናል፡፡ ግን፤ እንዴት እንዴት የቢን ላደንና የአልቃይዳ ሽብር ሊረሳ ይችላል? በኒውዮርክና በዋሺንግተን የ3ሺ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈ የሽብር ጥቃት መፈፀማቸውስ እንዴት ይዘነጋል? ከዚያ በኋላ፣ በአሜሪካ መሪነት፣ በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ወታደሮች ወደ አፍጋኒስታን መዝመታቸውን መላው አለም ያውቀዋል፡፡

ለኢቲቪ እንዴት እንደተሰወረበት እንጃ! አናስታውስም? ለአመታት በመንዛዛቱ “ዘመቻነቱ”ና ውጤታማነቱ ቢደበዝዝም፣ በጊዜው ትክክለኛ እርምጃ ነበር።
የሆነ ሆኖ፣ የአሜሪካ ዘመቻ ቢን ላደንን ለመግደል፣ አልቃይዳን ለመውጋትና ጥላ ከለላ የሆናቸውን የታሊባንን ሃይል ከስልጣን ለማስወገድ እንጂ፣ “ሰላም ለማስከበር” የተካሄደ ዘመቻ አይደለም። በአጭሩ፣ ለጦርነት ነው፣ አሜሪካና አጋሮቿ ወታደሮቻቸውን ያዘመቱት። በእርግጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ የወታደሮቹ ቁጥር ቀንሷል። ነገር ግን፣ ዛሬ ከአስር አመት በኋላም፣ ገሚሶቹ ከአሜሪካ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ከሌሎች የኔቶ አባል አገራት የተውጣጡ ወደ መቶ ሺ የሚጠጉ ወታደሮች በአፍጋኒስታን እንደተሰማሩ ናቸው። ሰላም አስከባሪ የሚሰማራው ደግሞ፣ “ሰላም ሰፍኗል” ተብሎ ሲታሰብ ነው - “ሰላምን ለመጠበቅ”። የተባበሩት መንግስታት ሰላም አስከባሪ ሃይል ወደ ሶማሊያ ያልተሰማራው ለምን ሆነና? በአገሪቱ ሰላም የለም፣ ሰላም ከሌላ ሰላምን ማስከበር አይቻልም በሚል ነው። ታዲያ የአፍሪካ ህብረት፣ ለምን “ሰላም አስከባሪ ሃይል” አሰማራ? “የተወሰነ ሰላም ተገኝቷል” ብሎ ስላመነ ነዋ።
በአፍጋኒስታን ግን፣ የሰላም አስከባሪ ሃይል የማሰማራት ሃሳብ በጭራሽ ተነስቶ አያውቅም። ሰሞኑን ስለ አፍጋኒስታን እና ስለ አሜሪካ ወታደሮች የሚያወሱ በሺ የሚቆጠሩ ዜናዎችና ዘገባዎች ቢሰራጩም፣ በአንዳቸውም ላይ “ሰላም አስከባሪ ሃይል” የሚል አባባል አታገኙም - በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በተሰራጨው ቀሽም ዜና ካልሆነ በቀር። በእርግጥ፣ ዜናውን የሰራው ጋዜጠኛ ቀሽም ላይሆን ይችላል። ደግሞም፣ በዜናው የተካተቱ በርካታ መረጃዎች ሲታዩ፣ ጋዜጠኛው ቀሽም እንዳልሆነ ይጠቁማሉ። ቀሽም ስህተት እንዳይፈጠር የሚከላከል አሰራርና ባህል በድርጅቱ ውስጥ አለመኖሩ ይመስለኛል - ዋናው ችግር።
“የሜርከል ፓርቲ አሸነፈ፣ ፓርቲያቸው ተሸነፈ”
በቅርቡ በጀርመን በተካሄደው ምርጫ በአብላጫ ድምፅ ያሸነፈውና በአንጌላ ሜርከል የሚመራው ፓርቲ፤ አዲስ መንግስት ለመመስረት ውይይት እያካሄደ ነው። ሲዲዩ የተሰኘው ፓርቲ ከነአጋሩ፣ በምርጫው 42 በመቶ ድምፅ አግኝቷል። ታዲያ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ የተሰራጨው ዜና ምን ይላል አትሉም? ቀደም ብሎ እንደተጠበቀው የአንጌላ ሜርከል ፓርቲ በምርጫው ሲያሸነፍ፣ ተፎካካሪው ሲዲዩ ፓርቲ 42 በመቶ ድምፅ በማግኘት ተሸንፏል ይላል ዜናው። ትክክል ይመስላል። ከሃምሳ በመቶ በታች ድምፅ ያገኘ ፓርቲ በተሸናፊነት መጠቀሱ አይገርምም። ቀሽሙ ስህተት ምን መሰላችሁ? ሲዲዩ የአንጌላ ሜርከል ተፎካካሪ ፓርቲ አይደለም፤ አንጌላ ሜርከል የሚመሩት ፓርቲ ነው። አሸነፈ እንጂ አልተሸነፈም፡፡ በኢቴቪ አዘጋገብ…”አቶ ኃይለማርያም የሚመሩት ፓርቲ በምርጫው ሲያሸንፍ ኢህአዴግ ተሸንፏል” እንደማለት እኮ ነው፡፡
የአንጌላ ሜርከል ፓርቲ (ሲዲዩ) ከነአጋሩ 42 በመቶ ድምፅ በማግኘቱ ነው፣ በአብላጫ ድምፅ አሸናፊ ለመሆን የቻለው። ዋናው ተፎካካሪ ፓርቲ (ኤስፒዲ) ደግሞ 25 በመቶ ገደማ ድምፅ አግኝቷል። 9 በመቶ፣ 8 በመቶ፣ እና ወደዚያው ገደማ ድምፅ ያገኙ ሌሎች ፓርቲዎችም አሉ። የአንጌላ ሜርከል ፓርቲ በአሸናፊነት የሚጠቀሰው፣ መንግስት ለመመስረት ከአንድ ፓርቲ ጋር ጥምረት መፍጠር ስለሚበቃው ነው። ተቀናቃኛቸው ኤስፒዲ ፓርቲ ግን፣ ከአራት ወይም ከአምስት ፓርቲዎች ጋር ጥምረት ካልፈጠረ፣ መንግስት ለመመስረት የሚያስችል አቅም አይኖረውም። እንግዲህ፣ የአንጌላ ሜርከል ፓርቲ በአብላጫ ድምፅ ሲያሸንፍ፣ ተፎካካሪው ሲዲዩ ፓርቲ 42 በመቶ ድምፅ ተሸንፏል የሚለው ዜና፤ በቀሽም ስህተት ሳቢያ ምን ያህል መረጃውን ሁሉ እንዳዛባው አያችሁ?
የአካባቢው ጥበቃ ሟርትና የዩኤን እዬዬ
በዚሁ ወር የተሰራጨ ሌላ ዜናም ልጥቀስላችሁ። “ከአካባቢ ጥበቃ” ጋር. በተያያዘና የአለም የሙቀት መጠንን በተመለከተ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስር፣ በየጊዜው ጠቅላላ “ሳይንሳዊ” ሪፖርት አዘጋጅቶ የሚያቀርብ ድርጅት አለ። በእርግጥ፣ የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ፣ በአመዛኙ “ከፖለቲካ እምነት” ጋር እንጂ፣ “ከሳይንሳዊ እውነታ” ጋር ብዙም አይዛመድም። ምን ለማለት እንደፈለግኩ ልንገራችሁ፡፡ “ሟርት” ማስተጋባት የማይሰለቻቸው የአካባቢ ጥበቃ ቡድኖች፤ ከሰላሳ አመት በፊት፣ “አለም በቅዝቃዜ ደንዝዛ በበረዶ ትሸፈናለች” በማለት ነበር ዘመቻ የሚያካሂዱት። ነገር ግን፣ የተነበዩለት “Global Cooling” በእውን አልተከሰተም። ግን ሌላ ትንበያ አላጡም። አለምን የሚያሰጋት፣ የበረዶ ቅዝቃዜ ሳይሆን፣ የዓለም ግለት “Global Warming” ነው ተባለ።

በእርግጥም፣ የአለም አማካይ ሙቀት፣ በመቶ አመታት ውስጥ በግማሽ ሴንቲግሬድ እንደጨመረ የተለያዩ የሳይንስ ምርምሮች ይመሰክራሉ። የአካባቢ ጥበቃ ቡድኖች ግን፣ ሳይንሳዊ ግኝት ላይ ሳይሆን፣ ከሟርት ያልተለየ ትንበያ ላይ ነው የሚያተኩሩት። በመቶ አመታት ውስጥ የአለም ሙቀት እስከ 5 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ይጨምራል በማለት አለምን የሚያስበረግግ “እዬዬ” ማስተጋባት፣ የቡድኖቹ የእለት ተእለት ስራ ነው። “እዬዬ”ውን በአስለቃሽነት እያስተባበረ የሚመራው ደግሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ነው - በየጊዜው በሚያዘጋጃቸው ጠቅላላ “ሳይንሳዊ” ሪፖርቶች።
የ“ሟርት” ነገር! ዩኤን እና የአካባቢ ጥበቃ ቡድኖች የተነበዩት ያህል የአለም ሙቀት አልጨመረም። በተለይ ባለፉት 20 አመታት፣ ከቁጥር የሚገባ ጭማሪ አላሳየም። ለዚህም ይመስላል፣ “የአለም ግለት” ከሚለው ስያሜ ይልቅ፣ በደፈናው “የአየር ንብረት ለውጥ” “Climate Change” የሚል ፈሊጥ ያመጡት። አምስተኛው ጠቅላላ “ሳይንሳዊ” ሪፖርት በቅርቡ የተሰራጨውም፣ በዚህ ድፍን ስያሜ ነው። ከቀድሞዎቹ ሪፖርቶች ብዙም የተለየ አይደለም፤ ትንሽ ለየት የሚለው፣ ባለፉት 20 አመታት የአለም ሙቀት እንደተጠበቀው አለመጨመሩን ለመካድ አለመድፈሩ ብቻ ነው። ከተጠበቀውና ከተተነበየው ጋር ሲነፃፀር፣ ከሶስት እጥፍ በታች ነው የሙቀት ለውጥ የተመዘገበው። ከሪፖርቱ ጋር በተያያዘ የተሰራጩ ዓለማቀፍ ዘገባዎችም፣ ይህንን አወዛጋቢ መረጃ በስፋት ጠቅሰውታል። የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሬቴድ) ግን፣ ጨርሶ ጉዳዩን አላነሳም። እናስ ምን ዘገበ? በተባበሩት መንግስታት አስተባባሪነት የሚሰራጨው ሪፖርት ውስጥ የተካተቱ የዓለም ግለትን የሚመለከቱና ዓለምን የሚያስበረግጉ ወሬዎችን ነዋ። ግን ምን ዋጋ አለው? የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እነዚህን ጎደሎ መረጃዎችንም ቢሆን በትክክል አልዘገባቸውም። እንዴት በሉ።
እንደሚታወቀው፣ በዩኤን እና በአካባቢ ጥበቃ ቡድኖች ድምዳሜ መሰረት፣ የአለም ግለት መንስኤ የሰዎች አኗኗር ነው። በተለይም በነዳጅ አጠቃቀም የሚፈጠረው ካርቦንዳይኦክሳይድ፣ ለአለም ግለት ዋነኛ መንስኤ ነው ይላሉ።

ምን ያህል እርግጠኞች ናችሁ ተብለው ሲጠየቁ፣ በአብዛኛው እርግጠኛ ሆነናል የሚል ምላሽ ነበር የሚሰጡት። ከቅርብ አመታት ወዲህ ደግሞ፣ “በጣም እርግጠኞች ነን፤ 90 በመቶ እርግጠኞች ነን” ወደ ማለት ደረሱ። በዘንድሮው ሪፖርት ደግሞ፣ “እጅግ በጣም እርግጠኞች ነን” ወደ የሚል ደረጃ ተሸጋግረዋል። የአለም ግለት በሰዎች አኗኗር ሰበብ እንደተከሰተ 95 በመቶ እርግጠኞች ሆነናል ይላል ሪፖርቱ። የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ግን፤ የአለም ግለት 95 በመቶ ያህሉ በሰዎች አኗኗር ሰበብ የሚከሰት ነው ብሎ ዘገበው። ምን እንደማለት መሰላችሁ? “የእገሌ ቡድን የተሸነፈው በተጨዋቾች አሰላለፍ ሳቢያ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ፤ 95 በመቶ እርግጠኛ ነኝ” ሲባልና፣ “የእገሌ ቡድን ለሽንፈት የተዳረገበት ምክንያት 95 በመቶ ያህሉ ከተጫዋቾች አሰላለፍ የመነጨ ነው” ሲባል ልዩነት የለውም?
ምናልባት ይህንን ልዩነት ማወቅ ይከብድ ይሆናል። አንዳንዴ ግን፣ የኢቴቪ ቀሽም ስህተቶች የሚመነጩት ካለማወቅ ብቻ አይደለም። ይህችን ቅንጣት ስህተት ተመልከቱ። ጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ፣ በኒውዮርክ ከተለያዩ ባለሃብቶች ጋር ባደረጉት ውይይት ስለኢትዮጵያ ኢኮኖሚና ስለኢንቨስትመንት እድሎች ገለፃ አድርገው አልነበር? በውይይቱ የተሳተፉ አንድ ባለሃብት፣ ለኢቴቪ አስተያየታቸውን ሲሰጡ፣ በገለፃው “intrigued” ሆኛለሁ አሉ - በእንግሊዝኛ። በኢቲቪ ሲተረጎም፣ “በገለፃው ተደስቻለሁ” ተብሎ ቀረበ። የባለሃብቱ አነጋገር ግን፣ “ገለፃው ትኩረቴን ስቧል”፤ “ገለፃው፣ የማወቅ ጉጉት አሳድሮብኛል” ከሚል ሃሳብ ጋር የጥርጣሬ ስሜትንም ጭምር የሚያስተላልፍ ነው። “ገለፃው ጥያቄ አጭሮብኛል” እንደማለት አይነት። ይሄ ነው፤ “በገለፃው ተደስቻለሁ” ተብሎ የተተረጎመው። የአላዋቂነት ስህተት ነው ወይስ ከፕሮፓጋንዳ ፍቅር የሚመነጭ ስህተት? የሆነ ሆኖ ስህተት ነው።
እንግዲህ፣ በጥቂት የዜና ስርጭቶች ውስጥ የታዘብኳቸው ቀሽም ስህተቶችን ነው ያካፈልኳቸው፡፡ ታዲያ እነዚህን ስህተቶች ማስተካከል ለኢቴቪ ይከብደዋል? ላይ ላዩን ስታዩት ከባድ አይመስልም። ነገር ግን፣ ወጣትና ጎበዝ ጋዜጠኞች የሚያጋጥሟቸው ቀሽም ስህተቶችን ማስተካከል የሚቻለው፣ ሙያውንና ሙያተኛውን የሚያበለፅግ አሰራር በማዳበር ነው። ይሄ ደግሞ ከባድ ነው። የረዥም ጊዜ ጥረትንና ፅናትን ይጠይቃል። ታዲያ ይሄ ነገር ኢቴቪ ውስጥ ይኖራል ተብሎ ይታሰባል? አይመስለኝም። የመንግስት ድርጅት ነዋ፡፡
ሌላውን ተዉት። ኢቴቪ የዜና እና የዘፈን ክሊፖችን ሳይቀር፣ ምስሎችንና ቪዲዮዎችን እየደፈጠጠ ማሰራጨት ካዘወተረ ስንት ወሩ ነው? የተለያዩ የቪዲዮ ፎርማቶች፣ በቁመታቸውና በወርዳቸው እንደሚለያዩ ማወቅኮ፣ የቴሌቪዥንና የቪዲዮ ‘ሀሁ’ ነው። በአንዱ ፎርማት የተዘጋጀ ቪዲዮ፣ በሌላ ፎርማት ከተሰራጨ… ወይ የተደፈጠጠ ድንክ ይሆናል ወይም ወደ ላይ የተመዘዘ ሞላላ ሆኖ ይታያል። ያው እንዳያችሁት የስንቱ ሰው መልክና ቁመና፣ በኢቴቪ ሲደፈጠጥ ከርሟል። አሁን፣ ቪዲዮዎችን በትክክለኛ ፎርማት ማሰራጨት ትልቅ ስራ ሆኖ ነው? ግን ለወራት አልተስተካከለም። ይህችን ለማስተካከል የሚበቃ የአፍታ ጥረትና ፅናት ካልተገኘ፤ ሌሎችን ስህተቶች ለማረም የረዥም ጊዜ ጥረትና ፅናት ከወዴት ይመጣል?

 

ከመስከረም እስከ ህዳር የወባ ወቅት ስለሆነ ጥንቃቄ አድርጉ!
በወባ በሽታ ከሚሞቱት ውስጥ 90 በመቶው አፍሪካውያን ናቸው!
በአገራችን 52 ሚ. ህዝብ የሚኖረው በወባማ አካባቢዎች ነው!

ዮናስ አብይ መንግስታዊ ባልሆነ ድርጅት ውስጥ ተቀጥሮ መስራት ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል፡፡ የስራው ባህርይው መስክ የሚያስወጣ ስለሆነ፣ አብዛኛውን ጊዜውን የሚያሳልፈው ከቦታ ቦታ እየተዘዋወረ ነው፡፡ ለስራ የሚንቀሳቀስባቸው የአገሪቱ ድንበር አካባቢዎች ቆላማ በመሆናቸው በወባ የመያዝ ዕድል ገጥሞታል፡፡ በአንድ ወቅት ለሞት አድርሳው የነበረችው የወባ በሽታው፣ በጊዜው እየተቀሰቀሰች ታሰቃየዋለች፡፡ ከአርተም በተባለው የወባ በሽታ መድሃኒት ከበሽታው እፎይታን ቢያገኝም ከበሽታው ጨርሶ ሊፈወስ ባለመቻሉ በየጊዜው መሰቃየቱ አልቀረም፡፡ “በሽታው ሊነሳብኝ ሲል ይታወቀኛል፤ ራስ ምታቱ፣ ብርድ ብርድ የማለት ስሜቱ ከፍተኛ ነው፡፡ የምግብ ፍላጐቴም ጨርሶ ይዘጋል፡፡ ከአዲስ አበባ ክልል ሳልወጣ ወባዬ ተነስታብኝ በጣም ታምሜ አውቃለሁ፡፡ በሽታው አንዴ ውስጥሽ ከገባ በየምክንያቱ እየተነሳ ያሰቃይሻል፡፡ ለስራ በምዘዋወርባቸው አካባቢዎች በበሽታው ተይዘው የሚሰቃዩትን ህፃናት ስመለከት በጣም አዝናለሁ፡፡ እኔ በዚህ አቅሜና ጥንካሬዬ ያልቻልኩትን ስቃይ እነሱ እንዴት እንደቻሉት ለማሰብ ከባድ ነው፡፡” ይላል - በሽታው ምን ያህል እንደሚያሰቃይ ሲገልጽ፡፡
ዮናስ፤ በወባ በሽታ ሳቢያ ለዓመታት መሰቃየቱንና መቸገሩንም ይናገራል፡፡ ሁልጊዜም የስጋትና የጭንቀት ህይወትን እንደሚያሳልፍ፣ በሽታው ያሳደረበት ተጽእኖም ቀላል እንዳልሆነ ይገልፃል፡፡ በአገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ቁጥር አንድ የሰው ልጆች ገዳይ በሽታ እንደሆነ የሚታወቀው የወባ በሽታ፤ በወረርሽኝ መልክ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ለብዙሃን ሞት ምክንያት ሆኗል፡፡
በሽታው በአገር ኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ ኑሮና በፖለቲካው ላይ የሚያስከትለው ቀውስ በቀላሉ የሚገመት ባለመሆኑም አገሮች ሁሉ ወባን ከአገራቸው ለማጥፋት ደፋ ቀና ማለቱን ተያይዘውታል፡፡ በአገራችንም በጤናው ዘርፍ ትኩረት ከተሰጠባቸው አምስቱ ዋና ዋና የጤና ችግሮች ቀዳሚው ወባን መከላከልና መቆጣጠር መሆኑ ይታወቃል፡፡ መንግስት በወባ መከላከል ላይ ፖሊሲ ነድፎ እያከናወነ ባለው ተግባር ውጤታማ እርምጃዎችን በመውሰድ፣ የወባ በሽታ ስርጭቱ በተሻለ ደረጃ ላይ እንዲገኝ ማድረግ መቻሉን የጤና ጥበቃ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
በዓለማችን በየዓመቱ ከ250 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወባ በሽታ የሚጠቁ ሲሆን ከእነዚህ የበሽታው ተጠቂዎች መካከል 10 በመቶ ያህሉ በዚሁ በሽታ ሳቢያ ህይወታቸውን ያጣሉ። በበሽታው ህይወታቸውን ከሚያጡት ሰዎች መካከልም 90 በመቶ የሚሆኑት የሚኖሩት በአፍሪካ ውስጥ ነው፡፡ ከአፍሪካ አገራት መካከል በወባ ስርጭት የሚታወቁት አገራት ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ታንዛንያና ኬንያ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ በሽታው በአብዛኛው በህፃናት፣ በአረጋዊያንና በነፍሰጡር እናቶች ላይ በይበልጥ ይታያል፡፡ ቀደም ሲል ንዳድ በሚል መጠሪያ ስም ይታወቅ የነበረው የወባ በሽታ፤ በአገራችን ከባህር ወለል በታች በ2000 ሜትር ርቀት ላይ በሚገኙ አካባቢዎች ላይ በስፋት ይከሰታል፡፡ ለወባ ትንኝ መራቢያነት ምቹ ከሆኑ ነገሮች መካከል የታቆረ ውሃ፣ ሙቀትና አየር ዋነኞቹ ሲሆኑ በአገራችን ያሉ 75 በመቶ ያህሉ አካባቢዎች ለወባ ትንኝ መራቢያነት ምቹ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ አስደንጋጩ እውነታ በእነዚህ ወባማ አካባቢዎች ከ52 ሚሊዮን በላይ ሰዎች መኖራቸው ነው፡፡
በሽታው በአብዛኛው ከመስከረም እስከ ህዳር ወራት ባሉት ጊዜያት የሚሰራጭ ሲሆን በአንዳንድ የበልግ ዝናብ በስፋት በሚታይባቸው አካባቢዎች፣ ከሚያዝያ እስከ ግንቦት ባሉት ጊዜያትም ይሰራጫል። በሽታው በሴቷ የወባ ትንኝ ንክሻ አማካኝነት እንደሚተላለፍ የሚታወቅ ሲሆን የበሽታው ምልክት የሚታየው ይህችው የወባ አማጭ ተህዋሲያንን የተሸከመችው ትንኝ ከተናከሰች ከ7ኛው ቀን እስከ አስራ አራተኛው ቀን ድረስ ነው፡፡ የበሽታው ምልክቶችም ከፍተኛ ራስ ምታት፣ ትኩሳት፣ ብርድ ብርድ የማለት ስሜትና ማስመለስ እንዲሁም የምግብ ፍላጐት ማጣት ናቸው፡፡ የበሽታው አምጪ ተህዋሲያን በተለያዩ የህመም ማስታገሻ መድሃኒቶች ሊሸፈኑና ህመምተኛው በሽታው ሳይታወቅለት ለቀናት ሊያሰቃይ ይችላል፡፡
በአገራችን የወጣ በሽታን ከሚያሰራጩት ተህዋሲያን መካከል ፕላስሞዲየም ፋልስፋርሞና ፓላስቲሞዲየም ቫይቫክስ የተባሉ ዋነኞቹ ሲሆኑ ለተዋህሲያኑ መራባት እጅግ አመቺ የሆኑት ወቅቶች የክረምቱ ወራት ተጠናቆ የበጋው ወራት የሚጀምርባቸው ከመስከረም እስከ ህዳር ያሉት ጊዜያት ናቸው፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት ዲዲቲ የወባ በሽታን ለመከላከል በመላው አገሪቱ በስፋት ጥቅም ላይ ይውል ነበር፡፡ የዚህ መድሃኒት ፍቱንነት እየተዳከመ በመምጣቱ ከአገልግሎት ውጭ እንዲሆን እየተደረገ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት ከዚህ መድሃኒት በተሻለ የወባ ትንኞች ለመግደል ይረዳል የተባለውና ዴላሜትሪን በሚል መጠሪያ የሚታወቀው መድሃኒት በጥቅም ላይ ውሏል፡፡ በወባማ የአገሪቱ አካባቢዎች በፀረ ወባ ትንኝ መድሃኒት ርጭት ባለሙያዎች አማካኝነት በተለይ በወባማ ጊዜያት የመድሃኒት ስርጭቱ የሚከናወን ሲሆን ህብረተሰቡም ኬሚካል የተነከሩ አጎበሮችን እንዲጠቀም የማስተማሩና አቅርቦቱን የማስፋፋቱ እንዲሁም ውሃ ያቆሩ አካባቢዎች የማደራረቁና የማጥፋቱ ተግባር በስፋት እየተሰራበት ይገኛል፡፡
መንግስት በጤናው ዘርፍ በምዕተ ዓመቱ አሳካቸዋለሁ ብሎ ከተነሳባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የሆነው ወባን የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ውጤታማ እየሆነ መምጣቱንና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የወባ ስርጭት እየቀነሰ መሆኑን ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ይሁን እንጂ የአለም ጤና ድርጅት በበኩሉ፤ አገሪቱ የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በቂ ጥረት አለማድረጓንና አሁንም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች በወባ በሽታ እየተያዙ እንደሚሞቱ ጠቁሟል፡፡
የዓለም ሙቀት መጨመርና አካባቢያዊ ለውጡ የበሽታው ስርጭት እንዲጨምር አስተዋፅኦ ማድረጉን የገለፀው የዓለም ጤና ድርጅት፤ ቀደም ሲል በሽታው ታይቶባቸው በማያውቁ አካባቢዎች ሳይቀር በሽታው መታየቱንና በአንዳንድ ወባ የጠፋባቸው ቦታዎችም ተመልሶ እየተከሰተ መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ በቅርቡ ባወጣው መረጃ፤ በአገሪቱ በየዓመቱ በወባ የተያዙ 3ሚ.149ሺ 741 በሽተኞች እንደሚመዘገቡ አመልክቷል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በአገሪቱ ወባማ ባልሆኑ አካባቢዎችም የወባ ስርጭቱ እየተስፋፋ መሆኑን የጠቆመው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና አጠባበቅ ትምህርት ቤት የተደረገ ጥናት፤ ለዚህም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች መስፋፋት፣ ሰፈራ፣ የህዝብ ቁጥር መጨመር፣ ፍልሰትና የአካባቢ መራቆት ዋነኞቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ጠቅሷል። በቆቃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ዙሪያ በተካሄደ ጥናትም፣ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ በግድቡ ዙሪያ የሚኖሩ ከ19 ሺህ 350 በላይ አርሶ አደሮች የወባ ተጠቂ እንደሆኑ መገለፁን ጠቁሟል-የጤና አጠባበቅ ትምህርት ቤቱ ጥናት፡፡

Published in ዋናው ጤና

አንድ እሥር ቤት ውስጥ የሆነውን ነገር ቆይተው ሲያስቡት ተረት እንጂ በዕውነት በታሪክ የተከሰተ አይመስልም፡፡
የእሥር ቤቱ ክፍል አራት በአራት ነው ፡፡ ከሃምሣ እስከ ስልሣ የሚሆኑ እሥረኞች ታጭቀውበታል፡፡ የሚተኙት እንደጨፈቃ ተጨፍቀው ነው፡፡ ጠዋት ሲነጋ ቀኑን ለመግፋት ዳማ፣ ዶሚኖ፣ ቼዝ እና እዚያው በተሠራ ወረቀት ካርታ ይጫወታሉ፡፡
የእሥረኛው ዓይነት እንደየጉዳዩ የተለያየ ነው፡፡ በፖለቲካ የታሠረ አለ፡፡ በኢኮኖሚ (ገንዘብ ነክ) ጉዳይ የሚመጣ አለ - ደረቅ ወንጀል ይሉታል፡፡ በእግሩ ድንበር አልፎ ለመሄድ ሲሞክር ተይዞ የሚታሠር አለ “እግር እላፊ” ይሉታል በእሥረኞቹ አጠራር፡፡ የዘማች ሚስት በማማገጥ የሚታሠር አለ “ጭን እላፊ” ይሉታል፡፡ በስርቆሽ የሚታሠር አለ “እጅ - እላፊ” ይሉታል፡፡ በዘለፋ፣ መንግሥት (መሪ) በመሰደብ የሚታሠር አለ - “አፍ -እላፊ” ይሉታል፡፡
እሥር ቤቱ ክፍል አሁን ዳማ የማጫወቱት ሁለት ሰዎች፤ አዕምሮአቸውን ነካ የሚያደርጋቸው ናቸው፡፡ በአፍ - እላፊ ነው የታሠሩት፡፡ ዳማ እየተጫወቱ ይወያያሉ፡፡
“ይሄ መንግሥት ዕብድ ማሠሩ አይገርምህም?” ይላል አንደኛው፡፡
“አሣሪው ይሁን ታሣሪው ዕብዱ? ገና አልለየምኮ” ይላል ሁለተኛው፡፡
“እኔ መንግሥት ይመስለኛል ዕብድ”
“እኔ ግን እኛ ዕብድነታችንን ቢያዘልቅልን ከመንግሥት እንሻላለን እላለሁ”
“ይልቅ ዳማችንን እንጫወት፡፡ ለሁላችንም የሚሻለን፤ ህዝብ ቢያብድ ነበር”
“ለምን?”
“አለዛ ድንዝዝ ፍዝዝ ብሎ ይቀራላ!”
“በል እሺ ዳማችንን እንጫወት?”
ዳማቸውን መጫወታቸውን ይቀጥላሉ፡፡
አንደኛው የሌላኛውን ንጉሥ፤ በወታደርም፣ በንጉሥም የሚበላት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡
ሁለተኛው - “በንጉሥ ትገደዳለህ፡፡ ንጉሤን በንጉሥ ነው እንጂ በወታደር አትበላኝም” ይላል፡፡
አንደኛው - “በየትኛውም ብበላህ ጨዋታው ያልቃል፡፡ በፈለኩት እበላለሁ”
ሁለተኛው - “በጭራሽ! በንጉሥ ትገደዳለህ”
አንደኛው - “እኔ እምልህ፤ አንዴ ሞት ከተፈረደብህ በቺቺ ግደሉኝ በክላሽ ግደሉኝ እያልክ ምን ያጨቃጭቅሃል?” አለው፡፡
* * *
በትንሹም በትልቁም ነገር ከማበድ ይሰውረን፡፡ የመሞቻ መሣሪያ ከማማረጥ ያድነን፡፡ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ እንከኖቻችን ጥቅል ውጤት ማስጨነቁና ማሳሰቡ የሀገርና የህዝብ ስሜት ላለው ሁሉ አይቀሬ ነው፡፡ በተለይም ዱሮ የእጅ - እላፊ ይባል የነበረው የምዝበራና አገርን የማራቆት ተግባር፣ (ዛሬ ሙስና የተባለውን)፤ “ባንዱ ያለማ ባንዱ ያደለማ” ሆኗል፡፡ አገር ትልቅ ለውጥ ላይ ናት፤ ከፍተኛ የትራንስፎርሜሽን ሂደት ላይ ነን እየተባለ፤ በጐን የዝርፊያ የኮንትሮባንድ እና “በአንድ ጀንበር ፎቅ ሠርቼ ልደር” ዓይነት ዘመናዊ ምዝበራ ይታያል፡፡ “በአንዴ ዘጋ/ዘጋች” ዛሬ የተለመደ ቋንቋ ነው፡፡ እንደነናይጄሪያና እንደነናይሮቢ (“ናይሮበሪ” እንደተባለው) ዐይን - ያወጣ የቀን ተቀን ዘረፋ የሚመጣው ከላይ እስከታች እየተወሳሰበ ያለው ሙስና ፍፁም ወደፈጠጠ ደረጃ ሲደርስ ነው፡፡ “ልጄን የእንቁላሉ ዕለት ቆንጥጬው ቢሆን በሬ ሲሰርቅ አይያዝም ነበር” አለች እንደሚባለው ነው፡፡
አንድም ሙስናው በየአቅጣጫው መሆኑ፤ አንድም ደግሞ ቢሮክራሲያዊ መጠቅለያ መኖሩ እጅግ ውስብስብ ያደርገዋል፡፡ (ዱሮ “ቢሮክራሲያዊ ካፒታሊዝም ይውደም” የሚል መፈክር ነበር፤ ነብሱን ይማረው!) በዚህ ላይ የግለሰቦች አሻጥር ሲጨመርበት፣ ከቁጥጥር ውጪ ወደሆነ ደረጃ ይሸጋገራል፡፡ የመሬት አሰቃቂ አወሳሰድ፣ ከፍተኛ የኮሚሽንና የድለላ ሥራ፣ አደገኛ ወገናዊ አሠራር…በአስደንጋጭ የድህነት መቀመቅ ውስጥ ለገባች አገር ከምትሸከመው በላይ ትከሻ አጉብጥ ሸክም ይሆንባታል፡፡ የባሰ ዘግናኝ የሚሆነው ደግሞ ከዕለት ወደ ዕለት በምዝበራ ምክንያት መታሰር ራሱ እየተለመደና ቀላል እየመሰለ መምጣቱ ነው፡፡ “እገሌ ታሠረኮ” ሲባል፤
“ተወው በልቷል - የሚበቃውን ቀለብ አከማችቷል”
ማለት እንደሰላምታ የሚነገር መሆኑ አሳዛኝ ነው፡፡
ዱሮ “በሥራው አጋጣሚ በእጁ የገባውን የመንግሥት ገንዘብ ለግል ጥቅሙ በማዋሉ” የሚለው ሐረግ ነበር ሬዲዮንና ቴሌቪዥን ያጣበበው፡፡ ዛሬ ዳር እስከዳር በየሰው አፍ የሚወራ ነገር ሆኗል፡፡ ዝርፊያው ዓይነት በዓይነት ሆኗል፡፡ ተወርቶም በቀላሉ ይረሳል፡፡ በተለይ ለህብረተሰብ ቀጥተኛ መጥፊያ የሚሆኑ እንደመድሃኒት ያሉ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ባመቸው መንገድ ሁሉ ተበርዘው ከተባዙ፣ ምን ያህል አሰቃቂ የሆነ ዕልቂት እንደሚያስከትሉ መገመት አያዳግትም፡፡ የሚያስገኙት ገንዘብ የትየለሌ፣ የሚፈጁት ህዝብ የትየለሌ!!
ማናቸውንም የጥፋት ድርጊት የሚፈጽሙ ወገኖች ለሀገር እንደቆሙ፤ የህዝብ ልጆች እንደሆኑ አድርገው መጮሃቸውና ሀቀኛ መምሰላቸው፤ ሌላው እንዳይናገር በር ይዘጋል፡፡ They shout at most against the vices they themselves are guilty of እንደሚሉት ነው ፈረንጆቹ - ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮህ እንደማለት ነው፡፡ ጩኸቱ በቅጡ ለገባው አገር - ወዳድ ሰው ግን፤ “ቤቱን አቃጥሎ እንዴት ብሩህ ቀን እንደሆነ ተመልከቱ” አለ እንደተባለው ነው፡፡ ልዩነቱ ያኛው ለግሉ እየተጠቀመ፤ ይሄኛው የገዛ ንብረቱን ጭምር እያወደመ የሚጃጃል መሆኑ ነው፡፡ ሁለቱንም መዋጋት ተገቢ ነው!

Published in ርዕሰ አንቀፅ

በአቶ ገ/ዋህድ ቤት ሁለት ክላሽን ጨምሮ 10 የጦር መሣሪያዎች ተገኝተዋል
በሚሊዮን የሚቆጠር ግብር እስከዛሬ አልተሰበሰበም
ከአስር በላይ ተከሳሾች በቁጥጥር ሥር አልዋሉም

የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ መላኩ ፋንታ እና ምክትላቸው አቶ ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ጨምሮ ሌሎች የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሃላፊዎች ከወርሃዊ ገቢያቸው በላይ በሚሊዮን የሚቆጠር ምንጩ ያልታወቀ ሃብትና ንብረት ማፍራታቸውን የፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግ ባቀረበው ክስ አመለከተ፡፡
በቡድን እና በተናጥል የተለያዩ ክሶች የቀረቡባቸው አቶ መላኩ ፈንታ፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 164,228,68 ብር እንዲሁም በመኖሪያ ቤታቸው 12,271 ብር፣ በድምሩ 176,499.68 ብር በጥሬ ገንዘብ ይዘው እንደተገኙ ተገልጿል፡፡ አቶ መላኩ በተጨማሪም በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ውስጥ 659 ኪ.ሜ ቦታ በ445,200 ብር መግዛታቸው፣ በቦታው ላይም 1,592,934.76 ብር በማውጣት ባለሁለት ፎቅ ግንባታ ማከናወናቸው እንዲሁም ለዚሁ ግንባታ ማስፈፀሚያ ከህብረት ባንክ ቦሌ መድሃኒዓለም ቅርንጫፍ 1,423,479.30 ብር መበደራቸው የተመለከተ ሲሆን በጠቅላላው ተከሳሹ በስልጣን ላይ በነበሩ ጊዜ ከወርሃዊ ገቢያቸው ጋር የማይመጣጠን 3,272,921.21 ንብረትና ገንዘብ አፍርተው በመገኘታቸው በፈፀሙት ምንጩ ያልታወቀ ሃብት ማፍራት የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡
አቶ መላኩ አንዲት ባለትዳር የነበረችን ግለሰብ ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀም ከቀድሞ ባለቤቷ ጋር ያቋቋመችው ኩባንያ እንዲከፍል የተወሰነበትን ግብር እንዲቀነስላቸው በማድረግ በፈጠሩት የፍቅር ግንኙነት፤ የ3 ልጆች እናት የነበረችን ሴት በትዳሯ ላይ እያለች ከማማገጣቸውም ባሻገር ከቀድሞ ባለቤቷ ጋር እንድትፋታና እሣቸውን እንድታገባ አድርገዋል የሚል ክስም ቀርቦባቸዋል፡፡
በተናጥልና ከሌሎች ጋር በጋራ ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም ገልገል እንዲሁም የመንግስትን ስራ በማያመች አኳኋን መምራት የሚሉ ክሶች በስፋት የቀረበባቸው የቀድሞው ምክትል ዳይሬክተር አቶ ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስ እና ባለቤታቸው ኮ/ል ሃይማኖት ተስፋዬ ላይ ነው፡፡ አቶ ገብረዋህድ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ከ1978 ዓ.ም ጀምሮ በቁጥጥር ስር እስከዋሉበት 2005 ዓ.ም ተቀጥረውና ተሾመው ሲሰሩ ከብር 247 እስከ ብር 5,719 ያልተጣራ ወርሃዊ ደመወዝ ይከፈላቸው የነበረ ሲሆን ባለቤታቸው ኮ/ል ሃይማኖት ደግሞ በአገር መከላከያ ሚኒስቴር ከ1989 እስከ 2000 ዓ.ም ተቀጥረው ሲሰሩ ከብር 790 እስከ ብር 2145 ያልተጣራ ወርሃዊ ደመወዝ ይከፈላቸው ነበረ፡፡ ሆኖም ተከሳሾቹ ያገኙት ከነበረው ደመወዝና ገቢ ጋር የማይመጣጠን ንብረትና ገንዘብ አፍርተው መገኘታቸው በክሱ ላይ ተመልክቷል፡፡
በአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ላይ እንደተመለከተው፤ ባልና ሚስቱ በራሳቸው እንዲሁም በልጆቻቸው ስም በወጋገን፣ በእናት፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ በዳሽን እና በአንበሳ ባንኮች የተለያዩ ቅርንጫፎች ከብር 387 እስከ ብር 203,424 ብር ድረስ አስቀምጠዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ተከሳሾቹ ለጊዜው ግምታቸው ያልታወቀ አውቶቡስ እና የንግድ መኪና በንብረትነት አፍርተው የተገኙ ሲሆን በአንደኛው ልጃቸው ስምም የ10ሺህ ብር አክሲዮን መግዛታቸው ተገልጿል። በብርበራ ወቅትም በመኖሪያ ቤታቸው 200ሺህ ብር፣ 26,300 ዶላር (ግማሽ ሚሊዮን ብር ገደማ)፣ 19,435 ዩሮ (ግማሽ ሚሊዮን ብር ገደማ)፣ 560 ፓውንድ እና 210 የታይላንድ ገንዘብ የተገኘ ሲሆን መቀሌ ከተማ ከሚገኝ መኖሪያ ቤት በተጨማሪ ግምቱ ብር 596,868.24 የሆነ 500 ካ.ሜ ቦታ ይዘው ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ ግለሰቦቹ የኑሮ ደረጃቸው አሁን ባሉበትም ሆነ አስቀድሞ በነበሩበት የመንግስት ስራ ከሚያገኙት ገቢ ጋር የማይመጣጠን ብር 1,451,941 (አንድ ሚሊዮን አራት መቶ ሃምሣ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ አርባ አንድ) እንዲሁም የተለያዩ የውጭ ሃገር ገንዘቦች ይዘው መገኘታቸው በክስ ማመልከቻው ተብራርቷል፡፡
በተናጥል በአቶ ገ/ዋህድ ላይ ብቻ በቀረበው 16ኛ ክስ ደግሞ የጦር መሣሪያ አያያዝና አጠቃቀም ደንብ ተከትለው ፍቃድ በማውጣት መሣሪያ መያዝ ሲገባቸው፣ በመኖሪያ ቤታቸው በተደረገ ብርበራ ሁለት ታጣፊ ክላሽ፣ አራት የተለያዩ የውግ ቁጥር ያላቸው ማካሮቭ ሽጉጦች፣ ሁለት የተለያዩ ቁጥር ያላቸው ኮልት ሽጉጦች እና አንድ ስታር ሽጉጥ በጠቅላላው አስር የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን ከተለያዩ ጥይቶች ጋር ይዘው በመገኘትም ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡
ሌላው ምንጩ ያልታወቀ ሃብት አፍርቶ በመገኘት ክስ የቀረበባቸው በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዋና አቃቤ ህግ የሆኑት አቶ ማርክነህ አለማየሁ ናቸው፡፡ ተከሳሹ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ከ1987 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 2005 ተቀጥረው ሲሰሩ ከብር 2535 እስከ ብር 10234 ያልተጣራ ወርሃዊ ደመወዝ እየተከፈላቸው የነበረ ቢሆንም በባለቤታቸው ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጦር ሃይሎች ቅርንጫፍ ከ900ሺ ብር በላይ ማስቀመጣቸው እንዲሁም “ውጭ ሀገር የሚገኙ ጓደኞቼ የላኩልኝ ገንዘብ ነው፤ አንቺ ጋ ይቀመጥልኝ” በማለት ሃዋሣ በምትገኘው እህታቸው የባንክ ሂሳብ በድምሩ ብር 1,900.000 እንዲቀመጥ ማድረጋቸው ተገልጿል፡፡
በተጨማሪም በእኚሁ እህታቸው ስም በሃዋሣ ከተማ 1,425,000 ብር የሚያወጣ መኖሪያ ቤት ማሠራታቸው ተመልክቷል፡፡ በተከሳሹ ቤት በተደረገ ብርበራም በኤግዚቢትነት ተመዝግቦ የሚገኝ 1, 388,899 ጥሬ ብር መገኘቱን የአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ያስረዳል፡፡ በአጠቃላይ አቶ ማርክነህ፤ ከወርሃዊ ደሞዛቸው ጋር የማይመጣጠን በድምሩ ብር 6,551,532.62 አካብተው የተገኙ ሲሆን ይህን በሙስና የተገኘ ንብረትና ሃብት ምንጩን ለመደበቅ በቤተሰባቸው ስም እና በመሬት ውስጥ እንዲቀበር በማድረግ በፈፀሙት በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብና ንብረት ህጋዊ አስመስሎ የማቅረብ ሙስና ወንጀልም ተከሰዋል፡፡
አምስት ኩባንያዎችን ጨምሮ ሃያ አራት ግለሰቦች በተከሰሱበት ሶስተኛው የክስ መዝገብ የተካተቱት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የጉምሩክ ስነስርዓት አፈፃፀም የስራ ሂደት መሪ የነበሩት አቶ አስመላሽ ወ/ማርያምም፤ በአጠቃላይ ከወርሃዊ ደሞዛቸው ጋር የሚይመጣጠን ግምቱ 4,459,179.5 የሆነ ከፍተኛ ንብረትና ገንዘብ በመያዝ የኑሮ ደረጃቸው የማይፈቅድላቸውን ሃብት አከማችተው መገኘታቸው ተመልክቷል፡፡ ተከሣሹ ከ1987 እስከ 2004 ዓ.ም በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ተቀጥረው ሲሰሩ በቆዩበት ወቅት ከብር 445 እስከ ብር 8,651 ወርሃዊ ደሞዝ ያገኙ የነበረ ሲሆን በመኖሪያ ቤታቸው በተደረገ ብርበራ ከተገኘው 1,947,676.10 ብር በተጨማሪ በተለያዩ ባንኮች እና አክሲዮኖች በስማቸው የተቀመጠ ብር 2,090,880.03 ተገኝቷል፡፡ በአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ላይ እንደተመለከተው፤ ተከሳሹ በራሳቸው እና በባለቤታቸው ስም በድምሩ የ30ሺህ ብር ቦንድ መግዛታቸው እንዲሁም ምንም ገቢ በሌላቸው ባለቤታቸው ስም በአዲስ አበባ ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 24 ቀበሌ 02/03 ውስጥ የተሠራ ግምቱ 200,000 ብር የሆነ ባለሁለት መኝታ ክፍል ኮንዶሚኒየም ቤት እንደገዙ ተገልጿል፡፡ አቶ አስመላሽ ገቢ በሌላቸው ባለቤታቸው ስም የ5ሺህ ብር ቦንድ ከመግዛታቸውም ባሻገር በተለያዩ ባንኮች 185ሺ641.19 ብር ማስቀመጣቸው ተመልክቷል፡፡
አቃቤ ህግ ካቀረባቸው የክስ አይነቶች ውስጥ “ጉቦ መቀበል” አንዱ ሲሆን በዚህም በሶስቱ የክስ መዝገቦች በሁለተኛነት የቀረቡት አቶ ገ/ዋህድ እና አቶ መርክነህ፤ ከአንድ ባለሃብት ከፍተኛ ጉቦ መቀበላቸው ተመልክቷል፡፡ ብስራት ኃ/የተ/የግ/ማህበር ያለቫት ደረሰኝ ግብይት ሲፈፅም ተደርሶበት ምርመራ ተጣርቶ ክስ ቀርቦበት ሳለ፣ ባለቤቱ በክርክር ላይ እያሉ አቶ ገ/ዋህድ ለኩባንያው ባለቤት አቶ ባህሩ አብርሃ በቀጥታ ስልክ በመደወል “አንተ ከማን ትበልጣለህ? ክስህን ወደ መደበኛ ፍ/ቤት አቅርበን ከፍተኛውን ቅጣት እንደምናስቀጣህ እወቅ” ብለው በማስፈራራት 250 ሺህ ብር ከተቀበሉ በኋላ፣ ባለሃብቱ አድርገውት የነበረውን ብራስሌት “የሱ አይነት ግዛልኝ” በማለት ግለሰቡ 30,000 ብር አውጥተው ብራስሌት እንዲገዙላቸው አድርገዋል፡፡ አቶ መርክነህም እንዲሁ 100ሺህ ብር ጉቦ ከተቀበሉ በኋላ፣ በባለሃብቱ ላይ የተመሰረተው ክስ ይግባኝ እንዳይጠየቅበት ማድረጋቸው ተመልክቷል፡፡
ጉቦ በመቀበል ከቀረቡ ክሶች መካከል በመዝገብ 3፣ በ26ኛ ክስነት በአቶ ገ/ዋህድ፣ በአቶ መርክነህ፣ ባልተያዘው የመስሪያ ቤቱ የግብር አወሣሠን ኦዲተር አቶ ዳንኤል ገ/ኪዳን እንዲሁም በአቃቤ ህግ አቶ አውግቸው ክብረት ላይ የቀረበው ይገኝበታል፡፡
ተከሣሾቹ ግብር ከፋይ የሆነውን ኦፊስ ቴክ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ባለቤት አቶ መሃመድ የሱፍን ድርጅቱ ኦዲት በሚደረግበት ወቅት በታክስ ማጭበርበር ወንጀል ከመከሠሡ በፊትና በኋላ በተለያየ ጊዜ በማግኘት ጉቦ እንደጠየቁ ተገልጿል፡፡ አቶ ዳንኤል በ2002 ዓ.ም ጥቅምት ወር ጀምሮ በተለያዩ ቀናት የግል ተበዳይን ተከታትሎ ካገኘው በኋላ “የላከኝ ገ/ዋህድ ነው፤ የደቡብ ፖሊስ ኮሚሽን አንተን እንድንቀጣህ ይፈልጋሉ፡፡ ስለዚህ ሁለት ሚሊየን ብር አምጣ፤ ካልሆነ ግብርም ይጨመርብሃል፤ አንተም ትታሠራለህ” በማለት የግል ተበዳይን ጉቦ እንዲሠጠው በአካልና በስልክ የጠየቀ ሲሆን ተበዳይ ገንዘቡን ለመስጠት ፍቃደኛ ሳይሆኑ ይቀራሉ፡፡ ባለሃብቱ ወደ ዱባይ በሄዱበት ወቅትም፣ ወደ ድርጅታቸው በመሄድ በአንድ ቀን ውስጥ ኦዲት አድርጐ አርባ ሁለት ሚሊዮን ብር ሂሣብ በማምጣት፣ በድርጅቱ ውስጥ በተለማማጅነት ትሠራ የነበረችን የመፈረም ስልጣን የሌላትን ግለሠብ አስፈራርቶ ማስፈረሙ ተመልክቷል፡፡ አቶ ገ/ዋህድ ደግሞ በ2003 ዓ.ም መጨረሻ ላይ እኚኑ የግል ተበዳይ “ግብር ዜሮ እንዲሆንልህና ክሡም እንዲቋረጥልህ ሁለት ሚሊዮን ብር ዱባይ በሚገኝ ሠው አማካኝነት አስገባ” ይሉታል፡፡ ይህንን ጉዳይ ለማጣራት የግል ተበዳይ ወደ አቶ ገ/ዋህድ ቢሮ ይሄዳሉ፡፡ ወደ ቢሮ እንዲዘልቁ ከፈቀዱላቸው በኋላ “አንተ አመፀኛ፤ ይህን የከተማ ጮሌነት ከአንተ በላይ አውቀዋለሁ፤ ኦሎምፒያ አካባቢ ከቀጠሩህ ሠዎች ጋር ጨርስ” በማለት የግል ተበዳይን በማስፈራራት፤ በቀጥታ ገንዘቡን እንዲከፍሉ ጠይቀዋል ይላል-የክስ ማመልከቻው፡፡ አቶ ማርክነህ እና አቶ አውግቸው ደግሞ የግል ተበዳይ ላይ ቀርቦ በሂደት ላይ እያለ፣ ቀጠሮ ለማራዘምና ለተከሣሹ ጊዜ ለመስጠት በሚል ጉቦ እንዲሠጣቸው በመደራደር ሁለት ቶሺባ ላፕቶፖች፣ ሁለት ሲዲኤምኤ እና 20ሺህ ብር ተቀብለው ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው ተመልክቷል፡፡
በሶስት የተለያዩ መዝገቦች በቀዳሚነት ክስ የተመሠረተባቸው የገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተርና ምክትላቸው፣ ከሌሎች በመዝገቦቹ ከተካተቱ ባለ ድርሻ አካላት ጋር በጣምራ እና በተናጥል የመንግስትን ስራ በማያመች አኳኋን መምራት የሚል ክስም በስፋት ቀርቦባቸዋል፡፡
ተከሣሾቹ በተለይ ከተለያዩ ታክስና ግብር ከፋዮች ጋር በመደራደር፣ ህገ ወጥ የቴክኒክ ኮሚቴ አቋቁመው፣ ህገወጥ ድርጊትን ማስፈፀም የሚያስችል መመሪያ በ2004 ዓ.ም ያወጡ ሲሆን ይህንኑ መመሪያ መሠረት በማድረግ፣ ሐዋስ አግሮ ቢዝነስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ለመንግስት ገቢ እንዲያደርግ ይጠበቅበት የነበረ ብር 22,379,145.28 በህገ ወጥ አሠራር መጠኑ ዝቅ እንዲል ከማስደረጋቸውም ባሻገር፣ ገንዘቡ እስከዛሬ እንዳይሠበሠብ አድርገዋል ተብሏል፡፡ በተመሣሣይ በሶስቱ መዝገቦች ሁለተኛ ተከሣሽ የሆኑት አቶ ገ/ዋህድ፤ ከሼባ ስቲል ሚልስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ላይ ይፈለግ የነበረ 104,487,978.40 ብር፣ ከኤጂኤች ኃ/የተ/የግ/ማህበር ላይ ይፈለግ የነበረ 6,809,763.42፣ ከሱሁራ 571 ኃ/የተ/የግ/ማህበር ይፈለግ የነበረ 91,747,355.68 ብር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን እንዳይሠበሠብ አድርገዋል ይላል ክሱ፡፡ በተጨማሪም አቶ ገ/ዋህድ ከሌሎች ጋር በጣምራ በቀረበባቸው ክስም ከ7 የተለያዩ የንግድ ድርጅቶችና ኩባንያዎች ይፈለግ የነበረ በሚሊዮን የሚቆጠር ገቢ የመንግስት ስራን በማያመች አኳኋን በመምራት እስካሁን እንዳይሠበሠብ ማድረጋቸው ተመልክቷል፡፡ ሌሎች የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የተለያዩ ሃላፊዎችም በተመሣሣይ መልኩ ግብርና ታክስ ከድርጅትና ኩባንያ ባለቤቶች ጋር በመመሣጠር እንዳይሠበሠብ ያደረጉ ሲሆን መንግስት ሊያገኘው የሚገባ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ አሣጥተዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡
በ3ኛው የክስ መዝገብ ከባለቤቶቻቸውና ስራ አስኪያጆቻቸው ጋር በመመሣጠር ኬኬ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ ጂ ኤች ሲሜክስ (ኢንተርኮንቲኔንታል) ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ ነፃ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ ጌታስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና ኮሜት ኃ/የተ/የግ/ማህበር በሚሊዮን የሚቆጠር ታክስና ግብር ባለመክፈል እንዲሁም በማጭበርበር ወንጀል ክስ የቀረበባቸው ሲሆን ስራ አስኪያጆቻቸውም ከየኩባንያዎቹ መንግስት የሚፈልገውን ገንዘብ ተከታትለው ባለመክፈል የጣምራ ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡
በሌላ በኩል ፍርድ ቤቱ ባለፈው ረቡዕ በዋለው ችሎት፣ በቀሪዎቹ 3 መዝገቦች የተከሠሡ አስራ ሶስት ግለሠቦችን ክስ በንባብ አሠምቷል፡፡ መዝገቦቹ በእነ ጌታሁን ቱጂ ሶስት ግለሠቦች፣ በእነ ዳዊት ኢትዮጵያ አምስት ግለሠቦች እንዲሁም በእነ ብርሃነ አርአያ አምስት ግለሠቦች ሲሆኑ በሁሉም ላይ ስልጣንን ያለ አግባብ የመጠቀም ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡
ተከሣሾቹ ስልጣናቸውን ተጠቅመው ከባለ ድርጅቶቹ ጋር በጥቅም በመተሣሠር ከንግድ ድርጅቶች እና ኩባንያዎች ይጠበቅ የነበረው የግብር መጠን እንዲቀነስና የንግድ ድርጅት ባለቤቶች በግብር ጉዳይ እንዳይከሠሡ በማድረጋቸው እንዲሁም ከኮንትሮባንድ ህገወጥ ንግድ ጋር በተያያዘ የጥቅም ተካፋይ ሆነው መገኘታቸውን የአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር አስረድቷል፡፡
አቃቤ ህግ በ6 መዝገቦች አደራጅቶ የመሠረታቸው ክሶች በአጠቃላይ 138 ሲሆኑ አቶ መላኩ ፈንታ እና አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ እያንዳንዳቸው በሶስት መዝገብ አንደኛ እና ሁለተኛ ተጠሪ በመሆን በርካታ ክስ በተናጥልና ከሌሎች ጋር በቡድን ቀርቦባቸዋል፡፡
በመዝገቦቹ ከተካተቱ ከ40 በላይ ተከሣሾች መካከል የጌታስ ሃላፊነቱ የተወሠነ የግል ማህበር ባለቤትን አቶ ጌቱ ገለቴ ጨምሮ ከ10 በላይ ተከሣሾች በቁጥጥር ስር ባለመዋላቸው በሌሉበት ጉዳያቸው ታይቷል፡፡
ለሶስት ተከታታይ ቀናት ስድስቱን መዝገቦች በንባብ ያሠማው ችሎቱ፤ የተከሣሽ ጠበቆች ከክሡ ጋር አብሮ ማስረጃዎች ተያይዘው አልቀረቡልንም በማለታቸው፣ ችሎቱ በቀጣይ ቀጠሮዎች አቃቤ ህግ ህጉ በሚያዘው መሠረት ማስረጃዎችን አያይዞ ለጠበቆችና ተከሣሾች እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሠጥቷል፡፡ በተጨማሪም ያልተያዙ ተከሣሾች በህግ ተይዘው እንዲቀርቡ ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡ ቀጣይ ሂደቶችን ለመመልከትም ሁሉንም መዝገቦች ለጥቅምት 19 እና 20, 2006 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡

በህገወጥ መንገድ ወደ ኬንያና ወደ ዚምባብዌ ድንበር ሲያቋርጡ ተይዘው የታሰሩ መቶ ያህል ኢትዮጵያውያን ክስ ይጠብቃቸዋል ተባለ፡፡
ሰሞኑን ወደ ናይሮቢ ሊገቡ ሲሉ በፖሊስ የተያዙት ሀምሳ ሶስት ወጣት ኢትዮጵያውያን ህጋዊ ፓስፖርት እንደሌላቸውና ከአማርኛ ውጪ በእንግሊዝኛ መግባባት እንደማይችሉ የሳምራ ፖሊስ ኮማንደር ኤል ሙታሚያ ተናግረዋል፡፡ ከስደተኞቹ ጋር፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር የሚያካሂዱ ደላሎች ናቸው የተባሉ ኬንያዊያንም ታስረዋል፡፡
በሌላ በኩል የዚምባቡዌን ድንበር አቋርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊሄዱ የነበሩ ሰላሳ ስምንት ኢትዮጵያውያን በሃገሪቱ ፖሊስ ተይዘዋል፡፡ ወጣት ስደተኞቹ ወደ ዙምባብዌ የገቡት በህገወጥ መንገድ ስለሆነ ክስ ይመሰረትባቸዋል ሲል ፖሊስ ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ በኬንያና በዙምባቡዌ ለታሰሩ ስደተኞች ከመንግስት እገዛ ይደረግላቸው እንደሆነ ከአዲስ አድማስ ተጠይቀው፣ “መንግስት ሁልጊዜም ዜጐቹን የመርዳት ፍላጐት አለው፤ በየአገሩ ያሉ ኤምባሲዎቻችንም በዚህ ፖሊሲ መሰረት እየሰሩ ነው” ብለዋል፡፡
በቅርቡ የወጣው የአለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት መረጃ እንደሚለው በየአመቱ ከሀያሺ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንና ሶማሊያዊያን በኬንያ በኩል ደቡብ አፍሪካ ይገባሉ፡፡

Published in ዜና

ሜጀር ጀነራል አደም መሀመድ የአየር ሀይል አዛዥ ሆነው መሾማቸውንና የአዛዥ ጄነራሎች ላይም የምደባ ለውጥ መደረጉን ምንጮቻችን አመለከቱ፡፡ በአየር ሀይል አዛዥ በነበሩት ሜጀር ጀነራል ሞላ ሀይለማርያም ምትክ የተሾሙት ሜጀር ጀነራል አደም የአየር ሀይል ፓይለት የነበሩና በሱዳን አቢዬ ግዛት የሠላም አስከባሪ ሀይል ምክትል አዛዥነት ያገለገሉ እንዲሁም የመከላከያ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ነበሩ፡፡
በሌሎች የመከላከያ የስራ ምድብ ቦታዎች ላይ የአዛዦች የምደባ ለውጥ መደረጉን የተናገሩት ምንጮች፣ አዲስ የሀላፊነት ምደባ ከተሠጣቸው ውስጥ ሌተናል ጀነራል ሠአረ መኮንን፣ ሌተናል ጀነራል አበባው፣ ሜጀር ጀነራል ዮሀንስ ወልደጊዮርጊስ፣ ሜጀር ጀነራል ገብራት አየለ እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
ባለፈው አመት እና ዘንድሮ ከ60 በላይ ለሚሆኑ መኮንኖች የጀኔራልነት ሹመትና እድገት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

Published in ዜና

“ሞያው የሚጠይቀውን መስዋዕትነት ለመክፈል ወስኜ ነው የምመጣው”
የአውራምባ ታይምስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ከሁለት አመታት የአሜሪካ የስደት ኑሮ በኋላ ጋዜጣውን እንደገና ለመጀመር ዛሬ ወደ አገሩ ይመለሳል፡፡
“ከሁለት አመታት በፊት ጋዜጣውን ዘግቼ ለመሰደድ የወሰንኩት በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በተከፈተብኝ ዘመቻ ለደህንነቴ በመስጋት ነው” የሚለው ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ፤ “ከምታገልለት ህዝብና ከመረጃ ርቄ የጋዜጠኝነት ስራ መስራቴ ውጤታማ እንደማያደርገኝ ስለተገነዘብኩ ወደ አገር ቤት ለመመለስ ወስኛለሁ” ብሏል፡፡
ትላንት ወደ ኢትዮጵያ ለመብረር አውሮፕላን ከመግባቱ አንድ ሠዓት በፊት ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ በስልክ በሰጠው ቃለ ምልልስ፤ “በአሜሪካ ለተሰጠኝ የፖለቲካ ጥገኝነት አመሰግናለሁ፤ ነገር ግን ሞያው የሚጠይቀውን መስዋዕትነት ለመጋፈጥ የፖለቲካ ጥገኝነት ፈቃድ አስረክቤ እየመጣሁ ነው›› ብሏል፡፡
ለመሰደድ መወሰኑ ስህተት እንደነበር ዳዊት ገልፆ፣ ምንም እንኳን ከፍተኛ ጫና ቢደርስብኝም ፈተናውን በአገር ውስጥ ሆኜ መጋፈጥና የሚጠይቀኝን ዋጋ መክፈል ይገባኝ ነበር ብሏል፡፡ በአሜሪካ ድረገጽ ከፍቼ መስራት ከጀመርኩ በኋላ በዚያው የሚገኙ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ግለሰቦች ከመንግስት ጋር ግንኙነት እንዳለኝ በማስመሰል ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ አድርገውብኛል የሚለው ዳዊት፣ ወደ አገር ቤት ለመመለስ የወሰንኩት ግን በዚህ ምክንያት አይደለም ብሏል፡፡
በጋዜጠኝነት ስራ ለመቀጠል ወደ አገር ቤት መመለስ፣ በአገሪቱ የፕሬስ ነፃነት ሁኔታ የተሻሻለ መሆኑን እንደማያሳይ የገለፀው ጋዜጠኛ ዳዊት፣ በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ ለመስራት እችላለሁ ብሎ እንደሚያምን ተናግሯል፡፡
ዳዊት በ1997 ዓ.ም አገር አቀፍ ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ፣ ከቅንጅት አመራሮችና ከሲቪል ማህበራት መሪዎች ጋር ለ2ዓመት ገደማ ታስሮ መፈታቱ ይታወሳል፡፡

Published in ዜና
Page 3 of 16