በረሃብ ደካክሞ ለ5ቀን ራስ ደስታ ሆስፒታል ህክምና ተደርጎለታል

ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ፒያሳ እምብርት ላይ በሚገኘው ዝነኛው ላሊበላ ወርቅ ቤት ውስጥ ለብዙዎች ትንግርት የሆነ ነገር ተከስቷል፡፡ ያውም በጠራራ ፀሃይ፡፡ ላሊበላ ወርቅ ቤት፤ በአካባቢው ከሚገኙ ሌሎች ወርቅ ቤቶች ለየት የሚያደርገው ለምሳ ከ7-9 ሰዓት መዘጋቱ ነው የሚሉት የወርቅ ቤቱ ባለቤት አቶ ኢዛና ካሣዬ፤ የዚያን ዕለት ግን ገበያ በመብዛቱ ለምሳ ሳይዘጋ እንደቀረ ይናገራሉ፡፡
የላሊበላ ወርቅ ቤት ትንግርት የተጀመረው ከጎኑ በሚገኘው ኢየሩሳሌም ወርቅ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ኮርኒስ ውስጥ የመንደፋደፍ ድምፅ እንደሰሙ የሚናገሩት የኢየሩሳሌም ወርቅ ቤት ሰራተኞች፤ ለጊዜው ቢደናገሩም “እርግብ ነው” በሚል ተስማምተው ወደ ስራቸው መግባታቸውን ይገልፃሉ፡፡ ሆኖም ድምፁ እየጨመረ በመምጣቱ ጥርጣሬ ይገባቸውና አንደኛው ሰራተኛ ክፍት በሆነው ኮርኒስ በኩል ባትሪ አብርቶ ተጠግቶ ይመለከታል፡፡
ኮርኒስ ውስጥ የሚንደፋደፈው እርግብ ሳይሆን ሰው መሆኑን ያረጋገጠው የወርቅ ቤቱ ሰራተኛ፤ “ሌባ… ሌባ” እያለ ሲጮህ ያልደነገጠ የለም፡፡ ኮርኒሱ ውስጥ ያሸመቀውን ወጣት ጨምሮ ሁሉም ድንብርብሩ ወጣ፡፡ ለማምለጥ የሞከረውም ወጣት ሲንደፋደፍ ከጎኑ ያለው የላሊበላ ወርቅ ቤት ኮርኒሱ ተቀዶ መሬት ሊፈጠፈጥ ሲል አንዱ የእንጨት ምሰሶ ደግፎት ይተርፋል፡፡  በዚህ ዱብዕዳ ወርቅ በመግዛት ላይ የነበሩ ደንበኞችና የወርቅ ቤቱ ሠራተኞች መደናገጣቸው አልቀረም፡፡ በዚህ ግርግር ወጣቱ ተመልሶ ወደ ኮርኒሱ  ውስጥ ይሸሻል፡፡ ይሄኔ ሁሉም ባለወርቅ ቤት በየራሱ ኮርኒስ ውስጥ ባትሪና ሻማ ይዞ በመግባት ወጣቱን ተጠርጣሪውን ማደን ጀመረ ይላል፤ የቅዱስ የብር ጌጣጌጥ መሸጫ ቤት ሠራተኛ ብርሃኑ አበበ፡፡ ተርታውን ያሉት የወርቅ መሸጫ መደብሮች የጥንት ቤቶች ስለሆኑ በኮርኒሳቸው ውስጥ ለውስጥ እንደሚገናኙ የነገሩን ሠራተኞቹ፤ ማታ ማታ ቤቱን ከመዝጋታቸው በፊት ወርቅና ብሮቹን ካዝና ውስጥ ከተው እንደሚቆልፉባቸው ገልፀዋል፡፡
በየግል ተጀምሮ የነበረው ወጣቱን የማደን ዘመቻ ከደቂቃዎች በኋላ በፖሊስ ሃይል ተጠናክሮ ቢቀጥልም ወጣቱ እምጥ ይግባ ስምጥ ሊታወቅ አልቻለም - ይላሉ አቶ ኢዛና፡፡ ከዚያም ጣራው አናት ላይ ወጥተው አሰሳውን ቀጠሉ፡፡ ወጣቱን ባያገኙትም ስለእሱ ድርጊቶች የሚጠቁሙ ፍንጮችን ለማግኘት እንደቻሉ የሚናገሩት አቶ ኢዛና፤ አንድ ቦታ ላይ ጣራው መቀደዱን ማየታቸውን፤ እዚያው አካባቢም ጣራው የተቀደደበት መቀስ መገኘቱን ገልፀዋል፡፡ወዲያው የተቀደደውን ቆርቆሮ በባለሙያ እንዳስደፈኑ ጠቁመው፤ አሰሳው ግን ያለውጤት መቋጨቱን ተናግረዋል፡፡
በነጋታው አርብ ጠዋት ደግሞ ቅዱስ የብር ጌጣጌጥ መሸጫ መደብር ውስጥ ሌላ ፍንጭ ተገኘ፡፡ በሩን ለመክፈት ሲሞክር የበሩ ቁልፍ (ጋን) እንዳስቸገረው የሚያስታውሰው ብርሃኑ፤ የቤቱን ባለቤት ጠርቶ አብረው ከፍተው መግባታቸውን ይገልፃል፡፡ ውስጡን ሲቃኙም አንዳንድ ነገሮች ተመሰቃቅለው ያገኛሉ፡፡ ወዲያው ፖሊስ ይጠሩና ሌላ የፍለጋ ዘመቻ ይጀመራል፡፡ ሆኖም ተፈላጊው አልተገኘም፡፡
ቅዳሜ ጠዋትም ብርሃኑ ከሱቁ ባለቤት ጋር ነበር በሩን የከፈትነው፡፡ የብር ጌጦቹን የሚደረድርበትን የመዝጊያ ብረት ሸርተት ሲያደርግ ነው ፈፅሞ ካልጠበቀው ነገር ጋር የተፋጠጠው፡፡ ሁለት ቀን መከራቸውን ያበላቸው ወጣት፤ ትልቅ የብር መስቀል በእጁ ይዞ መስተዋቱ ጋ ተለጥፎ ቆሟል፡፡ “ፊት ለፊት ቢያገኘኝ ግንባሬን ብሎኝ ወደ ውጭ ለመፈትለክ አስቦ እንደነበር ያስታውቅበታል” ያለው ብርሃኑ፤ በመስተዋት ውስጥና ውጭ ሆነን እንፋጠጣለን ብሎ የጠበቀ አይመስልም ብሏል፡፡ በሩን ከፍተው ሲገቡ ወደ ውስጥ ሊያመልጥ ቢሞክርም ወዴትም ሳይደርስ እንደያዙት የሚናገረው ብርሃኑ፤ ወዲያው  ተዝለፍልፎ መውደቁንም ገልጿል፡፡ ሰውነቱ ደካክሞና አቅም ክዶት እንደነበር በመግለፅም የምግብ እጥረት ሳያጋጥመው እንዳልቀረ ግምቱን ገልጿል፡፡
ወጣቱ ኪሱ ሲፈተሽ የብር ጌጦችና ጥቂት የወርቅ ቀለበቶች የተገኙበት ሲሆን ጀርባው ላይ ባዘለው ቦርሳ ውስጥ ደግሞ ውሃ፣ ቆሎ፣ መቀስ፣ ባትሪ እና የስለት መሳሪያዎች እንደተገኙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡ ተጠርጣሪው ወጣት ሰውነቱ በመጎዳቱና አቅም በማጣቱ፣ ራስ ደስታ ሆስፒታል ገብቶ ለአምስት ቀናት የህክምና እርዳታ የተደረገለት ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በአራዳ ክ/ከተማ ፒያሳ ፖሊስ ጣቢያ በምርመራ ላይ እንደሚገኝ ፖሊስ ጠቁሟል፡፡ ፒያሳ የሚገኙ አብዛኞቹ ወርቅ ቤቶች በመደብራቸው ውስጥ እያንዳንዳቸው ከ2 ሚ.ብር ያላነሰ የወርቅና ብር ጌጣጌጦች እንዳላቸው ምንጮች ሲገልፁ፤ በዚህ ዓመት ብቻ በእነዚህ ወርቅ ቤቶች ከአራት ጊዜ በላይ የዝርፊያ ሙከራ እንደተፈፀመባቸው ፖሊስ ገልጿል፡፡

Published in ዜና

በሪል እስቴቱ የተገዙ የግንባታ ቦታዎችን ለመውረር የተዘጋጁትን ህገ ወጦች እንፋረዳለን ብለዋል

በግንባታ መዘግየት እንዲሁም ከደንበኞች ጋር በተፈጠረ አለመግባባት እና በተለያዩ ችግሮች ምክንያት የአክሰስ ሪልስቴት መስራችና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ከአገር ወጥተው አለመመለሳቸው የሚታወስ ሲሆን፤ መንግስት የግንባታ ቦታዎቹ ላይ ህገወጥ ወረራ እንዳይካሄድ መከላከል አለበት ሲሉ ቤት ገዢ ደንበኞች ጠየቁ፡፡
ቦሌ ፍሬንድሺፕ ኢንተርናሽናል ሆቴል ፊት ለፊት የባለ 14 ፎቅ ህንፃ መሰረት እንደተጀመረና መቶ ሚሊዮን ብር እንደወጣበት የገለፀው የቤት ገዢዎች ኮሚቴ፤ ህገ-ወጥ መሬት ወራሪዎች ከመቶ መኪና በላይ አፈር በመድፋት ቦታውን ከጥቅም ውጭ አድርገውብናል ብሏል የኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ አክሎግ ስዩም፣ ለፖሊስ አመልክተን ምላሽ እየጠበቅን ነው ብለዋል፡፡
ከአሜሪካ እንደመጡ የገለፁ የቤት ገዢዎች ተወካይ በበኩላቸው፤ በርካታ ኢትዮጵያዊያን በቤት ሰራተኝነትና በሌሎች ዝቅተኛ ስራዎች ለፍተው ባጠራቀሙት ብር ከሪል ስቴቱ ቤት ለመግዛት ክፍያ መፈፀማቸውን ተናግረዋል፡፡
በእኛ ላይ የደረሰው ችግር አገሪቱንም ይጐዳል ያሉት እኚሁ ተወካይ፤ በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ይህንን ችግር ሲሰሙ ወደ አገራቸው ተመልሰው የመስራት ፍላጐታቸው በፍርሃት ይሰናከላል ብለዋል፡፡
“የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትራችን መሞታቸው የተሰማን አሁን ነው” ካሉ በኋላ፤ መንግስት ለህልውናው ሲል  እልባት እንዲሰጠን እንጠይቃለን ብለዋል፡፡
በፍ/ቤት የተጀመረው ሂደት በአብዛኛው ቤቶቹን ወደ ሀራጅ ሽያጭ ስለሚወስድ በቤት ገዢዎች ላይ ተጨማሪ ጉዳት እያደረሰ ነው ያሉት የኮሜቴው አባላት፣ አክሰስ ሪልስቴት ህልውናው እንዲቀጥልና ቤት ገዢዎችም እንዳይጐዱ የሚያስችል መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡
በከተማዋ 20 ሽያጭ የተካሄደባቸውና ዘጠኝ ሽያጭ ያልተካሄደባቸው የሪልስቴቱ የግንባታ ቦታዎች መኖራቸውን የገለፀው ኮሚቴው፣ እነዚህን ቦታዎች ለመቀራመት የሚሞክሩ ህገወጦች ስጋት ሆነውብናል ብሏል፡፡
በአክሰስ ሪልስቴት ውስጥ ችግር ከተፈጠረ በኋላ በ1800 የአገር ውስጥና በ350 በውጭ የሚኖሩ ቤት ገዢዎች የኩባንያው ባለአክሲዮን በመሆን እንደ አዲስ ያዋቀሩት ሲሆን፤  ከ1.4ቢሊዮን ብር በላይ ክፍያ መፈፀማቸውም ተገልጿል፡፡

Published in ዜና

ሌላ ጉድጓድ መቆፈር እጀምራለሁ ብሏል
ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የአለም አገራት በነዳጅ ፍለጋ ስራ ላይ የተሰማራው “ታሎው ኦይል” ኩባንያ፣ በደቡብ ኦሞ ቁፋሮ፣ የነዳጅ ሳይሆን የውሃ ክምችት ማግኘቱን ትናንት አስታወቀ፡፡
ዘ አይሪሽ ታይምስ እንደዘገበው፣ ኩባንያው “ሺመላ” በተባለ ቦታ፣ የእሳተ ጐመራ አለቶችን ጭምር በመቦርቦር 1,940 ሜትር ጥልቀት ድረስ በቁፋሮ ማካሄዱን ጠቅሶ፤ ከፍተኛ የውሃ ክምችት የያዘ የምድር ውስጥ ሃይቅ ማግኘቱን ገልጿል፡፡
ኩባንያው የነዳጅ ፍለጋ ቁፋሮው ስኬታማ ባይሆንም ተስፋ እንደማያስቆርጠው ገልጾ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የጀመረውን የነዳጅ ፍለጋ በመቀጠል  ‘ጋርዲም - አንድ’ የተባለ ሌላ አዲስ ጉድጓድ፣ በዚያው በደቡብ ኦሞ ራቅ ብሎ በሚገኝ ቦታ ቁፋሮ ለመጀመር መዘጋጀቱን ተናግሯል፡፡ ኩባንያው በደቡብ ኦሞ አካባቢ ሲያከናውነው የቆየውን ሌላ የነዳጅ ጉድጓድ ቁፋሮ፣ ምንም አይነት ተጨባጭ ውጤት ባለማግኘቱ በዚህ አመት መጀመሪያ ማቋረጡንም ዘ አይሪሽ ታይምስ አስታውሷል፡፡
ታሎው ኦይል የ‘ሺመላ - አንድ’ ቁፋሮውን ያለስኬት ማጠናቀቁን ተከትሎ፣ የኩባንያው የአክሲዮን ዋጋ በ1 ነጥብ 3 በመቶ መቀነሱ ተነግሯል፡፡
በደቡብ ኦሞ በሚደረገው የነዳጅ ፍለጋ፤ ታሎው ኦይል 50 በመቶ፣ አፍሪካ ኦይል ኮርፖሬሽን 30 በመቶ፣ ማራቶን ኦይል ኢትዮጵያ 20 በመቶ ድርሻ ይዘው በሽርክና እየሰሩ እንደሚገኙ ዘገባው ጨምሮ ገልጧል፡፡

Published in ዜና

ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው የህዳሴ ግድብ፤ በሱዳን፣ ግብፅና ኢትዮጵያ ትብብር መሠራት ነበረበት (ያሉት የሱዳን የውሃ ኤክስፐርት ዶ/ር ሳልማን አህመድ ሳልማን፤ “ወደፊትም ተመራጩ መፍትሔ የሦስቱ አገራትና የሌሎቹ የተፋሰሱ አገሮች ትብብር ነው” ብለዋል፡፡
“ሱዳን እና የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ መልካም እድሎች እና ፈተናዎች” በሚል ርዕስ ሰሞኑን በሱዳን በተዘጋጀ ወርክሾፕ ላይ ጥናት ያቀረቡት ዶ/ር ሳልማን፤ የተፋሰሱ አገራት በወንዙ ላይ እኩል መብት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ “በዚህ መንገድ የተቃኘ የትብብር ሀሳብ፣ ስድስት አገራት ተስማምተውበት ፈርመዋል፤ በኢትዮጵያ ፓርላማም ፀድቋል” ያሉት ዶ/ር ሳልማን፤  “አምስት ፈራሚ አገራት በፓርላማ ካፀደቁት በአለም አቀፍ ህግ መሰረት አስገዳጅነት ያለው ህግ ይሆናል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የትብብር ማእቀፉ ታሪካዊ መብታችንን ያሳጣናል በሚል ግብፅና ሱዳን የሚያሰሙትን ተቃውሞ መሰረተቢስ ነው ሲሉም አጣጥለውታል።
የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በቴክኒክ፣ በኢኮኖሚም ሆነ በአካባቢ ጥበቃ ረገድ የሚደገፍ ነው ያሉት ኤክስፐርቱ፤ ግድቡ በግብፅ፣ በሱዳንና በኢትዮጵያ ትብብር መሰራት ነበረበት፤ ቀድሞ ተሰርቶ ቢሆን ኖሮ ግብፅና ሱዳን ባለፉት ዓመታት  ያጋጠሟቸው ችግሮች አይፈጠሩም ነበር ብለዋል፡፡ ሱዳን ከታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ሀይል በመግዛት የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ትሆናለች  ያሉት ዶ/ር ሳልማን፤ ሱዳን በ1959ኙ ስምምነት መሰረት  ከተመደበላት ኮታ ውስጥ 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሀ ለምን እንዳልተጠቀመች  የመስኖና ተፈጥሮ ሀብቶች ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ሹመኞቿ ሊጠየቁ ይገባል ብለዋል፡፡
በውይይቱ ተሳታፊ የነበሩት የግብፅ የኢንፎርሜሽን አታሼ አብዱራህማን ናስር፤ የተፋሰሱ አገራት የሌሎችን አገራት ፍላጎት በማይነካ መልኩ የሚያካሂዱትን ልማት ግብፅ ትደግፋለች  ሲሉ አስተያየት ሰንዝረዋል፡፡

Published in ዜና

የአልባሳት፣ የጨርቃጨርቅ እና የእግር ሹራብ አምራቾችንና ነጋዴዎችን በአንድነት ያሰባስባል የተባለ የንግድ ሣምንት ከነሐሴ 11-14 2006 ዓ.ም በአሜሪካን ላስቬጋስ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገለፁ፡፡
አለማቀፍ የፋሽን ድርጅቶች ይሳተፉበታል የተባለው የንግድ ሣምንት አለማቀፍ የፋሽን ማህበረሰቡን በማቀራረብ ሰፊ ግብይት ይፈፀምበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የዝግጅት አስተባባሪ የ251 ኮሚኒኬሽንና ማርኬቲንግ ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ አዲስ አለማየሁ ገልፀዋል፡፡
አክለውም በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ አልባሣት፣ ጨርቃጨርቅ እና ጫማ አምራቾች እንደሚሳተፉና ከ100 ሃገራት ከተውጣጡት የንግድ ሳምንቱ ተሳታፊ ኩባንያዎች ጋር የረዥም ጊዜ ግንኙነት ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
የንግድ ትርኢቱ ከ6 ሺህ በላይ የሚሆኑ የምርት አይነቶች የሚቀርቡበት መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፤ የ251 ኮሚኑኬሽን ተባባሪ የሆነው ማጂክ ኢንተርናሽናል የአለማቀፍ ቢዚነስ ኃላፊ ቦብ በርግ በበኩላቸው በዘርፉ የተሰማሩ የኢትዮጵያ ፋብሪካዎች ከንግድ ትርኢቱ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል፡፡
በንግድ ትርኢቱ ላይ ይሳተፋሉ ተብለው ለሚጠበቁ የኢትዮጵያ የቆዳ ኢንዱስትሪ ማህበር፣ ለኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅ አምራች ማህበራት እና ለUSAID እንዲሁም ለአሜሪካ ኤምባሲ የፕሮግራም አዘጋጆች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡  

Published in ዜና

በሶሻል ሚዲያ ላይ ስላንቺ የተፃፉ ነገሮች አሉ፡፡ ምንድነው ነገሩ?
በ”ቃል ኪዳን” መጽሔት ላይ የወጣውን መረጃ አይተሽ ይሆናል፡፡ መጽሔቱ ይዞት የወጣውን መረጃ ተመርኩዞ ነው ሶሻል ሚዲያውም የስም ማጥፋት ውንጀላውን የቀጠለው፡፡ አስገራሚው ነገር መጽሔቱ ከእኔ ጋር ያደረገው ቃለ መጠይቅም ሆነ የተለዋወጥነው መረጃ የለም፡፡ ዘገባው ሲወጣ፣ እኔ ከነአካቴው አዲስ አበባ አልነበርኩም፤ ለስራ አዳማ ሄጄ ነበር፡፡ የፋሲካን በዓል እንኳን ከቤተሰብ ጋር አላሳለፍኩም፡፡
በአሜሪካና በእስራኤል ኮንሰርት ለማቅረብ ከፕሮሞተሮች ጋር ጨርሼ፣ ኤምባሲ ለመግባት በዝግጅት ላይ ነበርኩ፡፡ የአዳማ ስራዬን ጨርሼ፤ ፕሮሞተሬ ጋር ስደውል አስደንጋጭ መልስ ሰጠኝ፡፡
ምን አለሽ?
መፅሄቱ ያወጣውን ዘገባ ነው የነገረኝ፡፡ የአዕምሮ ጤንነቴ እንደታወከና ሰሜን ሆቴል አካባቢ የሚገኘውን ቤቴን ለቅቄ፣ ኦሎምፒያና ላፓሪዚያን አካባቢ እንደምውል ፅፎ ከእነፎቶዬ አውጥቶታል፡፡ ከአንድ ወር ስራ በኋላ ተመልሼ አዲስ አበባ ስመጣ፣ ጉዳዩን ለብሮድካስት ኤጄንሲ አመለከትኩ፡፡ ብሮድካስት ኤጀንሲም መፅሄቱ ማስተባበያ እንዲያወጣ ነገረው። ማስተባበያው ግን አልተሰራም፡፡ ይሄንንም አሳወቅሁኝ፡፡ ወሬው ቤተሰቤን ሁሉ ግራ አጋብቶ ነበር፡፡ እናቴ አሁንም ድረስ ታማ ተኝታለች። እኔ ቤተሰብ የማስተዳድር ሰው ነኝ፣ ሌሊት ሰርቼ ቀኑን ሙሉ የምተኛ ሰው አይደለሁም፡፡ ይሄው መጽሔት ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ላይም የስም ማጥፋት ውንጀላ ፈጽሞበታል፡፡ ለጎሳዬ እንደውም ማስተባበያ ሰርተውለታል፤ ያውም ከእኔ በኋላ ነው ለማንኛውም በመፅሄቱ ላይ ክስ ለመመስረት ሂደቱን ጀምሬአለሁ፡፡
የውጭ አገር ኮንሰርቱ ምን ደረሰ?
የተናፈሰው ወሬ ሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ውጭ አገርም ደርሷል፡፡ አንድ ፕሮሞተር ደግሞ ለኮንሰርት ሰው ሲወስድ፣ ታሪኩን በደንብ አጥንቶ ነው እንጂ ዝም ብሎ ከፍተኛ ብር አውጥቶ ሪስክ አይወስድም፡፡ ፕሮሞተሬ ኤምባሲ ለቪዛ ከመግባቴ በፊት ማድረግ ያለብኝን ነገር እንደሚነግረኝ ገልፆልኝ ነበር፡፡ በኋላ ግን ከእኔ ጋር ያሰበውን ኮንሰርት ሰርዞ፣ ከሌላ ድምፃዊ ጋር መዋዋሉን ነገረኝ፡፡ ምክንያቱን እንዲነግረኝ ጠይቄው ነበረ፡፡ ለጊዜው ትቼዋለሁ ብቻ ነው ያለኝ፡፡
ከዚህ ቀደም የውጭ አገር ኮንሰርቶች ሰርተሻል?
አረብ አገራት በሙሉ የቀረኝ የለም፡፡ አሜሪካና እስራኤል ግን የመጀመሪያዬ ጊዜ ነበር።
እስካሁን ስንት አልበሞችን ሰርተሻል?
“ሀቢቢ” የሚለውን ሙሉ አልበሜን ከሰራሁ በኋላ፤ አሁን ሁለተኛ ስራዬን ማስተሩን ጨርሻለሁ፣ እነ ይልማ ገብረአብ፣ መሰለ ጌታሁን፣ ሱራፌል አበበ፣ አዱኛ ቦጋለ የተሳተፉበት ሙሉ ስራ አልቆ ተቀምጧል፡፡ ምክንያቱም አሁን ሙዚቃ ቤቶች የኮፒራይት ጉዳይ ስለሚያሳስባቸው ስራዎችን አይቀበሉም።
አሁን ምን እየሰራሽ ነው ታዲያ?
አንድ የሱዳን ካምፓኒ ከሱዳን አገር መጥቶ፣ ሙሉ የሱዳንኛ ዘፈን ከፍሎ አሰርቶኛል፡፡
ምን ያህል ተከፈለሽ?
ለአስራ አንድ ዘፈኖች፤ አስራ ሶስት ሺህ ብር ነው የከፈሉኝ፡፡  ከእነ ባንዳቸው መጥተው እዛ አገር የሚወደዱ ሱዳንኛ ዘፈኖችን አሰርተውኛል።  
ከሙዚቃ ስራ ውጪ በምን ትተዳደሪያለሽ?
እኔ የስምንት ቤተሰብ አስተዳዳሪ ነኝ፤ የምኖረው ከእናቴ ጋር ነው፡፡ “ሀቢቢ ባንድ” የሚባል የራሴ የሙዚቃ ባንድ አለኝ፡፡ አሁን ለጊዜው ስራው ስለቆመ ንግድ ጀምሬያለሁ። ኮስሞቲክሶችና ሌሎች የመዋቢያ ቁሳቁሶችን ይዤ ባዛር ላይ እሳተፋለሁ፡፡ አሁን ሙዚቃ ብዙም አዋጪ ስላልሆነ፣ ባለኝ አቅምና ችሎታ ወደ ንግዱ እየገባሁ ነው፡፡ በቅርቡ “ጥራኝ አዳማ” የሚል ነጠላ ዜማ ለቅቄያለሁ። ለመኖርም ለመስራትም የማስበው አዳማ ነው፡፡ አሁን ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንኩ ትንሽ እረፍት እፈልጋለሁ፡፡ ቤተሰቤን ይዤ። በተሰራው ስራ በጣም ነው የከፋኝ፡፡ ስሜን ያጠፉት ኢትዮጵያዊነት የማይሰማቸው ግለሰቦች ናቸው። እኔ ፍፁም ጤነኛና የስራ ሰው መሆኔን ማንም ኢትዮጵያዊና አድናቂዎቼ በዚህ አጋጣሚ እንዲያውቁልኝ እፈልጋለሁ፡፡

Published in ጥበብ

           ኢትዮጵያ በአለማቀፍ ደረጃ ለሚከሰቱ የርሃብና የድህነት ቀውሶች ተገቢ መፍትሄ የማፈላለግ ዓላማ ያለውንና በአለማቀፍ የምግብ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲቲዩት የተዘጋጀውን ‘2020 ቢልዲንግ ሪሳይለንስ ፎር ፉድ ኤንድ ኒዩትሪሽን ሴኪዩሪቲ’ የተሰኘ አለማቀፍ የምግብ ዋስትና አቅም ግንባታ ፖሊሲ የምክክር ጉባኤ እያስተናገደች ነው። ፖሊሲ አውጪዎችን፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ የግሉን ሴክተር፣ ተመራማሪዎችንና ማህበረሰቡን በምግብ ደህንነት ዙሪያ መረጃ ለመስጠት፣ ተጽእኖ ለመፍጠርና ጉዳዩን ቀዳሚ አጀንዳቸው አድርገው እንዲንቀሳቀሱ አለማቀፍ ንቅናቄን ለመፍጠር በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ነው የተባለው ይህ አለማቀፍ የፖሊሲ ምክክር ጉባኤ፤ በዘርፉ ያንዣበቡ አደጋዎችን ለይቶ በማውጣት በጋራ የሚመከርበት፣ መፍትሄዎች የሚመነጩበት፣ ክፍተቶች የሚለዩበትና ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ የድርጊት መርሃግብሮች የሚቀረጹበት ነው ተብሏል።

ፖሊሲዎችን፣ ኢንቨስትመንቶችንና ተቋማትን በማሻሻል በአለማቀፍ ደረጃ የምግብ ደህንነትን ማጠናከር በሚቻሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በሚመክረው ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና አለማቀፍ ጉባኤ እያስተናገደች ነው አለማቀፍ ጉባኤ ላይ፣ በተለያዩ ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ 28 ያህል የጥናት ወረቀቶች የሚቀርቡ ሲሆን በአለማቀፍ ደረጃ ታዋቂነትን ያተረፉ 140 ባለሙያዎችና ተመራማሪዎችም በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ ይሰጣሉ። በጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ እና በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ንኮሳዛና ድላሚኒ ዙማ ንግግር፣ ከትናንት በስቲያ በሸራተን አዲስ የተከፈተውና ከተለያዩ የአለም አገራት የተውጣጡ ከ800 በላይ በምግብ፣ በጤና፣ በግብርና፣ በሰብአዊ ተግባራትና ከልማት ጋር በተያያዙ ሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ ባለሙያዎችና የሚመለከታቸው አካላት ተወካዮች እየተሳተፉበት የሚገኘው ይህ አለማቀፍ ጉባኤ፣ ዛሬ ምሽት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

የፈጠራ ስራቸው የስንዴን ምርት ከ3 እጥፍ በላይ ማሳደግ አስችሏል ከ42 ሃገራት የተውጣጡ 700 ተመራማሪዎች በውድድሩ ተሳትፈዋል

            ኢትዮጵያዊው ተመራማሪ ዶ/ር መለሰ ተመስገን፣ በተለያዩ ዘርፎች ላይ ትኩረት በማድረግ ለአፍሪካ ችግሮች መፍትሄ የሚሰጡ የፈጠራና የምርምር ውጤቶችን ለሚያበረክቱ ተመራማሪዎች በየአመቱ የሚሰጠው ‘ኢኖቬሽን ፕራይዝ ፎር አፍሪካ’ የተባለው ታላቅ አህጉራዊ ሽልማት አሸናፊ ሆኑ። ዶ/ር መለሰ ለዚህ አህጉራዊ ሽልማት የበቁት፣ ‘አይባር ቢቢኤም’ የተባለውና በአነስተኛ ዋጋ ለገበያ በመቅረብ ላይ የሚገኘው የኮትቻ አፈር ማጠንፈፊያ መሳሪያ የፈጠራ ስራቸው፣ የህዝብን ኑሮ በማሻሻል ረገድ ለውድድር ከቀረቡ በርካታ የፈጠራና የምርምር ውጤቶች ብልጫ በማሳየቱ እንደሆነ በተለይ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል። ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት ለተመረጡና የላቀ የምርምር ውጤት ላበረከቱ ተመራማሪዎች በየአመቱ ሽልማት የሚሰጠው አፍሪካን ኢኖቬሽን ፋውንዴሽን (The African Innovation Foundation) የተባለው ተ ቋም ፣ ዘ ንድሮም ከ42 የአፍሪካ አገራት የተውጣጡ 700 ተመራማሪዎችና የፈጠራ ባለሙያዎች በዕጩነት የቀረቡበት ውድድር በማካሄድ፣ ከተደጋጋሚ ምዘናና ማጣሪያ በኋላ፣ ባለፈው ሳምንት በናይጀሪያ አቡጃ በተካሄደ ስነስርዓት ላይ ኢትዮጵያዊውን ዶ/ር መለሰን ጨምሮ ሶስት የአህጉሪቱ ምርጥ ተመራማሪዎች ሸልሟል።

ዶ/ር መለሰን ለዘንድሮው የ‘ኢኖቬሽን ፕራይዝ ፎር አፍሪካ’ ተሸላሚነት ያበቃቸው ‘አይባር ቢቢኤም’፣ የተባለው የቴክኖሎጂ ፈጠራቸው፤ ውሃማ አካባቢዎችን በቀላሉ ለማጠንፈፍ የሚያስችል ሲሆን፣ ቀደም ሲል ለረጅም ዓመታት ኢትዮጵያዊው ተመራማሪ ዶ/ር መለሰ ተመስገን አህጉራዊ ሽልማት ተቀበሉ የፈጠራ ስራቸው የስንዴን ምርት ከ3 እጥፍ በላይ ማሳደግ አስችሏል ከ42 ሃገራት የተውጣጡ 700 ተመራማሪዎች በውድድሩ ተሳትፈዋል በአለም አቀፍና ሀገራዊ የምርምርና የትምህርት ተቋማት በምርምር የተሰሩት መሳሪያዎች ዉጤታማ ሳይሆኑ መቆየታቸው የተጠቀሰ ሲሆን የእሳቸው ፈጠራ ችግሩን ለመቅረፍ እንደቻለ ታውቋል። ተመራማሪውን ለሽልማት ካበቋቸው ምክንያቶች መካከል፣ ከዚህ በፊት ባልታየ መልኩ ለየት ባለ አቀራረብ ሰርተው ያወጡት ይህ የኮትቻ አፈር ማጠንፈፊያ መሳሪያ፣ የግብርና ምርትን በማሳደግና የህዝቡን ኑሮ በመቀየር በኩል ያለው አስተዋፅዖ ከፍተኛ መሆኑ በተግባር መረጋገጡ ተጠቃሽ ነው።።

መሳሪያው በአነስተኛ ዋጋ ለገበያ የሚቀርብ ከመሆኑ በተጨማሪ፣ ለአጠቃቀም ምቹ መሆኑም ተፈላጊ እንደሚያደርገው የተናገሩት ዶ/ር መለሰ፣ እስካሁን በ ጥቅም ላ ይ በ ዋለባቸው ማ ሳዎች ላ ይም የስንዴ ምርትን ከሶስት እጥፍ በላይ ድረስ ለማሳደግ መቻሉንና በአመት ሁለት ጊዜና ሦስት ጊዜ ለማምረት እንደሚያስችልም ገልጸዋል። ድርቅ በሚያጠቃቸው አካባቢዎችም የዝናብ ውሃን በማቆር ምርታማነትን ለማሳደግ እንደተቻለ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ለአነስተኛ መስኖና ለተለያዩ አገልግሎቶች እንደሚውልና በአለም ላይ ካሉ ተመሳሳይ መሳሪያዎች የተሻለ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በኢትዮጵያ ከ5 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ቦታ፣ ውሃ የሚተኛበት በመሆኑ የግብርና ስራ የማይከናወንበት ሲሆን የዚህ መሳሪያ መፈጠር መሰል ቦታዎችን ለእርሻ ስራ በማዋል በአገሪቱ ምርታማነትን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተነግሯል። ዶ/ር መለሰ ከያኔው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለማያ የግብርና ኮሌጅ በግብርና ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በማእረግ ተቀብለው በግብርና ምርምር ኢንስቲቲዩት የሰሩ ሲሆን እንግሊዝ አገር ከሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኒውካስል አፖንታይን፣ በተመሳሳይ የትምህርት መስክ የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል። ወደ አገራቸው ተመልሰው በግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በተመራማሪነት ለ15 አመታት ካገለገሉ በኋላም፣ ባገኙት የትምህርት ዕድል ኒዘርላንድ ውስጥ በሚገኘው ዴልፍት ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂ እና የዩኔስኮ የትምህርት ተቋም የውሃ ሃብቶች የትምህርት ክፍል፣ የፒኤችዲ ትምህርታቸውን ተከታትለው ተመርቀዋል።

ተመራማሪው፤ ብሄራዊ የግብርና ሜካናይዜሽን ምርምር ፕሮግራምን በማስተባበር የሰሩ ሲሆን በተለያዩ አገር አቀፍና አለም አቀፍ አውደጥናቶች ላይ የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማቅረብና ለህትመት በማብቃት ይታወቃሉ። ዶ/ር መለሰ ተመስገን፣ የግብርና ምርታማነትን የሚያሳድጉ አስር ያህል የምርምር ውጤቶችን በማውጣትም ጥቅም ላይ እንዲውሉም አድርገዋል። በሰኔ 2002 በኢፌዲሪ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን አዘጋጅነት፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ጠቀሜታ ላይ በማዋል የላቀ ስኬት ላስመዘገቡ ባለሙያዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠውን ብሄራዊ ሽልማት፣ ከቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዚደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ እጅ የተቀበሉ ሲሆን ሁለት ጊዜ የሀገር አቀፍ ተሸላሚ በመሆንም የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ናቸው። ዶ/ር መለሰ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በረዳት ፕሮፌሰርነት በማስተማር፤ እንዲሁም የማስተርስና የዶክትሬት ተማሪዎችን የምርምር ሥራ በማማከር ያገለገሉና በማገልገል ላይ ያሉ ከመሆናቸው ሌላ፣ ከ25 በላይ የጆርናልና ሌሎች ሳይንሳዊ ፅሁፎችን ያሳተሙ አንጋፋ ተመራማሪ ናቸው።

Monday, 19 May 2014 09:07

የመፅሐፍ ቅኝት

መንደርተኝነት፤ የስንኩል ፖለቲከኞች አስተሳሰብ ውጤት

ርዕስ - ዶክተር አሸብር እና ሌሎችም፤ / የገፅ ብዛት - 237 / የህትመት ዘመን - መጋቢት 2006 ዓ.ም / የሽፋን ዋጋ - በኢትዮጵያ 65 ብር፤ በአሜሪካ 10 ዶላር/ ህትመት - ኤች ዋይ ኢንተርናሽናል ደራሲ - አሌክስ አብርሃም / ዘውግ - አጭር ልብወለድ (መድበል)

/ ቅድመ ኩሉ

                       የሥነ ፅሁፍ ምሁራን፤ አጭር ልብወለድ ከክርስቶስ ልደት 3000 ዓመት በፊት እንደተጀመረ ማስረጃ እየጠቀሱ ያስረዳሉ። እንዲያውም አፍአዊ ስነቃል ወይም ተረትን እንደ አጭር ልብወለድ በመውሰድ ዘመኑን ከዚያም ያርቁታል። ስቴቨን ዊልከንስ የተባሉ የሥነ ጽሑፍ ተመራማሪ እንደሚሉት፤ አንድን አጭር ልብወለድ ለመዳኘት ለማሄስ የሚከተሉትን አምስት መመዘኛዎች ከግምት ውስጥ ማስገባት ያስፈልጋል። ወጥነት (Originality) የደራሲው የፈጠራ ብቃት (creativity) ሴራ (Plot) ጭብጥ (theme) ፍጻሜ (ending) ከዚህ ሌላ አንድ አጭር ልብወለድ ከሰባት ሺህ እስከ አስር ሺህ በሚደርሱ ቃላት ብቻ መጻፍ እንዳለበት፤ ሆኖም አንዳንድ ምሁራን ከሁለት ሺህ እስከ አራት ሺህ በሚሆኑ ቃላት ብቻ መጻፍ አለበት ይላሉ። “ዶክተር አሸብር እና ሌሎችንም” ለማየት የተጠቀምሁት ከላይ የተዘረዘሩትን መመዘኛዎች ነው። ይህ ሲባል ሃያ አምስቱ ታሪኮች ሁሉ ተመዝነዋል ማለት አይደለም፤ ተነብበዋል፤ ግን ለማሳያ ያህል “ተሰቀለ ቢሉኝ ባርኔው ነው ብዬ” በሚል ርዕስ የተጻፈውን አጭር ታሪክ መርጨዋለሁ።

ለዚህ ምክንያቴ ከወቅቱ የአገራችን ሁኔታ ጋር ስለሚስማማ ነው። የትረካው ይዘት የታሪኩ ባለቤት (ተራኪው) አብርሃም የሚባል የአራተኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነው። በአንድ መኝታ ክፍል ውስጥ ስምንት ተማሪዎች ይኖራሉ፤ ከእነሱ ውስጥ ደግሞ “አስቻለው” የሚባል ጓደኛ ነበራቸው። አስቻለው “ሱስ” ከሚባል ነገር ሁሉ የሚቀረው አልነበረም፤ ያጨሳል፣ ይቅማል፣ ይጠጣል፣ ሃሽሽ ይጠቀማል፣ ይዘሙታል። ለዚህ ሁሉ ሱሱ ማስታገሻ ሲል ያገኘውን ሁሉ እየሸጠ ጓደኞቹን የሚያስመርር ሌባ ነበር። አንድ ቀን ምክንያቱ ባይታወቅም አስቻለው ራሱን ሰቅሎ ተገኘ። የተለያዩ ተማሪዎች እነ አስቻለው መኝታ ቤት እየመጡ ለቅሶ ደረሱ፤ እንዲያውም አንድ ቀን ከእነ መንደርተኝነት፤ የስንኩል ፖለቲከኞች አስተሳሰብ ውጤት ጨምሮ ብዙዎቹ ኮረዶች በቀላሉ ያፈቅሩት ነበር። የመጀመርያ ሚስቱን በ36 ዓመቱ ያገባው ፒካሶ፣ ሁለተኛ ሚስቱን በ79 ዓመቱ ነበር ያገባው - ያውም የ27 ዓመት ወጣት። አስቻለው መኝታ በር ላይ እንዲህ የሚል ሙሾ (የለቅሶ ግጥም) ተጽፎ ተገኘ “ተሰቀለ ቢሉኝ ባርኔጣው (የዲግሪ ቆብ) ነው ብዬ፣ ተሰቀለ ቢሉኝ ያ ሱሪው ነው ብዬ (የነበረው አንድ ያረጀ ጅንስ ሱሪ ብቻ ነበር)፣ ተሰቀለ ቢሉኝ “ግሬዱ” ነው ብዬ። ለካስ አስቻለው ነው ትልቁ ዱርዬ!!” ይህን ግጥም በደንብ ማየት ያስፈልጋል፤ ደራሲው ለታሪክ ማጓዣ የተጠቀመው ይህን ግጥም ነው። ግጥሙ የህዝብ ሲሆን የተገጠመውም ከሌሎች አርበኞች ጋር መራር መስዋዕትነት ከፍሎ ለዘውድ ያበቃቸውን በላይ ዘለቀን ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ በግፍ ከሰቀሉ በኋላ ነው።

“ተሰቀለ ቢሉኝ እንግቱ (ወታደራዊ ትጥቁ) ነው ብዬ፤ ተሰቀለ ቢሉኝ ሽጉጡ ነው ብዬ፤ ተሰቀለ ቢሉኝ ዝናሩ ነው ብዬ፤ ለካስ በላይ ኖሮአል ትልቁ ሰውዬ” የሚል ነው መሠረታዊው ግጥም። ከዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አንዱ ኳሽ ደግሞ ለጀግናው በላይ ዘለቀ የተገጠመውን ቀየረና ለዱርየው አስቻለው ተጠቀመበት፤ ግጥሙን ያነበበና አስናቀ የሚባል የጐጃም ልጅ እንዴት በጀግናው ይቀለዳል ብሎ አካኪ ዘራፍ ይላል፣ ደራሲው ይህንን ግጥም ነው የልብወለዱ የግጭት መነሻ ያደረገው። ከዚህ በኋላ ስቴቨን ዊልከንስ በአመለከቱን የአጭር ልብወለድ መመዘኛዎች መሠረት ልብወለዱን እንቃኘው። ወጥነት (Originality) “ተሰቀለ ቢሉኝ ባርኔጣው ነው ብዬ” ከወጥነት አንፃር ስናየው አዲስ ነገር ላናገኝ እንችላለን። ሆኖም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምን አይነት ሆደ ባሻ ትውልድ እያፈሩ እንደሆነ ትዝብቱን የገለጠበት መልካም ሃሳብ ነው። እርግጥ ነው፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች ረብሻ ሊቀሰቀስ ይችላል፤ ሲቀሰቀስም ኖሯል።

ምክንያቱ ግን የመንደርተኝነት ጣጣ አልነበረም፤ ወይ ከምግብ ጋር የተያያዘ ቅሬታ ውጤት ነው፤ አለዚያም አገራዊ የፖለቲካ ጥያቄ ነበር ብቸኛውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሲንጠው የኖረው። በሳል ጥያቄ ለማንሳት፣ በአገሪቱ የፖለቲካ ጉዳዮች ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ፣ ንቁ አዕምሮ ያስፈልጋል፤ ንቁ አዕምሮ በሌለበት ህሊና ውስጥ ሊነሳ የሚችለው መናኛና እዚህ ግባ የማይባል እንቶ ፈንቶ ጣጣ ብቻ ነው። እንቶ ፈንቶ ሰው የጠራ ዓላማ የለውም፤ በአንጻሩ ለሽብር እና ግርግር ምቹ በመሆኑ፣ በሆነ ባልሆነው ከጓደኛው፣ ወይ ከጐረቤቱ፣ ወይም ከመ/ቤቱ ሰዎች ጋር አምባጓሮ ከመፍጠር አይመለስም። ለምን? እንዴት? ማን? ብሎ መጠየቅና መረዳት ሽንፈት ይመስለዋል። ስለሆነም ድክመቱን በረብሻ መጋረጃ ይሸፍነዋል፤ የእሱን ጣጣ የጐሳ ካባ ስለሚደርብበት ሌሎችን ያነካካል። ስለሆነም ልብወለዱ መናኛ በምትመስል ምክንያት የዘመናችንን እውነት የሚነግረን በመሆኑ ፍልስፍናው ወጥ ነው ማለት እንችላለን። የደራሲው የፈጠራ ብቃት (creativity) ደራሲው በበነነ በተነነው ሁሉ የሚጋጩ ወጣቶችንና ምስኪን ፖለቲከኞችን የታዘበው በጥልቅ ስሜት ነው። ይታዘባቸዋል፤ ይተቻቸዋል። ግን “ደካሞች፣ ስግብግቦች፣ መንደርተኞች…” ብሎ አይፈርጃቸውም። ይልቁንም እያዝናና፣ እያዋዛ ልክ ልካቸውን ይነግራቸዋል። በአንድ ክልፍልፍ ጐረምሳ ምክንያት፣ የሁለት ብሔረሰብ ተወላጆች ጐራ ለይተው ዩኒቨርሲቲውን በጥናትና ምርምር ፋንታ የብጥብጥ መስክ ሲያደርጉት ያሳየናል። በመሆኑም የቋንቋና የአገላለጥ ጥበቡ የደራሲውን ፈጠራ እንድናደንቅ ይጋብዘናል።

ሴራ (Plot) በልብወለዱ ውስጥ “ምን ይፈጠር ይሆን?” ብለን የምንጨነቅበት የተወሳሰበ ሴራ አናይም፤ ሴራው በጣም ቀላል ነው። የአገራችን የፖለቲካ ስርዓት ባመጣው ጣጣ ምክንያት መንደርተኝነት በመንገሱ፣ ለሀገር ዕድገት መሠረት መሆን የሚገባቸው ወጣቶች ምስኪኑን ድምር ህዝብ ጭምር ለመከራ ሲዳርጉት ማሳየት ነው፤ የልብወለዱ ሴራ። የአጭር ልብ ወለድ ዓላማ ደግሞ እንደ ረጅም ልብ ወለድ የተወሳሰበ ሴራ በመፍጠር ያንን ለመፍታት መቃተት አይደለም፤ ነጠላ ታሪክ መስርቶ ነጠላ ታሪኩን ሊያስኬድለት የሚችል ሴራና ውሱን ወኪል ባለ ታሪኮች (ገፀ ባህርይ የሚባለው) ብቻ የሚያስፈልጉት የጥበብ ዘርፍ ነው። በዚህ ስሌት ሲታሰብ፣ የልብ ወለዱ ሴራ የዘመናችን (የሀገራችን) ጉልድፍ መንደርተኛ አስተሳሰብ ውጤት ነው ማለት ይቻላል። በመሆኑም ሴራው ከሁለት ብሔረሰብ በመጡ ወጣቶች መሃል የሚደረግ ድንገተኛ ፍልሚያ ነው። ጭብጥ (Theme) የልብወለዱ ጭብጥ ፖለቲካ ነው፤ ብላሽ የሆነ የመንደር ፖለቲካ። ብላሹ የመንደር ፖለቲካ ብዙውን (የሚመለከተውንም የማይመለከተውንም) የሚያነካካ ክፉ በሽታ ነው፤ ሊተላለፍ ይችላል። ሲተላለፍ ደግሞ ጦሱ ቀላል አይደለም።

እናም አንድ ትዕግስት የለሽ ተማሪ በጫረው የመንደርተኝነት እሳት የሁለት ብሔረሰብ አባላት የሆኑ ተማሪዎች ለከፍተኛ ብጥብጥና የአካል ጉዳት መዳረጋቸውን እንመለከታለን። ይህ እውነት በየቀኑም ባይሆን፣ በየሳምንቱ፣ በየወሩ እና በየዓመቱ የሚከናወን ቋሚ የብጥብጥ አጀንዳ ነው። ቀሽም ፖለቲካና ግልብ ፖለቲከኛ ሲገናኙ እንዲህ ናቸው፤ ምንም የማያውቁ አርሶ፣ ተሸክሞ፣ ሰርቶ በሌዎችን ሁሉ ለመከራና እንግልት ይዳርጋሉ። በደቡብ ክልል በነበሩ የጉራፈርዳ አርሶ አደሮች ላይ የተወሰደውን የማሳደድ እርምጃ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የተከሰተውን ተመሳሳይ የማሳደድ ጣጣ ልብ ማለት ያሻል። ሁሉም እርምጃዎች የግልብ ፖለቲከኞች የሥራ ውጤቶች ናቸው። በቅርቡ ባህርዳር ላይ ኳስ ሜዳ ውስጥ በተነሳ መለካከፍ ጉዳዩ ወደ አስቀያሚ የብሔር ግጭት መሸጋገሩም የዚሁ የግልብ ፖለቲካና ፖለቲከኞች የሥራ ውጤት ነው። ህዝቡማ በደርግም በኃይለሥላሴ ዘመንም በፍቅር የኖረ ክቡር ህዝብ ነው። ለትውልዱ የተዘጋጀለት መርዘኛ ወጥመድ ግን እጅግ አደገኛ ነው። አብሮ የኖረ ህዝብ ላይጫወት፣ ላይቀልድ፣ በአጠቃላይም እንደ ልቡ ላይንቀሳቀስ ነው ማለት ነው። ይህ ነው የልብ ወለዱ ሁነኛ ጭብጥ። ፍጻሜ (Ending) ልብወለዱ የሚጠናቀቀው “ኤሎሄ፣ ኤሎሄ፣ላማ፣ ሰበቅታኒ” ብሎ ነው።

ትርጉሙ “አቤቱ አባት ሆይ! ለምን ተውኸኝ” ማለት ነው፤ ቋንቋው ደግሞ እብራይስጥኛ። ይህ ታላቅ ልመና ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ ሞቱን በተመኘበት ቅጽበት የተናገረው ነው። እኛንስ አምላክ ለምን ተወን? የሚል መልእክት አለው። የልብወለዱ ዋና ባለ ታሪክ፣ በረብሻው ምክንያት ክፉኛ ተደብድቦ፣ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚገኘው ክሊኒክ ራሱን ስቶ ከቆየ በኋላ ሲነቃ በፌደራል ፖሊሶች ተከብቦ በማየቱ ነው፣ ከላይ ያለውን ኃይለቃል የሚናገረው። እንደኔ እምነት ይህ ጥልቅ ፍልስፍና ነው፤ ፖሊስ ብጥብጥ እንዳይነሳ መከላከል እንጂ በዱላ ብዛት ራሱን ስቶ የወደቀ ምስኪን ተሰብስቦ መጠበቅ ምን የሚሉት ተግባር ነው? ያውም ተበዳዩን ወንጀለኛ በማድረግ። በአጠቃላይ “ዶክተር አሸብር እና ሌሎችም” የአጫጭር ታሪኮች ስብስብ ሲሆን በምፀታዊ አቀራረቡ፣ ጥቃቅን በሚመስሉ የህብረተሰቡ የዕለት ተለት ጣጣዎች ላይ ትኩረት በማድረጉ፣ ጣፋጭ በሆነ መንገድ የተዘጋጀ በመሆኑ ተነባቢነቱ፣ አስተማሪነቱና አዝናኝነቱ የጐላ እንደሚሆን አልጠራጠርም። ሆኖም በቋንቋ አጠቃቀም ላይ መጠነኛ ግድፈት ለምሳሌ “ከዚያ” በማለት ፋንታ “ከዛ” ዓይነት አጠቃቀም፣ “ነፍስ” በማለት ፋንታ “ነብስ” ማለት፣ “ኧረ ይሄ ነገር ይችን ሴትዮ ያሳብዳቸዋል (ገፅ 81)” አይነት አንድና ብዙ አጠቃቀም ስላለ ድጋሚ በሚታተምበት ወቅት ቢስተካከል (ቢታረም) መልካም ይመስለኛል።

Published in ጥበብ

               ስፔናዊው ሰዓሊ ፓብሎ ፒካሶ የ20ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ አርቲስት እንደነበር ይታወቃል። እስከ 92 ዓመት እድሜው በመኖር ረዥም ህይወት ያጣጣመው ሰዓሊው፤ የዚያኑ ያህልም በሥራው ውጤታማ እንደነበር ይነገርለታል። በሙያ ዘመኑ እጅግ በርካታ የአሳሳል ዘይቤዎችንና ጭብጦችን የዳሰሰ ሲሆን በተለይ ኩቢዝም የተሰኘውን ዘመናዊ የሥነጥበብ እንቅስቃሴ በፈር-ቀዳጅነት በመምራት የገነነ ስም ተቀዳጅቷል። ፒካሶ ትውልዱ ስፔይን ይሁን እንጂ አብዛኛውን ህይወቱን ያሳለፈው ፈረንሳይ ውስጥ ነበር። የዚህን ታላቅ ሰዓሊ አዝናኝ እውነታዎች እነሆ በረከት - *አዋላጇ የሞተ መስሏት ነበር ፒካሶ ወደዚህች ምድር የመጣው በቀላሉ አልነበረም። በብዙ ውጣ ውረድ ነው የተወለደው። በዚያ ላይ ድክምክም ያለ ህፃን ነበር። በዚህ የተነሳ አዋላጇ ሞቶ የተወለደ ስለመሰላት ችላ አለችው። ጠረጴዛ ላይ አጋድማው እናትየዋን ልትንከባከብ ሄደች። ዶን ሳልቫዶር የተባለ ሃኪም አጎቱ ባያየው ኖሮ አክትሞለት ነበር፣ እሱ ነው ከሞት ያተረፈው።

“በዚያን ዘመን ሃኪሞች ትላልቅ ሲጋር ያጨሱ ነበር። አጎቴም ከእነሱ የተለየ አልነበረም። ጠረጴዛው ላይ ተጋድሜ ሲያየኝ ጪሱን ፊቴ ላይ አቦነነብኝ ። ይሄኔ ከመቀፅበት በብስጭት ድምፅ አሰማሁ” ሲል ፒካሶ የሰማውን ተናግሯል። አዝናኝ እውነታዎች ስለ ፓብሎ ፒካሶ *አፉን የፈታበት የመጀመርያው ቃል ሰዓሊነቱን ያወቀው ገና ሲወለድ ሳይሆን አይቀርም። ከአንደበቱ የወጣው የመጀመርያ ቃል እርሳስ (በስፓኒሽ “piz,”) የሚለው ነበር። ለነገሩ ሰዓሊነት ከዘራቸው ነው። አባቱ ሰዓሊና የሥነጥበብ አስተማሪ (ፕሮፌሰር) ነበሩ። ከ7 ዓመቱ አንስቶ በመደበኛ የሥነጥበብ ትምህርት ኮትኩተው ነው ያሳደጉት። ፒካሶ 13 ዓመት ሲሞላው አባትየው ስዕል መሳል እንደሚያቆሙ ምለው ተገዘቱ። ለምን ቢሉ? ልጃቸው ፒካሶ እንደበለጣቸው ስለተሰማቸው ነበር። *የመጀመርያ ስዕሉን በ9ዓመቱ አጠናቋል ፓብሎ ፒካሶ Le picador የተሰኘውን የመጀመርያ ስዕሉን ሰርቶ ያጠናቀቀው እ.ኤ.አ በ1890 ዓ.ም ሲሆን ያኔ ገና የ9 ዓመት ልጅ ነበር። ስዕሉም በኮርማ ትግል ላይ ፈረስ የሚጋልብ ሰው ያሳያል። የመጀመሪያ “ምሁራዊ” ሥራው የመጀመርያው ቁርባን የተሰኘ ሲሆን በስዕሉ ላይም እናትና አባቱ እንዲሁም አትሮንስ ፊት ተንበርክካ የምታነብ ታናሽ እህቱ ይታያሉ። ፒካሶ ይሄን ስዕሉን ሰርቶ ሲያጠናቅቅ የ15 ዓመት ታዳጊ ነበር። *ክፍል ውስጥ ረባሽ ነበር በሥነጥበብ በኩል ብሩህ አዕምሮ እንደነበረው ፈፅሞ የሚያጠራጥር አይደለም።

በእድሜ አምስትና ስድስት ዓመት የሚበልጡትን የክፍል ጓደኞቹን የትናየት ያስከነዳቸው ነበር። የሱ ችግር ረባሽነቱ ላይ ነው ። ይሄን አድርግ ሲባል ያፌዝ ነበር። በዚህም የተነሳ በተደጋጋሚ ባዶ ክፍል ውስጥ ተዘግቶበታል። “በረባሽ ተማሪነቴ ባዶ ክፍል ውስጥ ብቻዬን ይከረቸምብኝ ነበር። የክፍሉ ግድግዳ ኖራ የተቀባና አግዳሚ ወንበር ያለው ነው። እኔ ግን እዚያ መሆኑን እወደው ነበር። ምክንያቱም የስኬች ደብተሬን ይዤ እገባና ያለገደብ እስላለሁ---ዝም ቢሉኝ ያለማቋረጥ እየሳልኩ ለዝንተዓለም መቀጠል እችል ነበር” *የመጀመርያ ሥራው - 750 ዶላር ፒካሶ የመጀመሪያ ሥራውን የተዋዋለው ፈረንሳይ ውስጥ ከአንድ የስዕል ነጋዴ ጋር ሲሆን በወር 750 ዶላር እንዲከፈለው ነበር የተስማማው። *ፒካሶ ሞና ሊዛን ሰርቋል? በፍፁም አ ልሰረቀም። ነገሩ እንዲህ ነው። እ.ኤ.አ በ1911 ዓ.ም ሞና ሊዛ ከሉቨር ሙዚየም ትሰረቃለች። ፖሊስ የፒካሶ ገጣሚ ጓደኛውን Guillaume Apollinaireን ይይዘዋል። ጓደኛው ደግሞ ጣቱን ወደ ፒካሶ ይጠቁማል። ይሄን ጊዜ ፒካሶም ተይዞ ምርመራ ይደረግበታል። በኋላ ግን ሁለቱም በነፃ ተለቀዋል። *ፍቅረኞቹ ስፍር ቁጥር አልነበራቸውም ዝነኛ ሰዓሊ መሆኑ የፍቅረኞቹን ቁጥር አንበሽብሾለታል። አፍቃሪዎቹ ስፍር ቁጥር አልነበራቸውም። በሞዴልነት የሚሰራቸውንጨምሮ ብዙዎቹ ኮረዶች በቀላሉ ያፈቅሩት ነበር። የመጀመርያ ሚስቱን በ36 ዓመቱ ያገባው ፒካሶ፣ ሁለተኛ ሚስቱን በ79 ዓመቱ ነበር ያገባው - ያውም የ27 ዓመት ወጣት።

Page 11 of 21