<> ዶ/ር ሙሁዲን አብዶ ከላይ ያነበባችሁት ዶ/ር ሙሁዲን አብዶ ለዚህ አምድ አዘጋጅ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ ነው፡፡ ዶ/ር ሙሁዲን የማህጸንና ጽንስ ሕክምና እስፔሻሊስት ሲሆኑ የሚሰሩት በኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል እንዲሁም ሀያት እና ቅዱስፓውሎስ ሜዲካል ኮሌጅ በአስተማሪነት ነው፡፡የደም መርጋትን እንደበሽታ ከመቁጠር አስቀድሞ ተፈጥሮአዊውን ሁኔታ ኢንካርታ 2009/ እንደሚከተለው ይገልጸዋል፡፡ Thrombocytes, ወይም platelets በሚባል የሚታወቁ ትናንሽ እና ቀለም የሌላቸው ክብ ቅርጽ የሆኑ ህዋሳት በደም ውስጥ በብዛት ይገኛሉ፡፡

እነዚህ አካላት በማንኛውም ጊዜ የደም ስር በሚቆረጥበት ወይንም ደም በሚፈስበት ጊዜ ደምን ከመፍሰስ ለማዳን እንዲረጋ የማድረግ ስራ ያላቸው ናቸው፡፡ቅቁሮ..ስቁስ..ቋ ደም ቅዳና ደም መልስ የተባሉት የደም ስሮች ጉዳት እንደደረሰባቸው ሲያውቁ ወዲያውኑ እርስ በእርሳቸው በመጣበቅ ወይንም አንዳቸው በአንዳቸው ላይ በመውጣት ወደተቆረጠው የደም ስር በመሄድ አካባቢውን ይዘጋሉ፡፡ ከዚህም ባለፈ ደም እንዳይፈስ በርከት ያሉ መሰሎቻቸውን ወደ አካባቢው እንዲመጡ እና መፍሰስን እንዲያቆሙ እገዛ እንዲያደርጉ በደም ውስጥ መልእክት ያስተላልፋሉ፡፡ ይህ ጤነኛውና የሚፈለገው የደም መርጋት ሲሆን ጤነኛ ያልሆነውና በበሽታ መልክ የሚገለጸው የደም መርጋት በዶ/ር ሙሁዲን አብዶ እንደሚከተለው ተገልጾአል፡፡

ደም በደም ስሮች አማካኝነት የፈሳሽ ቅርጽ ይዞ እንደልብ እየተዘዋወረ መደበኛ ስራውን መስራት የሚገባው ሲሆን ያ ሳይሆን ሲቀርና ወደ መርጋትና አንዳንዴም ጠጥሮ የደም ስሮችን ሲያውክ እንዲሁም ሂደቱን ወይንም ዝውውሩን ሲያስተጉዋጉል የደም መርጋት ተከሰተ ይባላል፡፡ ማስተጉዋጎል ብቻም ሳይሆን ሕመም የሚፈጥር ሲሆን በተለይም የደም መልስ በሚባለው የሰውነት ክፍል ውስጥ መርጋት ሲፈጠር በተለያየ ምክንያት ከንቅላት ወይንም ሳንባ አካባቢ ከሚገኙ ትናንሽ የደም ስሮች በማለፍ እስከሞት የሚያደርስ ከፍተኛ አደጋ ይፈጥራል፡፡ በተለይም በአሁኑ ወቅት በማደግ ላይ ባሉ አገሮች እናቶችን ለሞት የሚያበቁ ከሚባሉ መካከል የሚጠቀስ ሕመም ነው፡፡ ይህ በሽታ ባደጉት አገሮች በከፍተኛ ደረጃ የቀነሰ በመሆኑ ለሞት ምክንያት መሆኑም እንዲሁ ወርዶ ይገኛል፡፡

እንደኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ አገሮች ግን በሆስፒታል ውስጥ ከሚሞቱ እናቶች በሚወሰደው መረጃ መሰረት እስከ 20 ኀየሚሆነው የእናቶች ሞት በደም መርጋት በሽታ ምክንያት በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ እጅግ አሳሳቢ ነው፡፡ ለእናቶች ሞት ምክንያት የተባሉት መድማት፣ መመረዝ፣ከወሊድ ጋር የምጥ መርዘም፣ ከውርጃ ጋር ተያይዞ የሚመጡ ችግሮችና የመሳሰሉት በምእተ አመቱ የልማት ግብ ትኩረት እንዲደረግባቸው አጽንኦት ቢሰጣቸውም የደም መርጋትም አንዱ በከፍተኛ ሁኔታ እናቶችን ለሞት የሚያበቃ እና ትኩረትን የሚሻ በሽታ ነው፡፡ የደም መርጋት ከእርግዝናና ከወሊድ ጋር የመከሰቱ ሁኔታ ቀደም ባሉት ዘመናትም የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ጊዜ ግን ካለው የአኑዋኑዋር ዘዴ ጋር በተገናኘ እጅግ ተስፋፍቶ እና ለብዙዎች ታማሚነት ምክንያት እየሆነ ነው፡፡ ምክንያቶቹም የሚታወቁ ናቸው፡፡ የደም ዝውውርን የሚያስተጉዋጉሉ ተብለው የሚጠቀሱት ምክንያቶች በዋናነት በሶስት ይከፈላሉ፡፡

* የደም ዝውውሩ በትክክለኛው መንገድ መሆን ሲገባው ነገር ግን ሲገታ፣

* በደም ውስጥ የደም መርጋትን አጋጣሚ የሚጨምሩ ነገሮች በሚጨምሩበት ጊዜ፣

* በደም ስር ውስጥ ያሉ ተፈጥሮአዊ አካላት በሚጎዱበት ወይንም አደጋ በሚደርስባቸው ጊዜ፣ ከላይ የተጠቀሱት ሶስት ምክንያቶች እርስ በእርሳቸው በሚደጋገፉበት ጊዜ ውጤቱ የደም መርጋት በሽታ ይሆናል፡፡ በተለይም በእርግዝና ወቅት ተጠቃሾቹ ምክን ያቶች እንዲከሰቱ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩ በርካታ አጋጣሚዎች የሚኖሩ በመሆኑ በበሽታው ለመያዝ ቀላል ይሆናል፡፡ አንዲት ሴት በእርግዝና ላይ ከሆነች እና በወሊድ ወቅት ሊያጋጥሙዋት ከሚችሉ የጤና እክሎች አንዱ የደም መርጋት ነው ፡፡ በዚህ ወቅት የደም መርጋት በሽታ እንዲከሰት የሚያደርጉ የተለያዩ አጋጣሚዎች በመኖራቸው ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል፡፡

•በእርግዝና ጊዜ ሰውነት በራሱ ደም እንዳይፈስ ለመከላከል ሲል የሚያዘጋጃቸው የደም መርጋት ተፈጥሮአዊ ሂደቶች ይጨምራሉ፡፡

•እርግዝናው ጊዜውን እየጨመረ በሚመጣት ጊዜ ጽንሱ በማደጉ ምክንያት በሚፈጠረው ጭነት ምክንያት ደም መልስ የሚባለው አካል በትክክል ስራውን እንዳይሰራ የሚሆንበት አጋጣሚ ይኖራል

•በእርግዝና ወቅት በምጥ ሰአት ወይንም በውርጃ ጊዜ በተለይም ደግሞ ከወሊድ በሁዋላ በተለይም በመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንታት ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ የደም መርጋት ሂደቱን የሚያባብሱ ነገሮች አሉ፡፡ በተለይም...

•ከምጥ ጋር በተያያዘ የደም ስሮች መጎዳት፣

•በኦፕራሲዮን መውለድ ፣ •የሰውነት ውፍረት፣ •ተገቢውን አካላዊ እንቅስቃሴ ካለማድረግ ...ወዘተ ጋር በተያያዘ ወላድዋ የደም መርጋት ሕመም ሊገጥማት ይችላል፡፡ዶ/ር ሙሁዲን አብዶ እንዳብራሩት በአብዛኛው ጊዜ የደም መርጋት በሽታ ምክንያቱ የሚታወቅ እና ሊከላከሉት የሚቻል ሲሆን ከጥንቃቄ ጉድለት በርካታ እናቶችን ለጉዳት ሲዳርግ የሚታይ በእንግሊዝኛውም Silent killer (ዝምተኛው ገዳይ) እስከመባል የደረሰ ነው፡፡ በሽታው የሚከሰተው በአብዛኛው ደም መልስ በሚባለው የሰውነት ክፍል ሲሆን በይበልጥ የሚጀምረውም ከታችኛው የሰውነት ክፍል ከእግር አካባቢ እንዲሁም በማህጸን ዙሪያ አካባቢም የሚጀምር ሲሆን በተለይም ሂደቱ ወደሳምባ ወይንም ወደጭንቅላት በማለፍ በትናንሽ የደም ስሮች ላይ ጉዳት ሊያደርስ እና የመተንፈስ ችግር ብሎም የሞት አደጋ ሊያስከትል ይችላል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በማህጸን ውስጥ እና ዙሪያውን ባሉ አካላት ላይ በሚፈጠርበት ጊዜ ወደ እንግዴ ልጅ በማለፍ ጽንስንም ሊጎዳ የሚችልበት አጋጣሚ ይስተዋላል፡፡ የደም መርጋትን ሊያስከትሉ የሚችሉ ምክንያቶች ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል ውፍረት ፣እንቅስቃሴ አለማድረግ ፣መተኛት የመሳሰሉት ከላይ ተገልጸዋል፡፡ አንዲት ሴት በተለይም በኢትዮጵያ ስትወልድ ከሚደረግላት እንክብካቤ መካከል ምግብ ከለመደችው መጠንና አይነት በላይ መስጠት እና ለእረፍት መተኛት እንዳለባት ይነገራል፡፡ ይህንን ዶ/ር ሙሁዲን ይቃወሙታል፡፡ ‹‹...እንደባህል ሆኖ በኢትዮጵያ የወለደች ሴት መታረስ አለባት ከሚል አስተሳሰብ ብዙ እንድትተኛ ቅባት ያላቸውን ምግቦች ከመጠን በላይ እንድትመገብ ይደረጋል፡፡ በተለይም መኝታው እንደእረፍት የሚቆጠርበት መንገድ ትክክል አለመሆኑን መረዳት ይገባል፡፡ እረፍት ማለት መኝታ አይደለም፡፡ ማረፍ ማለት ሰውነት እንዳይንቀሳቀስ በማድረግ ለተለያዩ በሽታዎች እንዲጋለጥ ማድረግ ተብሎ ሊተረጎም አይገባም፡፡

ማረፍ ማለት ቀደም ሲል ከነበረው አስጨናቂ ነገር አእምሮን ገለል አድርጎ ጥሩ ጥሩ ነገር እያሰቡ አዲስ ስላገኙት ነገር በተለይም ስለወለዱት ልጅ ምቹ ነገርን እያሰቡ ቀድሞ ከነበረው ውጥረት የበዛበት የኑሮ እንቅስቃሴ እራስን ገለል አድርጎ በመጠኑ እየተንቀሳቀሱ ለተወሰነ ጊዜ እራስን ማደስ ተብሎ ቢታሰብ ይበጃል፡፡ ከወለዱ በሁዋላ መተኛት የሚለው እጅግ ጎጂ የሆነና የተሳሳተ አስተሳሰብ መሆኑን ሁሉም ቢረዳው መልካም ነው፡፡ ስለዚህ አንዲት ሴት ከወለደች በሁዋላ ለተወሰነ ጊዜ እረፍት አድርጋ በየአንድ እና ሁለት ሰአቱ ልዩነት ለአስራ አምስት እና ሰላሳ ደቂቃ ያህል ከአልጋ እየተነሳች ብዙ ሳትርቅ ከክፍል ክፍል ዞር ዞር ማለት እና አቅሙዋም በጨመረ ጊዜ በደንብ በቤቷ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ማለት ይጠበቅባታል፡፡

ወደምግቡ ሁኔታ ስንመለስም... በወለዱ ጊዜ የሚመገቡት ምግቦች ስብ እና ጣፋጭ የበዛባቸው እንዲሆኑ አይመከርም፡፡ ይልቁንም በፈሳሽ መልክ የተዘጋጁ ምግቦችን እንዲሁም መጠጦችን እየወሰዱ በወለዱ ጊዜ የሚሰሩ የአካል እንቅስቃሴዎችን በየደረጃው በባለሙያ ምክር መስራት ሊከሰት የሚችለውን የደም መርጋት ሊያስቀር ይችላል፡፡ በተለይም ኦፕራሲዮን ሆነው የወለዱ ሴቶች ከቁስሉ ጋር በተያያዘ የተለያዩ ምክንያቶችን ለራሳቸው እየፈጠሩ ፍርሀት ሰለሚያድርባቸው እራሳቸውን ከእንቅስቃሴ ሊገድቡ ስለሚችሉ የደም መርጋት ክስተቱን ሊያባብሱ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ማንኛዋም ወላድ የመጀመሪያዎቹን ስምንት ሰአታት ካረፈች በሁዋላ በየደረጃው የሰውነት ክፍሉዋን ማንቀሳቀስ ይጠበቅባታል...›› ብለዋል የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ሙሁዲን አብዶ፡፡ ይቀጥላል

Published in ላንተና ላንቺ
  • ሮበርት ዳውኒንግ ጁኒየር፤ 75 
  • ሚሊዮን ዶላር
  • ቻኒንግ ታተም፤ 60 ሚሊዮን ዶላር
  • ሂውጅ ጃክማን፤ 55 ሚሊዮን ዶላር
  • ማርክ ዎልበርግ፤ 52 ሚሊዮን ዶላር
  • ዘ ሮክ ወይም ድዋይን ጆንሰን፤ 46 
  • ሚሊዮን ዶላር
  • ሊያናርዶ ዲካርፒዮ፤ 39 ሚሊዮን ዶላር
  • አዳም ሳንድለር፤ 37 ሚሊዮን ዶላር
  • ቶም ክሩዝ ፤ 35 ሚሊዮን ዶላር
  • ዴንዘል ዋሽንግተን፤ 33 
  • ሚሊዮን ዶላር
  • ሊያም ኔሰን፤ 32 ሚሊዮን ዶላር

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትርን ላለፉት ሁለት አመታት በተጠባባቂ ሥራ አስኪያጅነት ሲመሩ በቆዩት አቶ ደስታ ካሳ ምትክ አርቲስት ተስፋዬ ሽመልስ የትያትር ቤቱ አዲስ ሥራ አስኪያጅ ሆኖ ተሾመ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ የተፈረመ የሹመት ደብዳቤ የደረሰው አርቲስት ተስፋዬ፤ ከሐምሌ 4 ጀምሮ ትያትር ቤቱን እንዲመራ በደብዳቤው ላይ ተገልጿል፡፡ መደበኛ ሥራውን ከመጀመሩ በፊትም ዘንድሮ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው በተሾሙት አቶ ሙልጌታ ሰኢድ አማካኝነት ከትያትር ቤቱ ሠራተኞች ጋር ተዋውቋል፡፡ በትያትር ፀሃፊነቱ የሚታወቀው አርቲስት ተስፋዬ፤ “ስንብት” እና “ሰማያዊ አይን” የተሰኙ ትያትሮችን ለመድረክ ማብቃቱ ይታወቃል፡፡
በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በጋዜጠኛነት የሰራው አርቲስቱ፤ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሸገር ኤፍኤም ሬዲዮ የአየር ሰአት ገዝቶ የራሱን ፕሮግራም ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡

የ“አለ ኪነጥበባት” ትምህርት ቤት ሰዓሊዎች ከ“ነፃ አርት ቪሌጅ” ጋር በመተባበር የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ስለ ሥዕል እና ቅርፃ ቅርፅ ያላቸው ግንዛቤ እንዲዳብር “ሰምና ወርቅ” የተሰኘ የጐዳና ላይ ትርዒት በማዘጋጀት የመነጋገርያ ሃሳብ አቀረቡ፡፡ ባለፈው ረቡዕ የቀረበው ዝግጅት በ”አለ ኪነጥበባት” ትምህርት ቤት ተጀምሮ ከአራት ሰአታት የከተማዋ ጉብኝት በኋላ የተጠናቀቀ ሲሆን አራት ኪሎ፣ ፒያሳ፣ ተክለሃይማኖት፣ ሜክሲኮ፣ ራስ መኮንን ድልድይ፣ መርካቶና ጃንሜዳን ያካተተ ነው፡፡ በጐዳና ትእይንቱ ሰዓሊ ታምራት ገዛኸኝ፣ ተስፋሁን ክብሩ፣ ዳንኤል አለማየሁ፣ ሙልጌታ ካሳ እና ለይኩን ናሁሰናይ እና ሌሎች ተሳትፈዋል፡፡ ረዳት ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን፣ ዶክተር ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ እና የውጭ አገር ኮሙኒቲ አባላት በክብር እንግድነት ተገኝተዋል፡፡

 

“የሰው ነገር” የተሰኘ አዲስ የሬዲዮ መዝናኛ ፕሮግራም ነገ በሸገር ኤፍኤም 102.1 እንደሚጀመር ማርቭል ፕሮሞሽን እና ኮሙኒኬሽን አስታወቀ፡፡ በየሳምንቱ እሁድ በ8 ሰዓት የሚቀርበውን ዝግጅት የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋዜጠኞች የነበሩት ሲሳይ ጫንያለው፣ ዘላለም ሙላቱ፣ ብስራት ከፈለኝና ስዩም ፍቃዱ እንደሚያቀርቡት ድርጅቱ አስታውቋል፡፡ “የሰው ነገር” በፊልም፣ በሙዚቃ፣ በሥነ ፅሁፍ፣ በስዕል እና ሌሎች የጥበብ ዘርፎች ላይ የሚያተኩር ሲሆን ፕሮግራሙ መዝናኛና ቁምነገርን በሚዛናዊነት እንደሚያቀርብ ተገልጿል፡፡

በፊልም ባለሙያው ተስፋዬ ማሞ ወንድም አገኘሁ የተፃፈው “የጨረቃ ጥሪ” ወንጀል ነክ ረዥም ልቦለድ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ ልቦለዱ ከ21 ዓመት በፊት የተፃፈ መሆኑን ደራሲው ገልጿል፡፡
በ1982 ለንባብ የበቃችው “ዕፀበለስ” የተሰኘች መፅሐፉ በአንባቢያን ዘንድ መወደዷ በፈጠረበት ግለት ተነሳስቶ “የጨረቃ ጥሪ” የተባለውን ሁለተኛ መፅሐፉን ቢፅፍም የህትመት ብርሃን ሳያይ መቆየቱን ተናግሯል፡፡
በኤችዋይ ኢንተርናሽናል ፕሪንቲንግ የታተመው ባለ 212 ገፅ ልቦለድ መፅሐፍ፤ ለኢትዮጵያ ገበያ በ50 ብር፣ ከኢትዮጵያ ውጭ ደግሞ በ15 ዶላር ይሸጣል፡፡ “ሉሲ ተሸጣለች” የተሰኘው ረዥም ልቦለድም ለንባብ የበቃው በዚህ ሳምንት ነው፡፡
በአንድነት አየለ ኃይሌ የተፃፈው ባለ 289 ገፅ መፅሐፍ፤ በአሀዱ ማተሚያ ቤት የታተመ ሲሆን ለሀገር ውስጥ በ44.96 ብር ፣ ለውጭ ሀገራት በ45 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡

ላለፉት 20 ዓመታት በሂፕሆፕ ሙዚቃ ከፍተኛ ተወዳጅነት እና ስኬት ባገኘው ራፐር ናስ ስም ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ፌሎውሺፕ ማቋቋሙን አስታወቀ፡፡ በሂፕሆፕ ሙዚቃ ታሪክ ያላቸውና ነባራዊ ገፅታን በረቀቀ መንገድ የሚያንፀባርቁ ሃሳቦችን በብዛት በመስራት ክብርና ዝና የተቀዳጀው ናስ፤ በሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ናስር ጆንስ ፌሎሺፕ ተቋቁሞለታል፡፡ ዌብ ዱ ቦይስ ኢንስቲትዩት እና ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ የሂፕሆፕ ክምችት ፌሎሺፑን የሚያስተዳድሩ ሲሆን የሂፕሆፕ ሙዚቃ ባህል፤ በታሪክ እና በፈጠራ ሂደት የሚኖረውን ሚና ለማጎልበት በሚል እንዲሁም ከሂፕሆፕ ጋር የተገናኘ የኪነጥበብ ትምህርት ለሚወስዱ ተማሪዎች ድጋፍ እንደሚሰጥበት ታውቋል፡፡ በሙሉ ስሙ ናስር ቢን ኦሉ ዳራ ጆንስ ተብሎ የሚታወቀው ራፕሩ፤ ባለፈው ዓመት “ላይፍ ኢዝ ጉድ” በሚል መጠርያ 11ኛ አልበሙን ለገበያ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡

*“የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ጉዞ” መፅሐፍ ለገበያ በቃ

“ጳጉሜ፣ የኢትዮጵያ ቀን መቁጠርያ የማን ነው?” የሚል መፅሐፍ ዛሬ ገርጂ በሚገኘው የዩኒቲ ዩኒቨርስቲ አዳራሽ እንደሚመረቅ አዘጋጁ አስታወቁ፡፡
የመፅሐፉ አዘጋጅ የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ፋሲል ጣሰው፤ የቀን አቆጣጠሩ የኢትዮጵያ ብቻ አይደለም የሚል መሟገቻ በመፅሐፋቸው ያቀረቡ ሲሆን ወርሃ ጳጉሜ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ማስገኘት አለባት በማለትም፣ ሠራተኞች ተጨማሪ ደመወዝ፣ የቤት አከራዮች የኪራይ ገንዘብ ጳጉሜን ታሳቢ በማድረግ ማግኘት እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡ በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ ዶ/ር አረጋ ይርዳውን ጨምሮ ሌሎች የሚድሮክ የሥራ ኃላፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ መፅሐፉ ለሀገር ውስጥ በ100 ብር፣ ለውጭ ሀገራት በ35 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡በሌላም በኩል “ነገር በምሳሌ” ቁጥር 1 መፅሐፍ በመጪው ሐሙስ በ10፡30 በብሉ በርድ ሆቴል ይመረቃል፡፡

አቶ አብርሃም ሐዲሽ ያዘጋጁት ባለ 103 ገፅ መፅሐፍ፤ የሥራ ባህል እንዳይዳብር መሰናክል ሆነው የቆዩ ልማዶችን ለመዋጋት የመፍትሄ ሀሳቦችን ያቀርባል፡፡ መፅሐፉ በ30 ብር እየተሸጠ ነው፡፡በፈለቀ ደምሴ (ኤርምያስ) የተዘጋጀው “የኢትዮጵያ እግር ኳስ ጉዞ” መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ በበርካታ መረጃዎች እና ፎቶግራፎች የተደገፈው ባለ 179 ገፅ መፅሐፍ፤ በፋርኢስት ትሬዲንግ የታተመ ሲሆን ዋጋው 47 ብር ነው፡፡ በመፅሐፉ የኋላ ሽፋን ላይ የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የቡና ክለብ ተጫዋች አሰግድ ተስፋዬ፣ ጋዜጠኛ ኢብራሂም ሻፊ አህመድ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ምክትል አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ እና የኢትዮጵያ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች አልፊያ ጃርሶ አስተያየታቸውን አስፍረዋል፡፡

ኦስካር ተሸላሚው ፎረስት ዊቴከር በመሪ ተዋናይነት የሰራበት አዲስ ፊልም ርእሱ ተኮርጇል በሚል መከሰሱን ሎስ አንጀለስ ታይምስ ገለፀ ፡፡ “ዘ በትለር” የተባለው የፊልሙ ርእስ እ.ኤ.አ በ1916 ዓ.ም ከተሰራ ድምፅ አልባ ፊልም የተወሰደ ነው የሚል ነው ክሱ፡፡ ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ በመላው ዓለም ለእይታ የሚበቃው ፊልሙ፣ በተመሰረተበት ክስ ከተሸነፈ ርእሱን ለመቀየር ይገደዳል፡፡ “በሲኒማው ኢንዱስትሪ ታሪክ ለ122 ጊዜያት ርእሶች ተደጋግመዋል፣ ተመሳስለው ተገኝተዋል” ይላል ፊልሙን የሰራው የዌይንስተን ኩባንያ ስራ አስኪያጅ - “ዘ በትለር” ፊልም ላይ የተለየ ነገር መነሳቱ አግባብ አይደለም በሚል ሲከራከር፡፡
በ25 ሚሊዮን ዶላር በጀት በዋርነር ብሮስ የተሰራው “ዘ በትለር”፤ ለስምንት የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች በአገልጋይነት ስለሰራ አንድ ጥቁር አሜሪካዊ የህይወት ታሪክ ያሳያል፡፡ ፎረስት ዊቴከር በዚህ አዲስ ፊልሙ ለኦስካር የሚያበቃ የትወና ብቃት ማሳየቱን የጠቀሰው ሎስ አንጀለስ ታይምስ፤ በዚሁ ፊልም ላይ ኦፕራ ዊንፍሬይ፤ ሊያም ኔሰን እና ሮቢን ዊልያምስ መተወናቸውን አመልክቷል፡፡ እ.ኤ.አ በ2006 “ዘ ላስት ኪንግ ኦፍ ስኮትላንድ” በተባለው ፊልም ላይ የኢድ አሚንን ገፀባህርይ በመጫወት በምርጥ ተዋናይነት ኦስካር የተሸለመው ፎረስት ዊቴከር፤ በተመሳሳይ የጎልደን ግሎብ እና የባፍታ ሽልማቶችንም ወስዷል - በምርጥ ተዋናይነት፡፡ የ52 ዓመቱ የፊልም ባለሙያ ከተዋናይነቱ በተጨማሪ በፊልም ፕሮዱዩሰርነትና ዳሬክተርነትም ይታወቃል፡፡

  • በዓለም ላይ 140 ሚ. ልጃገረዶች የግርዛት ሰለባ ናቸው
  • 92 ሚ. ያህሉ አፍሪካ ውስጥ ይገኛሉ

ሴት አያቷ ወደቤታቸው በመጡ ዕለት ጦንጤ ኢኮሉባ (Tonte Ikoluba) የ13 ዓመት ታዳጊ ነበረች፡፡ ያቺ ቀን ታዲያ ለጦንጤ የዕድሜ ልክ ፀፀት እንጂ የጥሩ ነገር ብሥራት አልነበረችም፡፡ ምክንያቷም አያቷ የመጡት ሊገርዟት ነበርና፡፡ 
የሴትነት ግማሽ አካሏ ተቆርጦ የተቀበረባትን ያቺን ዕለት በፍፁም አትዘነጋትም፤ ዛሬም ድረስ ድርጊቱ ትናንት የተፈፀመ ያህል ነው የምታስታውሰው፡፡ ዛሬ ግን ሳይንስና ቴክኖሎጂ ምሥጋና ይግባውና ለጦንጤና በብዙ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ ልጃገረዶችና ሴቶች ተስፋ ሰጪ የምሥራች የሆነ የሕክምና ጥበብ ብቅ ብሏል፡፡ ምሥራቹን ላቆየውና ወደ ጦንጤ ታሪክ ልምራችሁ፡፡ አያቷ፣ “የሚደረግላት ግርዛት፣ የተከበረች ሴት እንድትሆን፣ በጓደኞቿ ፊት እንዳታፍርና ወደፊት ደግሞ ባል የማግኘት ዕድሏን ከፍ እንደሚያደርግላት፤ እንዲሁም፤ በጣም ጠቃሚ ነገር ስለሆነ የሚያስጨንቅና የሚያስፈራ ነገር የለም” በማለት ጐጂ ልማዳዊ ድርጊት እንዲፈፀሙባት አግቧቧት፣ አባባሏት፣ አሳመኗት፡፡
ጦንጤ፣ በዚያች ዕለት ስለሆነችው ነገር መናገር አትፈልግም፡፡ ምክንያቱም ትዝታዋ በጣም መራርና የሚያሳምም ነው፡፡ ከዚያ በፊት በታላቅ እህቷ ላይ ተመሳሳይ የጭካኔ ድርጊት ተፈጽሞ በጣም ብዙ ደም ስለፈሰሳት ማላዊ ሆስፒታል ተወስዳ ደም ተሰጥቷት እንደነበር ስለምታውቅ በጣም ፈርታ ነበር፡፡ ግን ምንም ማድረግ አልቻለችም - ምስኪን ታዳጊ!
የዓለም ጤና ድርጅት፣ ግርዛትን፣ “የሴት ብልትን ውጫዊ አካል (ከንፈር) ግማሽ ወይም በሙሉ ማንሳት፤ ምንም የሕክምና ጥቅም ለሌለው ነገር በሴት ብልት ላይ የሚፈፀም ማንኛውም ዓይነት ጉዳት” በማለት ይገልፀዋል፡፡
የሴት ልጅ ግርዛት የተለያዩ ማኅበረሰቦች ሴትን ልጅ “በጨዋነት” ለማሳደግ ይጠቅማል ብለው የሚያምኑበትና ለረዥም ዘመናት የዘለቀ ጐጂ ባህላዊ ልማድ ነው፡፡ በዓለም ጤና ድርጅት ሪፖርት መሠረት፤ በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም 140 ሚሊዮን ልጀገረዶችና ሴቶች የዚህ ጐጂ ባህል ሰለባ ናቸው፡፡ 10 ዓመትና ከዚያም በላይ ዕድሜ ካላቸው የድርጊቱ ሰለባዎች መካከል 92 ሚሊዮን ያህሉ አፍሪካውያን መሆናቸውን ሪፖርቱ ጨምሮ አመልክቷል፡፡
የሴት ልጅ ግርዛት ድርጊቱ እንደተፈፀመና በረዥም ጊዜም የሚያስከትለው የጤና ጉዳት በርካታ ነው ይላሉ - በካሊፎርኒያ የሳን ማቴዎ የማህፀን ስፔሻሊስት ዶ/ር ማርሲ ቦወርስ፡፡ እንደ ጦንጤ ሁሉ በርካታ ሴቶች ከተገረዙ በኋላ ለዓመታት ይሰቃያሉ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ግርዛቱ ጥሎባቸው የሚያልፈው ተጽእኖ፣ ፍርሃት ስለሚፈጥርባቸውና ቁስሉም በየጊዜው ስለሚያመረቅዝ እንደሆነ ዶ/ር ቦወርስ ይናገራሉ፡፡ የሐኪሟን ሐሳብ ጦንጤም ትጋራዋለች፡፡ ጦንጤ በአሁኑ ወቅት የ35 ዓመት ሴት ናት፡፡ ይሁን እንጂ ግርዛቱ በፈጠረባት ተጽእኖ ትዳር አልመሠረተችም - ሴተ ላጤ ናት፡፡ ምክንያቱም ሕመሙ ቋሚ ነው ትላለች ጦንጤ፡፡ ስለዚህም ማንም ሰው ቢሆን ብልቷ አካባቢ እንዲደርስ አትፈቅድለትም - ሐኪም እንኳ ቢሆን፡፡
ዶ/ር ቦወርስ፤ ሕመም፣ የበርካታ በሽተኞቻቸው ዋነኛ ችግር መሆኑን ለ”አፍሪካ ሪነዋል” መጽሔት ገልፀዋል፡፡ “የአብዛኞቹ ሕሙማን፣ የሴት ልጅ ከፍተኛው የወሲብ ስሜት ኅዋስ የሆነው ቂንጥር (Clitoris) በሚሰቀጥጥ ሁኔታ ተቆርጧል፡፡ ይህ ብቻም አይደለም፡፡ ለሽንትና ለወር አበባ መውጪያ፣ ለግብረ ሥጋ ግንኙነትና ለልጅ መውለጃ ትንሽ ቀዳዳ ብቻ አስቀርቶ፣ ሁለቱ ከንፈሮች ተስበውና ተወጥረው ብልትን እንዲሸፍኑ ተደርገው ይሰፋሉ” ይላሉ፡፡
ሐኪሟ ሴቶቹ የተስተካከለ ሕይወት እንዲመሩ ለበሽተኞች የግርዛት ተቃራኒ የሆነ “Reversal surgery” የሚሠሩ የሴት ብልትና ቂንጥር ጠጋኝ ቀዶ ሐኪም ናቸው፡፡ በግርዛቱ ምክንያት በቂንጢር አካባቢ የሚፈጠረውና ስፍራውን የሚሸፍነው ኅዋስ ጠባሳ፣ ለቀዶ ሕክምና ምቹ አይደለም፡፡ ነገር ግን የብልታቸው ከንፈሮች ተወጥረው የተሰፉትን ሴቶች፣ ስፌቱን በመተርተር፣ ከተሰፋበት ጊዜ አንስቶ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ችግር እንዲሸኑና የወር አበባ እንዲፈሳቸው ማድረግ ይቻላል፡፡ እንዲሁም ሳይሰቀቁ ወሲብ መፈፀምና ልጅም መውለድ ይችላሉ፡፡
ቀዶ ሕክምናው የበሽተኞቹን ስቃይ በማስቀረት ረገድ መቶ ፐርሰንት ውጤታማ መሆኑን ሐኪሟ ተናግረዋል፡፡ “እነዚህ ሴቶች ቀዶ ሕክምናውን ሲያደርጉ የሚደሰቱበት ዋነኛው ምክንያት ከስቃይና ከጭንቀት የሚገላግል እፎይታ ስለሚሰማቸው ነው” ብለዋል ዶ/ር ቦወርስ፡፡
የተገረዙ ሴቶችን እንደገና የመጠገን ቀዶ ሕክምና (Reconstructive surgery) ከተጀመረ ረዘም ያለ ጊዜ አስቆጥሯል፡፡ ነገር ግን ቂንጥር እንደገና የመጠገን ቀዶ ሕክምና በፈረንሳዊው የሽንትና የፊኛ ስፔሻሊስት (Urologist) በዶ/ር ፒየር ፎልዴ እ.ኤ.አ በ2004 ዓ.ም የተጀመረ ነው፡፡ ዘዴው፣ ጠባሳውን ህዋስ በመክፈት ከስር የተቀበሩትን የነርቭ ህዋሳት ከጤነኛ ህዋሳት ጋር በማያያዝ ጠባሳው ስፍራ፣ አዲስ ጤነኛ ህዋስ እንዲያቆጠቁጥ ማድረግ ነው፡፡ አዲሱ ዘዴ፣ በግርዛቱ የተነሳ የሚመጣውን የማመርቀዝ ሕመም ይቀንሳል፡፡ ከዚህም በላይ ሴቶቹ፣ የወሲብ እርካታ መልሰው እንዲያገኙ ከማስቻሉም በላይ አንዳንድ ሴቶች ይህንኑ ከፍተኛ የእርካታ ስሜት (Orgasm) ማጣጣም ችለዋል፡፡
ዶ/ር ፎልዴ፤ በርካታ ቀዶ ሐኪሞች ባሰለጠኑበት ቡርኪናፋሶ ደግሞ ሕክምናው ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ ነው፡፡ ቀደም ሲል በ2001 መንግሥት አጠቃላይ ሆነ የሴት ብልት ቀዶ ሕክምና (Repair) ጀምሮ እንደነበር ብሔራዊው ፀረ-ግርዛት ኮሚሽን ሪፖርት አመልክቷል፡፡ በዚሁ ወቅት በአፍሪካ የቂንጥር ጥገና ቀዶ ሕክምና ያለምንም ችግር በቀላሉ ተደራሽ እንዲሆን ሰባት የቀዶ ሕክምና ባለሙያዎች በሴኔጋል ዳካር በዶ/ር ፎልዴስና የማናንጃይት ዕጢ ካንሰር ባለሙያ (oncologist) በሆኑት ሴኔጋላዊው ዶ/ር አብዱል አዚዝ ካሴ ሠልጥነው በቅርቡ ሰርቲፊኬት ተቀብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ተመሳሳይ ሥራ ላይ የተሰማሩ ዶ/ር ቦወርስ፤ የዶ/ር ፎልዴ ተማሪ ነበሩ፡፡ ለጦንጤ ኢኮሉባ የቀዶ ሕክምና በነፃ የሠሩትም እኚሁ ሐኪም ናቸው፡፡ እንዲሁም ተመሳሳይ ችግር ላለባቸው ሴቶች ከሚበረከተው ከእያንዳንዱ ድጋፍ እኩል ከራሳቸው ገንዘብ ለመስጠት ቃል ገብተዋል፡፡ ይህ ብቻም አይደለም፡፡ ከዓለም አቀፉ ፀረ-ሴት ልጅ ግርዛት ዘመቻ ኔትዎርክ ጋርም በመተባበር፣ ቀዶ ሕክምናው በሁሉም የአፍሪካ አገራት እንዲዳረስ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡
የፀረ-ሴት ልጅ ግርዛት ዘመቻ ኔትዎርክ የተቋቋመው እንዲህ ነው፡፡ የሴት ልጅ ግርዛት በሚፈጽሙ ማህበረሰቦች ከወሊድ ጋር በተያያዘ የሚሞቱት ሕፃናትና እናቶች ቁጥር በጣም ከፍተኛ ሆነ፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ በአፍሪካ የሴት ሐኪሞች ቡድን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሴት ልጅ ግርዛት ዘመቻ ኔትዎርክ ከዛሬ 15 ዓመት በፊት በ1998 ዓ.ም አቋቋሙ፡፡ ድርጅቱ፣ በኒውዮርክም ፀረ-ሴት ልጅ ግርዛት ዘመቻ እያካሄደ ነው፡፡ ምነው? የሥልጣኔ ባለቤት በሆነችው አሜሪካም እንዲህ ያለው ነገር ይፈፀማል? እንዳይሉ፡፡ ምክንያቱም የሴት ልጅ ግርዛት ከሚፈጽሙ ማኅበረሰቦች ወደ አሜሪካ የሚገባው የሕዝብ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ነው፡፡
ዓለምአቀፉ ኔትዎርክ በደቡባዊ ናይጄሪያ በምትገኘው ሃርኮት ወደብ ግርዛት ለተፈፀመባቸው ሴቶች ቀዶ ሕክምና የሚያደርግ ሆስፒታል እያሠራ ነው፡፡ የሆስፒታሉ ግንባታ ሲጠናቀቅ Restoration Hospital ተብሎ የሚሰየም ሲሆን፣ ከምዕራብ አፍሪካ ወደ ሆስፒታሉ የምትሄድ ማንኛውም የግርዛት ሰለባ የሆነች ሴት ቀዶ ሕክምናው በነፃ ይሠራላታል፡፡ “በአሁኑ ወቅት ቀዶ ሕክምናውን ለማግኘት ተመዝግበው የሚጠባበቁ 400 ሴቶች አሉን፡፡ እኛ ለቅቀን ስንሄድ ሕክምናውን በነፃ የሚሰጡ የአገር ውስጥ ሐኪሞች እያሰለጠን ነው” ያሉት አሜሪካ ያለው የኔትዎርኩ ቅርንጫፍ ዳይሬክተር ዶ/ር አበሪ ኢኪንኮ ናቸው፡፡
ዳይሬክተሩ አያይዘውም፤ በአፍሪካ ያሉ አብዛኞቹ ሴቶች ለቀዶ ሕክምናው መክፈልም ሆነ ብዙ ርቀት ተጉዘው መታከም አይችሉም፡፡ ስለዚህ፤ ለሆስፒታሉ እውን መሆን ለሚያስፈልግ አቅርቦትና ዝግጅት ገንዘብ በኒውዮርክ ተሰብስቦ ወደ ናይጄሪያ ይላካል፡፡ የድርጅቱ ተስፋ የሆነው “ሪስቶሬሽን ሆስፒታል”፣ በግርዛት ሳቢያ ብዙ ቀናት በማማጥ የሚከሰተውን ፌስቱላ ጨምሮ ሌሎች የብልት ሕክምናዎችንም ለሴቶች በነፃ ይሰጣል ብለዋል፡፡
በ2012 ዓ.ም በከፍተኛ ባለሥልጣናት ደረጃ የተካሄደው የተባበሩት መንግሥታት ደርጅት ጠቅላላ ጉባኤ፣ የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቀረት አገራት ቁርጠኝነታቸውን እንዲጨምሩና ተጨባጭ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ድርጅቱ የሴትን ግርዛት ለማስቀረት በመላው ዓለም ያስተላለፈው ጠንካራ ውሳኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀባይነት ያገኘው ኖቬምበር 26 ቀን 2012 ዓ.ም ነበር፡፡
ውሳኔው ተቀባይነት እንዲያገኝ የላቀ ሚና የተጫወቱት የመጀመሪያዋ የቡርኪናፋሶ ሴት ቻንታል ኮምፓዎሬ፤ የአፍሪካ አገራት ውሳኔውን ተቀብለው እንደሚፈርሙና ክልከላውንም በኃላፊነት እንደሚያስፈፅሙ ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል፡፡
የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቀረት ዓለም አቀፍ ጥረት ከተጀመረ ከሁለት አሥርት ዓመታት በኋላ፣ እነሆ አሁን ብዙ ማኅበረሰቦች ለውጡን እየተቀበሉት ነው፡፡ በ2011 በአፍሪካ ብቻ ሁለት ሺህ የሚጠጉ ማኅበረሰቦች፣ ግርዛቱ የሚያስከትለውን ጉዳት በመገንዘብ፣ ሴት ልጆቻቸውን ከማስገረዝ ታቅበዋል፡፡ የሴት ልጅን ግርዛት የሕዝብ ጤና ጉዳይ በማድረግና አንዳንድ ጊዜም በወጣት ልጃገረዶችና ሴቶች ላይ እስከ ሞት የሚያደርስ ጐጂ ባህላዊና ልማዳዊ ተጽእኖ መሆኑን በማሳየት የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችና ግለሰቦች እየበረከቱ በመምጣታቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ችግሩን ለማስቀረት የሚደረጉ ትምህርታዊ ጥረቶች ተቀባይነት እያገኙ ነው፡፡
ግርዛትን ለማስቀረት ዓለም አቀፍ ተስፋ ቢኖርም፤ እስካሁን ድርጊቱ ለተፈፀመባቸው በብዙ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ ልጃገረዶችና ሴቶች መፍትሔ ለማፈላለግ የተሰጠው ትኩረት በጣም አናሳ ነው፡፡ ግርዛትን እንደገና የማስተካከሉ ቀዶ ሕክምና (ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ) እንደ ጦንጤን ላሉ ወጣት ሴቶች፣ “ከእግዜር የተላከ” የተራቀቀ ሳይንሳዊ የሕክምና ጥበብ ውጤት ነው፡፡ “የሴትነት ግማሽ አካሌን ቆርጠው ወስደውብኛል፡፡ ያንን አካሌን በማጣቴ በጣም ይሰማኛል፡፡ እንደገና ሙሉ አካል ያላት ሴት መሆን እፈልጋለሁ” ብላ ነበር ጦንጤ፡፡ የተመኘችው ስለተሳካላት እንኳን ደስ ያለሽ! ልንላት ይገባል፡፡ የዚህ ጐጂ ባህልና ልማድ ሰለባ ለሆኑ በብዙ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ልጃገረዶችና ሴቶች፣ አዲሱ የማስተካከያ ቀዶ ሕክምና መፍትሔ ይሆን ይመስለኛል፡፡ ያገራችን ሴት ሐኪሞች፣ በፀረ ግርዛት ዙሪያ የምትንቀሳቀሱ ድርጅቶች፣ ግለሰቦችና መንግሥት፣ ምን ትላላችሁ?

 

Published in ዋናው ጤና
Page 5 of 13