Administrator

Administrator

ስብሐቲዝም የሀሳብ ውይይት የፊታችን እሁድ ሚያዝያ  20 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት(ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

"የሕላዌ እንቆቅልሽ " የተሰኘ መጽሐፍ ነገ ይመረቃል

የደራሲ ማንደፍሮ ማሩ "የሕላዌ እንቆቅልሽ" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ቅዳሜ ሚያዝያ 19 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ ይመረቃል።

በደራሲ ባየህ ንጉሴ የተዘጋጀው “ፋሽን” የተሰኘ በፋሽን እና ሞዴሊንግ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መጽሐፍ ቅዳሜ ሚያዝያ 19/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ጥሪ የተደረገላቸው
የጥበብ ቤተሰቦች እና እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል ይመረቃል።በስድስት ምዕራፍ የተከፈለው መጽሐፉ ስለ ሞዴሊንግ አይነቶች፣ ሞዴል የመሆን ትሩፋቶች እና ተግዳሮቶች፣ የቁንጅና ውድድር፣ ሻምፖ እና ኮድሽነር አመራረጥ፣ ፖርትፎሊዮና ሌሎችም ዝርዝር ጉዳዮችን ይዟል።

ዘመን ባንክ የሠራተኞቹን ዕውቀትና ክህሎት ለማሳደግ፣ በዓለም  ትልቁ የኢንተርኔት የመማሪያ መድረክ ከሆነው ሊንክድኢን ሊርኒንግ ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ፡፡

የዘመን ባንክ የሰው ሀብት ምክትል ዋና ኦፊሰር አቶ ታከለ ዲበኩሉ ስለ ስምምነቱ ሲገልጹ፤ “ዘመን ባንክ ለሰራተኞቹ ቀጣይነት ያለው የመማርና የሙያ እድገት ባህልን ለማሳደግ ቁርጠኛ ነው። ከሊንክድኢን ለርኒንግ ጋር ያደረግነው ስምምነት፣ ይህንን ቁርጠኝነት የሚያጎላ ከመሆኑም በላይ ሠራተኞቻችን በፋይናንስ ዘርፉ የሚጠይቀውን ችሎታ፣ እውቀትና ክህሎት እንዲያሳድጉ የሚረዳ ነው፡፡" ብለዋል፡፡

የሊንክድኢን ታለንት ሶሉዩሽን ዋና ኃላፊ ማቲው ግሬይ በበኩላቸው፤ ”ከዘመን ባንክ ጋር ያደረግነው ስምምነት የሰራተኞቹን የክህሎትና የእውቀት ክፍተቶችን ለማሟላት እድሉን የሚሰጠን ከመሆኑም በላይ ሊንክድኢን ለርኒንግ በአፍሪካ ተመራጭ የክህሎት ልማት መድረክ ሆኖ  መቀጠሉን ስለሚያሳይ እጅግ ተደስተናል። የዘመን ባንክ የሰው ሃብት ስትራቴጂ በቀጣይ አመታት ይበልጥ እንዲጎለብትና ውጤታማ እንዲሆን አብረን እንሰራለን።" ብለዋል፡፡

የእነዚህ ኮርሶች ወጪ ሙሉ በሙሉ በዘመን ባንክ የተሸፈነ ሲሆን፤ የባንኩ ሠራተኞች ሥልጠናውን  በነፃ እንደሚያገኙ  ታውቋል፡፡

ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ግማሽ ሚሊዮን (500ሺህ) ብር፣
ድምፃዊ ዳዊት ፅጌ 100ሺ ብር በመስጠት ጀምሯል ደጋግ ኢትዮጵያውያኖች የአቅማችሁን በማድረግ የትዕግስት ሶስት መንታ ልጆች የአይን ብርሃናቸው እንዲመለስ የበኩላችንን እናድርግ።
ሼር በማድረግ እንጀምር!
አካውንታቸው ይህው እባካችሁ
ሼር አድርጉት
* СВЕ 1000622473872
* Dashen Bank 5563671317021
* Abyssinia bank 91613069
* ኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ 1023500172828
* አዋሽ ባንክ 013471254339600
ትግስት ካሳ ቀፀላ
ስልክ
* 0911868306
* 0911137097
go fund me
ይህን ሼር ማድርግ መልካም ነገር መስራት ነውና እባካችሁ ሼር አድርጉላቸው
• ገዳሙን ለመታደግ ቅዳሜ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ይካሄዳል
ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል የአንድነት ገዳም በ1574 የተመሰረተና የጻዲቁ አባት አቡነ ሐራ ድንግል ገድልና ገቢረ ተዓምራት የሚካሄድበት ገዳም ነው - ይላሉ የገዳሙ መነኮሳት፡፡
ከ400 ዓመት በላይ ታሪክ ያለው ይህ ትልቅ ገዳም በሰሜን ጎጃም፣ ባህርዳር ዙሪያ የሚገኝ ሲሆን፣ ጻዲቁ አቡነ ሐራ ድንግል፣ ከፈጣሪያቸው በተገባላቸው ቃልኪዳን መሠረት፣ ደዌን ሲፈውሱና ተዓምራትን ሲሰሩ የቆዩበትና አሁንም የሚሰሩበት ጥንታዊ ገዳም መሆኑን፣ የገዳሙ ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ያወጣው መግለጫ ይጠቁማል፡፡
ይሁን እንጂ ይህ ገቢረ ተዓምር የሚሰራበት ታሪካዊ ገዳም፣ ትልቅ ችግር እንደተጋረጠበት መነኮሳቱ ተናግረዋል፡፡
“ለፈውስና ለድህነት ከመላው አገሪቱ ወደ ገዳሙ የሚመጡ ምዕመናን ድህነትና ፈውስ ካገኙ በኋላ፣ ገዳሙን ተጠግተው ቤት በመሥራት እዚያው እየኖሩ፣ ገዳሙ ይዞታውን እየተነጠቀ ከመጣበቡም በላይ፣ የገዳሙን ቅድስና የሚያረክሱ ተግባራት እየተፈጸመበት ይገኛል፡፡” ይላል፤ የኮሚቴው መግለጫ፡፡
የገዳሙ መነኮሳት የታሪክ ዶሴና ማስረጃ ላይ ተንተርሰው እንደሚናገሩት፤ ዓጼ ዮሐንስ በነቀርሳ ተይዘው በአቡነ ሐራ ድንግል ጸበል በመዳናቸው ነበር ለገዳሙ የአንድ ሰዓት የእግር መንገድ ያህል ስፋት ያለው ቦታ ለገዳሙ የሰጡት፡፡ ደርግ ሥልጣን ሲይዝ በገዳሙ 800 የሚደርሱ መናንያን እንደነበሩ የሚያስታውሱት መነኮሳቱ፤ በወቅቱ “መሬት ላራሹ” የሚል አዋጅ በመታወጁ የገዳሙን ይዞታ አርሶ አደሮች እየተቆጣጠሩት እንደመጡና መናንያኑ ገዳሙን ጥለው መኮብለላቸውን ያስረዳሉ፡፡
በአሁኑ ወቅት በገዳሙ ይዞታ ላይ ከ250 በላይ አባወራዎች ሰፍረው እንደሚገኙ የሚገልጹት መነኮሳቱ፤ ይህን ችግር ለመቅረፍ ለመንግሥት በተደጋጋሚ አቤቱታ ካቀረቡ በኋላ፣ መንግሥት ነዋሪዎቹን አንስቶ ሌላ ቦታ ለማስፈር ፈቃደኛ ቢሆንም፣ ለነዋሪዎች ካሣ ለመክፈል በጀት እንደሌለው በመግለጽ፣ ገዳሙ ካሣውን እንዲከፍል መወሰኑን ይናገራሉ፡፡
ሆኖም የሚከፈለው ካሣ ከገዳሙ አቅም በላይ በመሆኑ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ አግኝቶታል የሚሉት የገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም የገቢ ማሰባሰቢያ ኮሚቴ አባላት፤ ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ስለ ገዳሙ አሁናዊ ሁኔታና ስለገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ ሊቃነ ጳጳሳት፣ የገዳሙ መነኮሳት፣ የቤተክህነት አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተነገረው፣ የአማራ ክልል ካቢኔ ለገዳሙ ሁሉንም ይዞታውን ባይሆንም 60 ሄክታር የሚደርስ መሬት እንዲመለስለት የወሰነ ሲሆን፤ ገዳሙ በበኩሉ ለአርሶ አደሮቹ የሚገባቸውን የመሬት ካሣ መክፈል ይጠበቅበታል፡፡
ይህን የመሬት ካሣ ለመክፈልና ለገዳሙ የማስፋፊያ ልማት ለማከናወን፣ የፊታችን ቅዳሜ ሚያዝያ 19 ቀን 2016 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል፣ በቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭት፣ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 6 ሰዓት የሚቆይ ዓለማቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር እንደሚያካሂድ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ለአርሶ አደሮቹ የመሬት ካሣውን ለመክፈልና የገዳሙ ይዞታ ከተለቀቀ በኋላ በሥፍራው ለሚከናወኑ ልማቶች በአጠቃላይ 100 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው የገለጸው የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴው፤ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተክርስትያን ልጆችና የጻድቁ አቡነ ሐራ ወዳጆች በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ላይ በንቃትና በትጋት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
በአሁኑ ወቅት በገዳሙ የሚገኙ መናንያን ቁጥር 5ሺ እንደሚደርሱና በጾም ወቅት የጸበልተኛው ቁጥር ከ50 ሺ በላይ መሆኑን የጠቆሙት የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ አባላቱ፤ እኒህን ሁሉ በአግባቡ የሚያስተናግድ በቂ መጠለያና የልማት ሥራዎች ማከናወን አስፈላጊ እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡
ለገዳሙ ድጋፍ ማድረግ የሚሹ ወገኖች፡-
በንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡- 1000610362463
በአባይ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡- 9221111060954312
እንዲሁም የዶላር ሒሳብ ቁጥር፡- 634110814 መለገስ ይችላሉ ተብሏል፡፡
እባክዎ!..አንድ የጎዳና ሰው የበዓል ምሳውን ይሸፍኑልን?
እኛ ስማችን ከዚህ በታች የተጠቀሰ ጋዜጠኞችና በጎ አድራጊዎች ሶሻል ሚድያን በመጠቀም ለመጪው የፋሲካ በዓል አስታዋሽ የለሾቹን የጎዳና ተዳዳሪ ወገኖች ምሳ በማብላት በዓሉን አብረን ለማሳለፍ አቅደናል። እርስዎም ከጎናችን ይሁኑ!..ከቻሉ አብረውን ያሳልፉ?..ቢያንስ የአንድ ሰው የምሳ ወጪ በመሸፈን አጋርነትዎን ይግለፁልን?!
መርሐግብሩን ለማዘጋጀት ያቀድነው በተለያዩ ምክንያቶች ጎዳና ለወጡ ወገኖች ቢያንስ አለኝታነታችንን ለመግለፅ እና በዓሉን ደስ ብሏቸው እንዲያሳልፉ በማሰብ ነው።
ከእርስዎ የምንፈልገው እገዛ ቢያንስ አንድ ሰው በመመገብ ዓላማችንን ደግፈው ከጎናችን እንዲቆሙ ነው።
የአንድ ሰው ምገባ ወጪ ግምት 500 ብር ነው። አቅምዎ ከፈቀደ ሁለትም ሶስትም ...ወገኖችን በመመገብ ከበረከቱ መቋደስ ይችላሉ።
የ 1 ሰው ምሳ ወጪ ለመሸፈን .................500 ብር
የ 3 ሰዎችን...ለምትሸፍኑ...1500 ብር
የ 6 ሰዎችን ...ለምትሸፍኑ.... 3000 ብር
የ 10 ሰዎችን.... ለምትሸፍኑ......5000 ብር
የ15 ሰዎችን ...ለመሸፈን...7500 ብር
የ20 ሰዎችን ....ለመሸፈን...10000 ብር
***
የምገባውን ዝርዝር መርሐግብር በቀጣይ የምናሳውቅ ይሆናል።
አሁን መላክ ጀምሩ?!...
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስላሴ ቅርንጫፍ
ሒሳብ ቁጥር
1000620235818...(ቴዎድሮስ፣ፍሬው እና አለምነሽ)
***ለተጨማሪ መረጃ አስተባባሪዎች
1.ቴዎድሮስ ካሳ(+251 98 900 0089)
2.ፍሬው አበበ (+251911617935)
3..አለምነሽ ኩምሳ (+25191 164 5458)
4.ቤቴልሄም ለገሰ (+251911335511)
5.ቆንጂት ሁሴን (+251911408541)
ሲያስገቡ ደረሰኙን መላክ አይዘንጉ!!
ማኀበራዊ ሚድያን ለበጎ ተግባር በመጠቀም ለውጥ እናመጣለን!!
እናመሰግንዎታለን!!
(በብርሃኑ በላቸው አሰፋ ፣ የ”ክቡር ልጆች” መጽሐፍ ደራሲ)
ዓለም አቀፍ የመጽሐፍ ቀን፤ የንባብ ባህልን ለማዳበር፣ ደራስያንንና አታሚዎችን ለማበረታታት ይከበራል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1995 ዓ.ም ነበር ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ የመጽሐፍ ቀን የተከበረው፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት ቀኑን የንባብ ልማድ እንዲዳብርና በተለይም ወጣቱን ትውልድ በማነቃቃት፣ የመረጃ ፍሰቱ በንባብ እንዲጎለብት ለማበረታታት በየዓመቱ ያስበዋል፡፡
በሀገራችንም ሀርመኒ ሂልስ ት̸ ቤት በትላንትናው ዕለት በተለያዩ ዝግጅቶች ቀኑን አክብሯል፡፡ ት̸ ቤቱ ደራሲያን መጽሐፍቶቻቸውን ለተማሪ ወላጆች እንዲያስተዋውቁ በማድረግ፣ የልጆች መጽሐፍ ደራሲያን ለተማሪዎች መጽሐፍ እንዲያነቡ በማድረግና የተማሪዎችና መምህራን መጽሐፍ የማንበብ ስነ ስርዓት በማካሄድ ዓለማቀፍ የመጽሐፍ ቀንን በድምቀት አስቦታል፡፡ በመርሃግብሩ ላይ የልጆች መጽሐፍ ደራሲ እምነቴ ድልነሳን ጨምሮ ሌሎችም ታድመዋል፡፡
የት̸ ቤቱ ዳይሬክተር ሩት መንበረ፣ ተማሪዎች የንባብ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ ታስቦ ቀኑን አክብረነዋል ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኤሌክትሮኒክስ የመጽሐፍ ንባብ ትልቁ ተግዳሮት በመሆኑ ልጆች በፍቅር እንዲያነቡ ምቹ ሁኔታን እየፈጠሩ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ልጆች እና መጻሕፍት
በቅርቡ የተካሄደ አንድ ጥናት እንዳመለከተው፤ ምንም እንኳን 70 በመቶ ወላጆች ማታ ማታ ለልጆች ጣፋጭ ታሪኮችን ማንበብ አስፈላጊነቱን ቢያምኑም፣ ግማሽ ያህሉ ብቻ ይተገብራሉ፡፡ ከአምስት ቤተሰቦች አንዱ ደግሞ በስራ ብዛት የተነሳ ለልጆች የማንበብ ልማድ የለውም፡፡
ይሁን እና ማምሻውን የሚነበቡ ተረቶች ምን ጥቅም አላቸው ?
በወላጅና በልጅ መካከል ያለውን ግንኙነት ያጠናክራሉ
የልጆችን የማንበብ ክህሎት ያዳብራሉ
የልጆችን የፈጠራ አቅም ያጎለብታሉ
የልጆችን የቃላት ችሎታ ያሳድጋሉ
የልጆችን የስሜት ብስለት ያዳብራሉ
የልጆችን የአእምሮ ጤና ያበለፅጋሉ
ለአካላዊ ጤንነት ምግብና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለአእምሮ እድገት ደግሞ ንባብ ወሳኝ ሚና አለው፡፡ ከመዋዕለ ህጻናት እስከ አራተኛ ክፍል ልጆች ለማንበብ መሰረታዊ ክህሎትን ይማራሉ፡፡ ከአራተኛ ክፍል ጀምሮ ደግሞ ለመማር ያነባሉ፡፡ የፔዳጎጂ ፅንሰ ሃሳብም ተማሪዎች በራሳቸው እንዲማሩና በቀላሉ እንዲገነዘቡ በማድረግ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የማንበብ ፍላጎትና ተነሳሽነት ይጠይቃል፡፡
መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ የልጆች የንባብ ክሂል ብቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ ነው፡፡ የሃገራችን ተማሪዎች የመጀመሪያ እርከን ሲጨርሱ ለምን ማንበብ ያዳግታቸዋል ? የተነበበላቸውን ለምን መረዳት ይቸግራቸዋል ? የሚሉት ጥያቄዎች መልስ ያሻቸዋል፡፡
ልጆች የማንበብ ልማድን እንዲያዳብሩ
በየቀኑ ማንበብ ማለማመድ
የስነ ልቦና ባለሙያዎች እንደሚሉት፤ በየቀኑ ለ20 ደቂቃ ተረት ማታ ማታ የሚነበብላቸው ልጆች፣ የአእምሮ ጤናቸው ከመጠበቁ ባሻገር የፈጠራ አቅማቸው ከፍ ያለ ነው፡፡
ወላጆች መጽሐፍትን በማንበብ አርአያ ሊሆኑ ይገባል
ምቹ የንባብ ከባቢ መፍጠር
ከልጆች ጋር ቤተ መጽሐፍት መጎብኘት
ልጆች የሚፈልጉትን መጽሐፍ እንዲመርጡ እድል መስጠት
ልጆች ደስ የሚላቸውን መጽሐፍ ደጋግመው እንዲያነቡ ማበረታታት ይገኙበታል፡፡


*በኤክስፖው ከ30ሺ በላይ ለሚሆኑ ጎብኚዎች  ነጻ የህክምና  ምርመራ ይሰጣል

አፍሮ-ኤዥያ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ፣ እዚህ አዲስ አበባ በኤግዚቢሽን ማዕከል፣ ከግንቦት 9-11 ቀን 2016 ዓ.ም ለሦስት ቀናት  ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በኤክስፖው ላይ ከ400 በላይ የአገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች፣ ከ30ሺ በላይ ጎብኚዎችና  ከ2ሺ በላይ የጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች  ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

የጤና ኤክስፖውን አስመልክቶ አዘጋጆቹና አጋር ተቋማት  ዛሬ ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ላይ በራማዳ  ሆቴል የሚዲያ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት  ሰፊ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡



በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተመለከተው፣ በጤና ኤክስፖው  ላይ የፓናል ውይይቶች፣ ዎርክሾፖችና ኤግዚቢሽኖችን ጨምሮ በርካታ ኹነቶች ይቀርባሉ፡፡ የጤና ባለሙያዎች የልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበትና የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር የሚካሄድበት እንዲሁም የትስስርና የትብብር ዕድሎች የሚፈጠርበት  መድረክ እንደሚኖርም ተጠቁሟል፡፡

ኤክስፖው በጤና አጠባበቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የህዝብ ጤናን፣ ፋርማሲዩቲካልስን፣ የህክምና ቴክኖሎጂንና ሌሎች በርካታ ርዕሰ ጉዳዮችንና ዘርፎችን እንደሚሸፍን የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ ሁሉን አቀፍ አቀራረብም ተሳታፊ ድርጅቶችና ጎብኚዎች በተለያዩ መስኮች ከአዳዲስ ዕድገቶችና ፈጠራዎች ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል ይፈጥራል ተብሏል፡፡

“ድልድዮችን እንገንባ፣ ህይወትን እናድን” በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ፤ ከ30ሺ በላይ ለሚሆኑ ጎብኚዎች ነጻ የጤና ምርመራ የሚከናወን ሲሆን፤ ለጤና አጠባበቅ  ባለሙያዎችም ነጻ ሥልጠና እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡

ለሦስት ቀናት በሚቆየው የአፍሮ- ኤዥያ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ ላይ ከህንድ፣ ዱባይ፣ ታይላንድ፣ ቱርክ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ማላይዥያና ሌሎችም አገራት የተውጣጡ በጤና ላይ የሚሰሩ ተቋማትና ባለሙያዎች እንደሚሳተፉበት ተጠቁሟል፡፡

ኤክስፖው ከወትሮው በተለየ በቢዝነስ ላይ ብቻ የሚያተኩር ሳይሆን፣ ተቋማት ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለመወጣት ልዩ ዕድል የሚያገኙበት እንደሆነም ተነግሯል፡፡

ይህን ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ ኤፍዚ ማርኬቲንግና ኮምዩኒኬሽን ኃ.የተ.የግ. ማህበር ከሰላም ኸልዝ ኮንሰልታንሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን፤ ሳልማር ኮንሰልታንሲ፣ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር፣ የኢፌዲሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን እንዲሁም የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በአጋርነት እንደሚሳተፉበት ታውቋል፡፡

For more than 3,000 years, the Jewish people have reenacted their journey to freedom during the Passover festival, as they joyously celebrate the Children of Israel's exodus from slavery in Egypt to a life of liberty and independence in the Land of Israel.

This holiday’s message can resonate with people of diverse backgrounds and beliefs, as it emphasizes the universal yearning for personal and collective freedom. Always coming just before the Ethiopian and other Eastern Christians’ celebrations of Fasika/Easter, the Passover holiday is one part of a larger holiday season which touches us all, Israelis and Ethiopians alike.

This year, however, our joy is tinged with sadness. As Israeli families gather for the traditional Seder meal, the Passover dinner will be accompanied by sorrow for our fallen soldiers and civilians, prayers for the recovery of the wounded, and expressions of solidarity with the tens of thousands of displaced Israelis who cannot return to their homes. Many families will set an empty place at their Passover table to symbolize our longing for the release of the 133 men, women and children still being held hostage in Gaza in the most horrific conditions imaginable.

Since October 7th, Israel has been confronted with brutal attacks and existential threats emanating from the Iranian regime and its many proxies, from Hamas in Gaza to Hezbollah in Lebanon, through the Houthis in Yemen to other militias and terrorists in Syria and Iraq. These self-declared enemies of the Jewish state openly threaten Israel with complete annihilation. More ominously, they have not hesitated to try and turn their malevolent aspirations into reality, as recently demonstrated by Iran's massive missile and drone attack and Hamas' massacre of 1,200 Israelis on 7 October.

Despite the resounding success in repelling Iran's attack on 14 April, realized with the extraordinary cooperation of the US and Israel’s allies in Europe and the region, as well as the exemplary military accomplishments made in the fight against Hamas in the Gaza Strip, the war is not yet over. Much remains to be done, including the restoration of deterrence against the Ayatollahs' regime and its proxies. This step is essential to preventing additional direct attacks on Israel, and also to stopping the spread of the Islamic revolution worldwide, Iran's efforts to become a nuclear power, and its ballistic missiles program.

A key element is the designation as a terrorist organization of the Iranian Revolutionary Guard Corps (IRGC) - which is a primary pillar of support of the regime and the spearhead of its repressive policies in Iran and aggressive actions abroad.
This war is not only about Israel. It is a combat waged with our allies to protect our shared values and the freedoms we hold so dear.

Jewish history is the story of prevailing, of a people that overcomes obstacles and challenges against all odds. The age-old longing to return to the Jewish homeland, as expressed every Passover with the words “Next year in Jerusalem," inspired generation after generation with the dream of becoming again a free people in the Land of Israel.
Alongside freedom, Passover bears a powerful message of resilience and optimism. This year too, despite the present situation, we will be strengthened by our heritage and will look forward towards the future with faith and hope.

Israel must fight to protect its citizens and their liberty against murderous aggressors. However, we will not abandon the struggle to live in peace and coexistence with other peoples of goodwill in our region.

May the festivals of Passover and Fasika bring Israel and Ethiopia – our countries and peoples – many blessings of health, peace and prosperity.

Page 1 of 703