Administrator

Administrator

                                       መልክአ ኢትዮጵያ - ፲፬

የቺካጎ ቆይታዬ የመጨረሻዋ ምሽት ላይ ነኝ። በዚህች ምሽት ከፍ ያለ ስምና ዝና ባለው ‹‹ካዲላክ ፓላስ›› (Cadillac Palace) ቴአትር ቤት ከታደሙት በሺሕ ከሚቆጠሩ ተመልካቾች አንዷ ኾኛለኁ። ተውኔቱ ሚልዮኖች በቴአትርና ሲኒማ ቤት ደጃፍ ተሰልፈው ላለፉት ኻያ ስምንት ዓመታት የተመለከቱትና የቪክቶር ሁጎ ድርሰት የኾነው ሌስ ሚዝራብልስ (Les Miserables) ሙዚቃዊ ብሮውዌይ ቴአትር ነው፡፡ የቤቱ አስተናባሪዎች በአክብሮት የሰጡኝን፣ ስለ ተውኔቱና ተዋንያኑ የተሟላ መረጃ የያዘውን የቴአትር ቤቱን ባለቀለም መጽሔት እያገላበጥኩ በተሰጠኝ የወንበር ቁጥር መሠረት ቦታዬን ይዣለኹ፡፡ በቴአትር ቤቱ ውበት የተማረክኹት ገና ከመግቢያው ጀምሮ ነበር፡፡ ከሰማንያ ሰባት ዓመታት በፊት በ12 ሚልዮን ዶላር ወጪ የተገነባው የቺካጎው ‹‹ካዲላክ ቴአትር››÷ አዝናንተው በሚያስቀምጡ፣ ምቾት ባላቸው መቀመጫዎቹ 2400 ተመልካቾችን ክትት ያደርጋል፡፡ ቴአትር ቤቱ በየጊዜው በሚደረግለት እድሳትና የውስጥ ማሻሻያ ዲዛይን ለውጥ ወደር የሌለው የሥነ ሕንጻ ውበት ተላብሷል፡፡ በአዳራሹ ውበት በመመሠጤ የተውኔቱ በሰዓቱ አለመጀመር ብዙም ግድ አልሰጠኝም፡፡ የውስጠኛውን ክፍል ጣሪያ ለማየት ቀና ያደረግኁትን አንገቴን፣ ምን አንገቴን ብቻ ክሣደ ልቡናዬን፣ እዚያው ተክዬው ቀርቻለኹ፡፡

ዲዛይኑ በአንድ ሰው ወይም በአንድ ወቅት የአእምሮ ፈጠራ ውጤት ብቻ መሠራቱ አጠራጣሪ ነው፤ ተጠበውበታል፤ ተጨንቀውበታል፡፡ ስፋቱ፣ የወንበሮቹ አደራደር፣ በመድረኩ ላይ የወረደው መጋረጃ ግርማ ሞገስ ተኩረው፣ ቆፍረው እንዲያዩት ያገብራል፡፡ የተገጣጠሙት ቁሳቁሶችና የተቀባው ቀለም ሕብሩ፣ ሥነ ርእዩ ውብ ነው ከማለት በቀር መግለጫ አጥቼለታለኹ፡፡ ሁሌም በሰው አገር ያየኹትን የሰው ነገር ከማውቀው ጋራ ለማነጻጸር በምናቤ ወደ አገሬ እመለሳለኹ፤ በሐሳቤም እዋቀሳለኹ፡፡ የካዲላክ ፓላስ ቴአትር ሥነ ኪን ባለአንበሳ ሐውልቱን ቴአትር ቤታችንን - ብሔራዊ ቴአትርን - አስታወሰኝ፡፡ በንጽጽሬ ግን ከመዝናናት ይልቅ ከፍተኛ ተግሣጽ እንደደረሰበት አዳጊ ዙሪያ ገባውን እያየኹ ሰውነቴን አሸማቅቄ፣ ድምፄን አጥፍቼ፣ ጥፍሬን እየቆረጠምኹ ‹‹ሌስ ሚዝራብልስ›› የተሰኘውን የብሮድዌይ ተውኔት መጀመር መጠባባቅ ያዝኹ፡፡ የተውኔቱ ታሪክ በፊልምም ተሠርቷል። በአሜሪካ ቦክስ ኦፊስ የሰንጠረዡን የላይ እርከን የተቆናጠጡ ፊልሞችን በትኩስነታቸው የሚያስኮመኩመው ‹‹ኤድናሞል ማቲ ሲኒማ›› ከወራት በፊት ሺሓት በአድናቆት የጎረፉለትን ‹‹ሌስ ሚዝራብልስ›› የተሰኘውን ፊልም አስመጥቶት ነበር፡፡

ፊልሙ በተመሳሳይ ርእስ ለአንባብያን በበቃው በታዋቂው ፈረንሳዊ ደራሲና ጸሐፊ ተውኔት ቪክቶር ሁጎ መጽሐፍ ላይ የተመረኮዘ ነው፡፡ መጽሐፉ ‹‹ምንዱባ›› እና ‹‹መከረኞቹ›› በሚሉ ርእሶች ተተርጉሞ ለአገራችን አንባቢዎች ቀርቧል። በኢትዮጵያ ሬዲዮ የ‹‹ከመጻሕፍት ዓለም›› ፕሮግራም በተተረከበት ወቅት የመጽሐፉ ተወዳጅነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ እንደነበር አስታውሳለኹ። ለዓመታዊው የኦስካር ሽልማት በበርካታ ዘርፎች ታጭቶ የነበረውና በሙዚቃዊ ድራማ ዘውግ የተሠራው ፊልሙ በኤድናል ማቲ ሲኒማ ቤት ለመቆየት የታደለው ግን ለአንድ ቀን ብቻ ነበር፡፡ በተመልካች ዘንድ አልተወደደም በሚል የመታያ ጊዜው በአጭሩ ተቀጭቷል፡፡ በኢትዮጵያ እምብዛም ተቀባይነት ያላገኘው ይህ ፊልም፣ በአሜሪካና በተቀረው ዓለም ሚልዮኖች በሲኒማ ቤት ተሰልፈውለታል፡፡ ተውኔቱን ደግሞ በ28 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ወደ 60 ሚልዮን ተመልካች ታድሞበታል፡፡ ለሁለት ሰዓት ከ50 ደቂቃ የታየው ተውኔት ከተጀመረበት እስከተጠናቀቀበት ደቂቃ ድረስ ለቅጽበት እንኳ ሌላ ነገር የማሰቢያ ጊዜ አልሰጠኝም።

የመድረክ ዝግጅቱ፣ ድምፁ፣ ሙዚቃው፣ አልባሳቱ፣ የተዋናያኑ የትወና ብቃት ከኹሉም በላይ ደግሞ የተጠቀሙበት ቴክኖሎጂ እጅግ ይማርካል፡፡ ታሪኩ የሚጠይቃቸው ነገሮች በሙሉ በመድረኩ ላይ በወጉ ተሟልተዋል፡፡ ቤቶቹ፣ መንገዱ፣ ዛፎቹ፣ ድልድዩ፣ ውኃው፣ ጦርነቱ ሳይቀር ልክ እንደ ፊልሙ በተውኔቱ ላይም ተሰናኝተው ታይተዋል፡፡ ቴአትሩ ተጠናቆ ተዋንያኑ ለተመልካቹ እጅ እስኪነሱ ድረስ ጠቅላላ መሰናዶው ለእውንነት የቀረበ፣ በእውኑ ዓለም የሚያቆይ ነበር፡፡ በአዳራሹ የሞላው ተመልካች ከመቀመጫው ተነሥቶ በከፍተኛ ጭብጨባ ለተዋንያኑ አድናቆቱን ገለጸ፡፡ የእኔ አድናቆት ግን ለአገሬ የጥበብ ሰዎች በዘርፉ የተሟላ መሰል ቴክኖሎጂንና ብቃትን አሟልቶ እንዲሰጣቸው ከመመኘት ጋራ ነበር፡፡ አዳራሹን ለቀን ወደ ሆቴላችን በሚያደርሰን አውቶብስ ውስጥ ስንገባ እንደተለመደው ስለውሎአችን ለሚጠይቀን ቡድን መሪው ጆን ሁላችንም በአንድ ላይ፣ ‹‹እጅግ በጣም ያምራል፤ እንዲህ ያለውን ጥበብ፣ ቴክኖሎጂ እንድናይ ስለጋበዛችኹን እናመሰግናለን›› በማለት ምላሽም ልባዊ ምስጋናም አቀረብን፡፡ ወደ ማደሪያችን እስክንደርስ ከቴአትሩና ተውኔቱ ሌላ ወሬ አልነበረንም፡፡ በርግጥም ቴአትሩ፣ ተዋንያኑና ተውኔቱ አፍሪካውያንን እጅግ በጣም አስደንቆንና አስደስቶን ነበር፡፡                                             ******************

አሜሪካ በመዝናኛ ኢንደስትሪው ላይ ከፍተኛ ትኩረት እንደምታደርግ ካዲላክ ፓላስ ቴአትርና ተውኔቱ ኹነኛ ማሳያ ነው፡፡ ቆየት ብዬ እንደታዘብኹት በየከተሞቿ እንደ ካዲላክና ከዚያም በላይ እጅግ የተጋነነ ውበት ያላቸው ቴአትር ቤቶች አላት፡፡ የኒውክሌርን ያህል ትቆጥራዋለች በሚባለው የፊልሟ ጥበብም ከራሷ አልፎ የዓለምን ቀልብ ስባበታለች። ራሷን ለገበያ የምታቀርበው፣ በሌሎች ዘንድ የምትናፈቅና የምትወደድ እንድትኾን የምታደርገው በፊልም ጥበብ ይመስለኛል፡፡ የአገሪቱ ወጣቶች በብዛት ወደ ሕክምና ሞያ እንዲገቡ ለማድረግ ከፍተኛ በጀት እየተመደበ እንኳ ምርጥ የቴሌቭዥን ተከታታይ ፊልሞች ይሠራሉ፡፡ ከወጣቶቿ የሚበዙት ከዋና ሥራቸው ወይም ሞያቸው ቀጥሎ ትኩረታቸው ለመዝናኛ ወሬ ነው፡፡ ርካሽና ፈጣን የኢንትርኔት ቴክኖሎጂውን አዘውትረው ጆሯቸው ላይ በሚሰኩት ማዳመጫና በስልካቸው ሲከታተሉና መረጃ ሲሰበስቡ ውለው ያድሩበታል፡፡ ከወገኖቻችን እንደ አንዳንዶቹ በምኑም በምኑም ሲያንቧትሩና ሲዳክሩ አይውሉም። የሚመለከታቸውን ነገር ጥንቅቅ አድርገው በጥልቀት ካወቁ ስለተቀረው ጉዳይ እነርሱን አይመለከታቸውም። ለዚህ ዝንባሌያቸው ሚዲያዎቻቸውም ሚና ሳይኖራቸው አይቀርም፡፡

በአንድ አካባቢ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የቴሌቭዥን ጣቢያዎች ቢኖሩም ከጥቂቶቹ በስተቀር አብዛኛዎቹ የቶክ ሾውና የመዝናኛ ቻናሎች ናቸው፡፡ ጥቂት የሚባሉት የዜና ቻናሎችም ቢኾኑ ምንም ቢፈጠር ከአካባቢያዊ ጉዳዮች ውጭ ሌላ ነገር አያቀርቡም፡፡ ዜናዎቻቸው በሙሉ ስርጭቱ በሚሸፍነው ግዛት ክልል ስለተከናወኑ ጉዳዮች ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ስለ ዓለም ወሬ መስማት የፈለገ ዓለም አቀፍ ቻናሎችን መግጠም አሊያም በኢንተርኔቱ ማሠሥ ግድ ይለዋል፡፡ ለዚህ ግን ጊዜ ያላቸው አይመስሉም፡፡ ቱሪስቶቹ ሌላ አገር ለመጎብኘት የሚነሡት በጡረታ ጊዜያቸው ላይ ነው። ወጣቶቹ የዕረፍት ጉብኝት ማድረግ የሚጀምሩት በዚያው በአሜሪካ ሌሎች ግዛቶች ነው፡፡ ከአሜሪካ የሚወጡ ወጣቶች ካሉ ጥቂቶች ናቸው፤ እነርሱም የቤተሰቦቻው ፈቃድና ፍላጎት መሠረት ያደርጋሉ፡፡ አሜሪካውያን በቤታቸው የሚያደርጉትን እንግዳ አቀባበልና ኑሯቸውን እንድንመለከት በየተመደብንበት ቤት ለአንድ ቀን ቆይታ አድርገን ነበር፡፡ እኔ፣ ናይጄሪያዋ ቲሚ እና ኬኒያዊው ታሩስ አስማ አንዋር ወደተባለች ወጣት አሜሪካዊት መኖሪያ ቤት ተመራን፡፡

አስማ የዐረብ ዝርያ ካላቸው ቤተሰብ የተወለደች ብትኾንም ተወልዳ ያደገችው ግን አሜሪካ ውስጥ ነው፡፡ በደቡብ ምሥራቅ ኤስያ አገሮች ጋዜጠኛና የንግግር ጸሐፊ ኾና ሠርታለች፡፡ አሁን የሕግ ባለሞያ በመኾኗ ፍሎሪዳ - ፔንሳኮላ ውስጥ በወንጀል መከላከል ጥብቅና ትሠራለች፡፡ ዐሥራ ሦስት የዓለም አገሮችን ተዘዋውራ ጎብኝታለች፤ አፍሪካ ውስጥም ግብጽን ጎብኝታለች፡፡ አስማ ዘንድ የተመደብነው ስለ አፍሪካ ታውቃለች ከሚል እንደኾነ ገምቻለኁ፡፡ እውነትም የአስማ ዓለም አቀፋዊ ዕውቀት ሰፋ ያለ ነው፡፡ ከየት እንደመጣኹ ጠይቃ ‹‹ከኢትዮጵያ›› ስላት ‹‹እርሷ ደሞ የት ነው የምትገኘው?›› ብላ እንደሌሎቹ አላሸማቀቀችኝም፡፡ አገሬን ታውቃታለች፡፡ መቼም ኢትዮጵያውያን ወደ ባሕር ማዶ ሲጓዙ አገራቸው በብዙ መልኩ በዓለም ሕዝብ ፊት ታዋቂ እንደኾነች ያስባሉ፡፡ ጥንታዊቷና የዘመናት ታሪክ ያላት አገራችን የት እንደኾነች መጠየቅ ምን ያህል ግርታ እንደሚፈጥር የሚታወቃቸው ግን ከአገር ሲወጡና መልክአ ምድራዊ መገኛዋን የመጠየቅ ‹ድፍረት› ሲገጥማቸው ነው፡፡ በአንድ አፓርትመንት ውስጥ በሚገኘው የአስማ መኖሪያ አብረናት አመሸን፡፡ ስለ ሥራዋ፣ ኑሮዋ አጫወተችን፡፡

ብዙውን ጊዜ እንደምታደርገው የነገረችንን ፓርቲ መሰል ዝግጅት ለምሽቱ አዘጋጅታለች፡፡ ቀለል ካለ ራት ጋራ ወይን እየተጎነጩ መጨዋወት እንደምትወድ ነገረችን፡፡ በዕለቱም ከተለያዩ ሰዎች ጋራ ብንወያይ እንደማይገደንና እንደማይደብረን በማሰብ በርካታ ጓደኞቿን መጋበዟን ነገረችን፡፡ ራት አዘጋጅታ ስታጠናቅቅ ተጋግዘን አቀራረብነው፡፡ ማምሻውን የተጠሩት ጓደኞቿ መጠጥ እየያዙ በሰዓቱ ተገኙ፡፡ አንድ ወጣት ፕሮፌሰርን ጨምሮ ሁሉም የአስማ ጓደኞች ምሁራን ናቸው፡፡ ከአስማ በቀር አንዳቸውም በስም እንኳ አገሬን አያውቋትም፡፡ ታሪክና ጂኦግራፊ ያበቃ መሰለኝ። ለእነርሱ ኢትዮጵያን ለማስረዳት ያልፈነቀልኁት ደንጊያ የለም፡፡ ሰሚ ባገኝ ብዬ በዝነኛው ቡና መሸጫቸው ውስጥ የሚገኘው የሲዳማ ቡና መገኛ እናት አገር ኢትዮጵያ መኾኗን ተናገርኁ፡፡ ቀደም እንዳልኋችኹ ከአገሬ ስነሣ ኢትዮጵያ የምትባለዋን አገር ዓለም ኹሉ እንደሚያውቃት የነበረኝን ሐሳብ ድራሹን አጠፉብኝ፡፡ ከራት በኋላ በነበረን የሞቀ ጨዋታ ስለ ናይጄሪያ፣ ኢትዮጵያና ኬንያ ለማስረዳትም ጊዜ ወስዶብን ነበር። ሁላችንም በየፊናችን ስለ አገራችን ለማስረዳት እንሻማለን፡፡ በሽሚያችን፣ የናይጄሪያዋ ቲም ወትሮውንም ስታወራ በጣም ትፈጥናለችና ያን ዕለት ስለ አገሯ እየተሽቀዳደመች ስታስረዳ÷ ‹‹እንዴት የሰው አገር ቋንቋ እንዲህ ፈጥነሽ ልታወሪ ቻልሽ?›› ብለው አሸማቀቋት፡፡

የየራሳችን ቋንቋ ያለን ሕዝቦች በእነርሱ ቋንቋ ማውራታችን በራሱ አስገርሟቸዋል፡፡ እኔና ኬንያዊው ጋዜጠኛ ስለየራሳችን አገር ስንገልጽ፣ ‹‹አትሌቶቻችን ከዓለም አንደኛ ናቸው›› በማለታችን የተካረረ ክርክር ተነሥቶ ነበር፡፡ ኬንያዊው ታሩስ በክርክሩ መሀል፣ ‹‹እናንተ ያላችኹ ኀይሌ ገብረ ሥላሴ ብቻ ነው›› ሲል የመምጫዬ አገር ታሪክና ጆግራፊያዊ አቀማመጥ ግራ አጋብቶት የነበረው አንዱ ወጣት አሜሪካዊ፣ ‹‹ገብረ ሥላሴ እናንተ አገር ነው እንዴ?›› ብሎ የመረጃ ክፍተቱን ስላሰፋልኝ ደስ አለኝ፡፡ ይህን ያህል ግዙፍ የመረጃ ክፍተት በማግኘቴም ስለቀሪዎቹ አትሌቶች ኮራ ብዬ አስረዳኹ፡፡ አሜሪካኖቹ የታሪክና ጂኦግራፊ ዕውቀታቸው አነስተኛ ነው፡፡ ይህ የኾነው ደግሞ አይጠቅመንም ብለው ስለሚያስቡ ነው፡፡ እነርሱን የሚጠቅመው የሚመለከታቸውን ጉዳይ አጥብቆ ይዞ ዕውቀታቸውን ማጎልበት፣ በዚያም ላይ መሥራትና በዕረፍት ጊዜያቸው መዝናናት ብቻ ነው፡፡ በእነርሱ አገር የጠቅላላ ዕውቀት የሬዲዮና ቴሌቭዥን ጥያቄና መልስ ውድድር የለም፡፡ በጨዎታችን ያግባባን የጋራ ጉዳይ ቢኖር የአሜሪካ ምርጫና ሙዚቃ ነበር፡፡ ስለ ዘፋኞቻቸው ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ ይህን ስመለከት ቻርልስ ኦያንጎ የተባለ ዑጋንዳዊ ደራሲና ጋዜጠኛ፣ ‹‹ ቢራና የአውሮፓ እግር ኳስ ባይኖር ኖሮ የአፍሪካ መሪዎችን ምን ይውጣቸው ነበር?›› ያለውን አስታውሼ ‹‹ለመዝናኛው ኢንደስትሪ እንዲህ ትኩረት ባትሰጥ ኖሮ አሜሪካን ምን ይውጣት ነበር?›› ብዬ አሰብኁላት፡፡ አስተሳሰቤ ግን የሞኝነት መኾኑን ቆየት ብዬ ተረዳኁት፡፡ አሜሪካኖች በኹሉም ጉዳዮች ላይ ስለሚመለከታቸው ነገር ለማወቅ የሚቀድማቸው የለም፡፡

የታሪክና የጂኦግራፊው ጉዳይም ከሚመለከታቸው ጋራ ስላልተገናኹ ይኾናል፡፡ ይህን የተረዳኁት ደግሞ የኮንግረስ ሠራተኛውን ማትን ዋሽንግተን ዲሲ ባገኘኁት ጊዜ ነበር፡፡ ወደ ኢትዮጵያ የመመለሻ ጥቂት ቀናት ሲቀሩኝ ሌላ ከተማ በሚኖሩ ጓደኞቼ አማካይነት ያገኘኁት ማት አሜሪካዊ መኾኑን እስክረሳ ድረስ ሐበሻ መስሎኛል፤ ሐበሻ ኾኖብኛል፡፡ ስለ አገሬ የማያውቀው ነገር የለም፡፡ እኔ እንደርሱ አገሬን አላውቃትም ብል አልተሳሳትኁም። ስለ ብዙኀን መገናኛውና ጋዜጠኞቻችን፣ ስለ ፖሊቲካውና ፖሊተከኞቻችን አንዲትም ሳትቀረው ያውቃል፡፡ ስለ ፖሊቲከኞቻችን ማንነት፣ ጠባይዕና የዕውቀት ይዞታ ጨምሮ ጥቃቅን ነገራቸውን ያወራል። በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የፖሊቲካ አስተሳሰብና አካሄድ ያውቃል፡፡ ታዋቂዎቹን የተቃውሞ ፖሊቲካ ፓርቲ አመራሮች በስምና በመልክ ለይቶ የሚገኙበትን ቦታና ኹኔታ ጭምር ጠንቅቆ ይናገራል፡፡ ፖሊቲካዊ ጉዳዮችን በሚመለከት በተለያዩ መድረኮች በሚካሄድ ውይይት ላይ የትኛው ፖሊቲከኛ ማስታወሻ እንደሚይዝና ማንኛው ፖለቲከኛ ተኮፍሶ እንደሚያወራ ሳይቀር አጥንቷል፡፡ ስለ ገዥው ፓርቲ ሹማምንትማ በሚገባ ያውቃል፡፡ በኢትዮጵያውያን ሬስቶራንት ጥሬ ክትፎ አብሮኝ የበላው ማት ሻይ ውስጥ ስለምንጨምረው ቀረፋና ቁርንፉድ (ጣዕማችን) ኹሉ ያውቃል፡፡ ስለ ማት ያለኝን ምስክርነት በእኔ የመረጃ ክትትልና የዕውቀት ዳርቻ ለማረጋገጥ ልድፈርና፣ ማት ስለ እኔ አገር ያለውን ዕውቀት ስሰማ አሜሪካውያን ሥራዬ ብለው በሚከታተሉት ጉዳይ ላይ ያላቸውን የመረጃና ዕውቀት መልክና ልክ በወጉ አሳይቶኛል፡፡ (ይቀጥላል)

  • ተቃዋሚዎች የፖለቲካ ፓርቲነት ባህሪም፣ ይዘትም፣ ቅርፅም የላቸውም
  • አስመራ ያለው ፀሃይ የጠለቀችበት ጠንቀኛ መንግስት ነው
  • ከመለስ በኋላ ህወሓት ተቀባይነት አጥቷል የሚባለው ስህተት ነው

የህወኃት መስራች እንዲሁም በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አለማቀፍ የሠላምና ልማት ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቦይ ስብሃት ነጋ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ላቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል፡

የመለስን ፋውንዴሽን በአዋጅ ማቋቋም ለምን አስፈለገ? የመንግስትን ጣልቃ ገብነት እንዴት ያዩታል? 54ሺ ሰማዕታት እያሉ እንዴት ለአቶ መለስ ብቻ ተለይቶ ፋውንዴሽን ይቋቋማል የሚሉ ወገኖች አሉና የእርሶ ምላሽ ምንድን ነው? በአፍሪካም በሌላም በሰው ስም የተቋቋሙ ፋውንዴሽኖች አሉ፡፡ እንዴት እንደተቋቋሙ አላውቅም፡፡ የመለስ ፋውንዴሽን በመንግስት አዋጅ መቋቋሙ ተገቢ ባይሆን ኖሮ የኛ ሰዎች አያደርጉትም ነበር፡፡ ለመሆኑ የሚከለክል ሕግ አለ ወይ? 54 ሺ ሰማዕታት ምናልባት የትግራይ ሰማእታት ብቻ ነው ሊሆኑ የሚችሉት፡፡ የአሁኒቱ አዲሲቱ ኢትዮጵያ፣ መላ ህዝቦች የጠራ ኢትዮጵያዊ ኘሮግራም ባይኖራቸውም፣ ከዚህ የከፋ የለም በማለት ማእከላይ መንግስትን የተዋጉበት ዘመንና የከፈሉት የንብረትና የህይወት ዋጋ የሚታወቅ ይመስለኛል፡፡

ከዚህ የከፋ ሲኦል የለም ብሎ ያለ ብቁ መሪ ሲፋለም የሞተውም ሰማእት ነው፡፡ ለነዚህ ሰማእታት በየክልሉ መታሰቢያ የተሰራላቸውም እየተሰራላቸውም ያለ ይመስለኛል፡፡ አልተረሱም፡፡ እነዚህ በየክልሉ ያሉ መታሰቢያዎች የመለስም መታሰቢያዎች ናቸው፡፡ የመለስ ፋውንዴሽንም የሁሉ የሃገሪቱ ሰማእታት ፋውንዴሽን ነው፡፡ ነጣጥሎ ማየት ሳይንሳዊም ፍትሃዊም አይደለም፡፡ ሁሉም ሰማእታት መንፈሳዊና ህሊናዊ ግንኙነት አላቸው፡፡ ለመላ የአትዮጵያ ህዝብም ዘልአለማዊ የህዝባዊነት ሃይል መልእክት እያስተላለፉ ይኖራሉ፡፡ አሁን የሚያሰጋው የመለስ ራእይ እንደቁምነገር ሳይሆን እንደመፈክር ይዞ በጥገኝነት ተዘፍቆ የነበረው እንደ መደበቂያ፣ አዲሶች ሊጨማለቁ የፈለጉ ደግሞ እንደ መታወቂያ ይዘው፣ ለአመታት ተዘፍቀንባቸው የነበሩ ችግሮችን እንዳንፈታ፣ እንደመጋረጃ እንዳይጠቀሙበት ነው፡፡ በታሪክ መኖር ባህላችን ነውና፡፡ ኢህአዴግ አንድ ውህድ ፓርቲ መሆን አለበት የሚሉ ሃሳቦች አሉና በእርሶ በኩል ያለው እይታ ምንድን? ኢህአደግ ስሙ እንደሚያመለክተው አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ኘሮግራም ይዞ የተነሳ የፖለቲካ ድርጅት ነው፡፡

የነፃ ገበያ ኢኮኖሚን በልማታዊ መስመር እየመራ በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ካፒታሊዝምን በመላ ኢትዮጵያ ለማስፈን ነው ዓላማው፡፡ ይህ እንደህልም እናየው የነበረና፤ በሌላ አገር ስናየውም ስንቀናበት የነበረ የማንነታችን ታላቅ የእድገት ደረጃ ነው፡፡ በዚህ ህልም የሚመስል ግን ሊፈፀም እንደሚችል ምልክት የታየበት የካፒታሊስት ስርዓት፣ ተጠቃሚ ሆነው በቆራጥነት ሊታገሉ የሚችሉት አርሶ አደሩ፤ አነስተኛው ባለሃብትና አብዮታዊ ምሁራን ናቸው፡፡ እነዚህ አራቱ መደቦች የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መሰረቶች ናቸው፡፡ ልማታዊው ባለሃብትንም እንደቆራጥ አጋር ይወስደዋል፡፡ ይህ መደብ በሂደት ሃላፊነቱን በወሳኝነት እየተረከበ ይሄዳል፡፡ አሁን ግን በጥራትም በብዛትም ደካማ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በዚህ ሁኔታ እያለም በካፒታሊዝም ግንባታና ዲሞክራሲን በማስፈን ረገድ ሚና አለው፡፡ በኢትዮጵያ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ /የካፒታሊዝም ስርዓት ግንባታ/ ነቀርሳ የሆነው ጥገኛው ነው፡፡

የጥገኝነት አመለካከት በተግባር የሚገለፀው እጅግ በጣም ብዙ በሆኑ መንገዶችና አግባብ ነው፡፡ እጅግ በጣም የህዝብ፣ የሃገር ጠላት ተደርጐ ነው መወሰድ ያለበት፡፡ የጥገኝነት አመለካከትና ተግባር በባለስልጣን ይሁን በባለ ሀብት፤ አገር በመበታተን አይን ቢታይ ከውጭ ወራሪ የባሰ ነው፡፡ ስለዚህ አደረጃጀቱ በግንባር ይሁን በውህድነት፤ የሚለው የመልክ ለውጥ እንጂ የአሰላለፍና፤ የፖለቲካ ይዘቱን አይቀይረውም፡፡ ጉዳዩ በጉባኤው ተነስቶ ይጠናል ተብሏል፡፡ ዋናው ጥያቄ መሆን ያለበት ግን የአብዮቱ ሃይሎች በመሉ በኘሮግራሙ ዙርያ ፀረ ጥገኝነት ማሰለፉና ጥገኝነትን መቆጣጠሩ ነው፡፡ እግረ መንገድ በኘሮግራም ደረጃ የኢህአዴግን የመሰለ የጠራና የወቅቱን የሃገር የእድገት ችግሮች የሚፈታ ኘሮግራም ያለው ፓርቲ በአፍሪካ የለም፡፡

በፓርቲ ብቻ ሳይሆን በመንግስት ባህሪ ደረጃም ኢህአዴግ ተወዳዳሪ የለውም፡፡ የዚህን ብርቅና የላቀ ድርጅት፣ የአደረጃጀት መልክ ከማየት በፊት፣ ኘሮግራሙን ማወቅና ለተፈፃሚነቱ ቅድሚያ መስጠት ይሻላል፡፡ ከአቶ መለስ ህልፈት በኋላ ህወሓት በትግራይ ህዝብ ያለው ተቀባይነት ቀንሷል የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡ ብዙ የህዝብ እሮሮ እና የመልካም አስተዳደር እጦት በትግራይ ውስጥ ይታያል ይባላል፡፡ በክልሉ ባለው የስራ አጥነት ችግርም በርካቶች ወደ አዲስ አበባ እየተሰደዱ እንደሆነም ይነገራል፡፡ እርስዎ ምን ይላሉ? በትግራይ የተሰሩ በጐ ነገሮች አሉ፡፡ ግን እንደሌላው ክልል ስራ አጥነት፤የመልካም አስተዳደር እጦትና ሌሎች የጥገኝነት መገለጫዎች ድሮ መለስ እያለም ነበሩ፡፡ ከመለስ በኋላ አዲስ የመጡ ችግሮች አይደሉም፡፡ የህወሓት ኘሮግራም ብቁና በመሰረቱ የማይቀየር ነው፡፡ ድርጅቱ ከመለስ በኋላ ተቀባይነት አጥቷል የሚል አባባል ስህተት ነው፡፡ መጠናከር ግን ያስፈልገዋል፡፡ የመጠናከር ኘሮግራም በህወሓት በየወቅቱ እንደአስፈላጊነቱ የሚመጣ ኦፊሴላዊ ኘሮጀክት ነበር፡፡ ህወሓት እጅግ በጣም ታሪካዊ ድርጅት ስለሆነ፣ በይሉኝታ ምክንያት ድክመትን ደብቆ አድበስብሶ ማለፍ ባህሉ አይደለም፡፡ ከመጠናከር፤ ከመታደስ የሚያፈገፍግ ድርጅት አይደለም፡፡ በየወቅቱ አስፈላጊው ዋጋ እየተከፈለበት የመጣ ህዝባዊ ድርጅት ነው፡፡ ድሮም አሁንም የጥንካሬ ምንጩ አባላቱና ህዝቡ ናቸው፡፡

የህውሓት ከፍተኛ አመራር ውስጥ ባልና ሚስት በርከት እያሉ መሆናቸው “የቤተሰብ ፓርቲ” ያስብለዋል የሚሉ አሉ፡፡ ቀደም ሲል አቶ መለስ እና ባለቤታቸው፤ አሁን ደግሞ አቶ አባይ ወልዱና ባለቤታቸው የስራ አስፈፃሚ ቦታ ላይ መቀመጣቸውን መነሻ በማድረግ በዚህ ቅሬታ የገባቸው አካላት ህወሓት እያከተመለት ነው ይላሉ … ባለፉት ጉባኤዎች አምስት ባልና ሚስት በህወሓት ከፍተኛ አመራር ነበሩ፡፡ አሁን ያሉት ባልና ሚስት ሁለት ናቸው፡፡ “በርከት ብለዋል” የሚለው ጥያቄ ከየት እንደሚመጣ ለኔም ለሌላም የሚገባው አይመስለኝም፡፡ የአሁኑ ጥንዶች ለስራው ብቁ ታጋዮች ናቸው፡፡ ግን ደግሞ ብቃት ተነፃፃሪ ነው፡፡ ስለዚህ አልጠየከኝም እንጂ እኔ በበኩሌ (በግሌ) እነዚህ ሁለቱም ሆኑ ሌሎች ሳይተኩ የቀሩ (ጥቂቶች) ጭምር አሁን በወጡትና በሌላ አዲሶች መተካት ነበረባቸው፡፡ ግን ከፍተኛው የህወሓት አካል ጉባኤው፤ ስለመረጣቸው መቀበል ነው ያለብን፡፡

ብዙ ነገር አያጐድልም፡፡ የኢትዮጵያና ኤርትራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ወዴት የሚያመራ ይመስልዎታል? ህዝብ ከህዝብ የሚያጣላ፣ ህዝብን የሚፈራ ፀረ - ህዝብ የሆነ መንግስት ብቻ ነው፡፡ ህዝቦች የሚያፋቅር እንጂ የሚያጣላ ጥያቄ የላቸውም፡፡ በኢትዮጵያና በኤርትራ ህዝቦች አለመተማመን ካለ፣ ድሮ አዲስ አበባ የነበሩ መንግስታትና አሁን ደግሞ (ከነሱ የባሰ) አስመራ ያለው መንግስት የፈጠሩት ነው፡፡ በኢህአዴግ ዘመንም ቢሆን በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ጊዜ በኢትዮጵያ የበላይነት ይዞ የነበረው፣ ከወላጆቹ የማይተናነስ የቀኝ ዘመም አርበኝነት/ ultra rightist patriotism/ አብሶት፣ የሰላም መፍትሄ ዕድል አልሰጥም ብሎ አስመራ ካልደረስኩ፣ አሰብን ካልያዝኩ ብሎ ነበር፡፡ ይህ አይነት አርበኝነት አሁን በኢትዮጵያ የለም፡፡ አሁን በኢትዮጵያ ያለው ሃይል ህዝባዊና የሰላም ሃይል ነው፡፡ በርግጥ የኤርትራ ህዝብ ወንድም ህዝብ ነው ከሚል “አሰብ የኛ ነው” የሚል ጨርሶ ጠፍቷል ማለት አይደለም፡፡ ግን የተዳከመና ጊዜው ያለፈ ነው፡፡ ስለዚህ እንዳልኩት አስመራ ያለው ሃይል ፀሃይ የጠለቀችበት ጠንቀኛ መንግስት ነው፡፡

የኤርትራ ህዝብ ከዚህ ዓይነት ስርዓት ከተገላገለ፣ ኤርትራ ነፃነትዋን ይዛ ከኢትዮጵያ ጋር በጣም የጠበቀና ልዩ ግንኙነት የምታደርግበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ ይህን የተዳፈነና የታመቀ የሁለቱን ህዝቦች ሃይል የሚያቆመው ምንም ነገር የለም፡፡ እኛ ከአካኪ ዘራፍ እንደተገላገልነው ሁሉ የኤርትራ ህዝብም መገላገሉ የማይቀር ነው፡፡ ይህ መሬት፣ ይህ ዳገት፣ ይህ ወንዝ … የሚባለው በህዝቦች ወንድማማችነት መተካቱን ሊያቆመው የሚችል ሃይል ያለ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህ ከሌሎች ጐረቤት ህዝቦች በፊት በሁለቱ ህዝቦች መካከል ልዩ ግንኙነት ይፈጠራል፡፡ ቀስ በቀስ እየተሸረሸረ ነው ስለሚባለው የሀገሪቱ የፕሬስ ነፃነት ምን ይላሉ? ቀስ በቀስ እየተሸረሸረ ነው ከተባለ ወደ ሃያ ዓመት ይጠጋል፡፡ ግን እስካሁን ለምን ተሸርሽሮ አላለቀም? አሁን ያለው የግል ኘሬስ ባብዛኛው ፤አንዳንዶቹ እየተሻሻለ ነው ቢሉም፤ እኔ አልፎ አልፎ እንደማየው ግን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በሃይማኖትም ሆነ በሌላ … ወገን ከወገን የሚያጣላ፤ ለአመፅ የሚሰብክ፤ ስለ ኢህአዴግ መጥፎ ነገር እንጂ ስለሃገሪቱ መሰረታዊ፤ ታሪካዊና ባህላዊ ጉዳዮችና ሌሎች ማነቆዎች ብዙም የማያነሳ ነው፡፡ ከፓርቲ ጉዳይ ባሻገር ስለሃገራዊ ግንባታ ጉዳይ ብዙም ደንታ ያለው አይደለም፡፡

ስለ ሃይማኖት መቻቻል፤ ከታሪካችን የወረስናቸውና የእድገት ማነቆ ስለ ሆኑት ጠባብነት ፤ትምክህት፤ታታሪነት፤ባለሞያነት ወዘተ አይፃፍም፡፡ ባጭሩ መሰረታዊ የሆኑ ያገር ግንባታ ጉዳዮች የማይታይበት፤ ከዚህ አለፍ ብሎም ስለግለሰቦችና ስለአመፅ ወይም ደህና ከተባለ ስለኢህአዴግ መጥፎነት የሚጽፍ ነው፡፡ የሌሎች የአፍሪካ አገሮች የግል ኘሬስና የኛን ስናወዳድረው ፤ እነሱ የሌሎች አገርን ማእከል አድርገው ነው የሚፅፉት፡፡ ሃገራዊ ጥቅም ያስቀድማሉ፡፡ የኛ የግል ኘሬስ ደረጃው በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ ይህ የሞያና የሃገራዊ አመለካከት ደካማነት ካለፈው ስርዓት የወረስነው ነው፡፡ የተከለከለ ስለነበር አልለመድንም፡፡ ለመብቃት ደግሞ ጊዜ ወሰደብን፡፡ ባጭሩ ግን በኔ እምነት፤ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ዓመፅን የሚሰብኩ ሁሉ፤ ሃገራዊ ክህደት ስለሆነ አደጋ አያመጡም እየተባሉ በቸልተኝነት ማየት ተገቢ አይደለም፡፡ ፖለቲካዊ ኘሮግራሙ የሆነ ይሁን ህገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ ለሚካሄደው የሃገር ግንባታ እንከን የሚፈጥር የግል ኘሬስና ፀሃፊዎችን መታገስ አይገባም፡፡ ኢህአዴግ ያለ ጠንካራ ተፎካካሪ በምርጫ መሳተፉ የመድብለ ፓርቲ ስርአት ግንባታ ላይ ያለው ተጽእኖ ምንድነው? ኢህአዴግ “ጠንካራ ተቃዋሚ” የለም ይላል፡፡?ኢትዮጵያ ውስጥ አስተዋይና ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ የመገንባትና የመምራት አቅም ያለው ዜጋ ጠፍቶ ነው ወይስ በኢህአዴግ ጫና ሳቢያ ነው? የኢህአዴግ ሚና በዚህ ረገድ ምን መሆን አለበት? አሁን በኢትዮጵያ ያሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤ ምናልባት አንድ ወይም ሁለት ይገኙ እንደሆነ እንጂ፤ በፓርቲ ምንነት አንፃር ካየናቸው ፤ የፖለቲካ ፓርቲነት ባህሪም ይዘትም ቅርፅም የላቸውም፡፡

አንድ ፓርቲ የሚገነባው ፖለቲካዊ ስርዓት በጥራት አስቀምጦ፤ የዚህ ስርዓት ሞተር ናቸው የሚባሉትን መደቦች፤ወይም መደብ ወይም የህብረተሰብ ክፍሎች ለይቶ በማስቀመጥና ከዚህ መደብ ወይም ወገን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በማድረግ ነው፡፡ የኛ ተቃዋሚዎች በኢህአዴግ ጠላትነት ብቻ ነው የተሰለፉት፡፡ ወዳጃቸውን፣ ወገናቸውን፣ መሰረታቸውን፤ ሳይለዩ ጠላት ብቻ ያስቀመጡ ሰዎች (ቡድኖች) በየትኛው መለኪያ የተቃዋሚ ፓርቲ ስም ይሰጣቸዋል?ለምንገነባው ስርዓት ወዳጅ፤ ጠላት/ተቀናቃኝ/ ብሎ በመፈረጅ ነው ትግሉ መጀመር ያለበት፡፡ የሚገነቡት ስርዓት ምንድነው? የሚገነቡት ስርዓት ተቃናቃኝ ማነው? ተሰላፊ ወዳጅስ ማነው? የትኛው መደብ ወይ የትኞቹ መደቦች ናቸው ወዳጆች ?ባጭሩ በኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ውስጥ የሚጠራቀሙት የተለያየ ቅሬታና ፍላጐት ያላቸው፣ በመሰረታዊ አመለካከት የማይገናኙ ግለሰቦች ናቸው፡ የኔ ጥያቄ ሁኔታቸው በሂደት እየመነመነም ቢሆንም ለምን ይህን ያህል ጊዜ በሚያሳዝን ሁኔታ ቆዩ የሚለው ነው፡፡ እኔ ለዚህ ጥያቄ ያሉኝ መልሶች ሶስት ናቸው፡፡ አንዱ በኢህአዴግ ውስጥ ያለ የጥገኝነት አመለካከትና ተግባር የሚያስጐመጃቸው ይመስለኛል፡፡ ስልጣን ብንይዝ በወገን የመስራት፤የመስረቅ ወዘተ ወዘተ እድል ይኖረናል ከሚል ያለአግባብ የሚያበለፅግ ወንበርን አሻግሮ የማየት ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ በኢትዮጵያ የመጣ ይምጣ፣ ሸምጥጦ መብላት፤ በወገን ለወገን አለአግባብ መስራት፤ ፍርድ ማዛባት የለም ብሎ ኢህአዴግ ደረቅ የስራና የልፋት፤ የህዝባዊ ውጤት ወንበር ብቻ ያሳያቸው፡፡

ሁለተኛ በህዝቡ በተለይ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መሰረት በሆኑ መደቦች፤ የጥገኝነት አመለካከትና ተግባርን በቅፅበት የሚያቃጥል እሳት መለኮስ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ አሁን ያሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች እሳት ይበላቸውና፣ ሕብረ ብሄር ልማታዊ ፓርቲ፤ ባለሃብቱና ላብ አደሩ በየፈርጃቸው እየተደራጁ፣ ቀስ በቀስ እያደጉ ወደ ስልጣን ይጓዛሉ፡፡ በመርህ ደረጃ የኢህአዴግ ዓላማም ፍላጐትም ይህ ነው፡፡ አሁን ያሉ ወንድሞቻችንና ጓደኞቻችን የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፤ ከኤምባሲ ወደ ኤምባሲ ከመንከራተትና ከውርደት ይገላገላሉ፡፡ ሶስተኛ መፍትሄ፤ የምርጫ ቦርድ ስለፓርቲ ምንነት አጥንቶ፣ ደረጃውን የጠበቀ የፓርቲ መስፈርት ቢያወጣና ቢያስተካክል ሁሉም ወደየስራቸው ይገባሉ፡፡ በነገራችን ላይ በዓለም ላይ ከጥይት፣ ከዱላ፣ ከግድያ፣ ከእስራት… ውጭ በዲሞክራሲያዊ አግባብ ያደገ ካፒታሊዝም የለም፡፡ እንደነሱ እንሁን ማለቴ ግን አይደለም፡፡ በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች እየተፈጠረ ያለው የብሔር መፈናቀል፣ ብሔር ተኮር የሆነው የአገሪቱ ፌዴራሊዝም ውጤት ነው የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡ እርሶ ምን ይላሉ? በአንዳንድ ክልሎች ውስጥ የሚደረገው መፈናቀል ከፌደራሊዝም ጋር ግንኙነት ያለው አይመስለኝም፡፡ ጉዳዮቹን በዝርዝር አላውቃቸውም፡፡ መንስኤው ግን ሁለቱ ክልሎች ትኩረት ሰጥተው አለማየታቸው ይመስለኛል፡፡ መንስኤው ይህም ይሁን ሌላ በምንም ዓይነት መልኩ መሆን ያልነበረባቸው መጥፎ አጋጣሚዎች ናቸው፡፡ የሆኖ ሆኖ መንግስት እርምጃ እየወሰደ ያለ ይመስለኛል፡፡

ከእንግዲህ ወዲህ የሚያጋጥም አይመስለኝም፡፡ የኢህአዴግ አንጋፋ መሪዎች በአዳዲሶች እየተተኩ ነው፡፡ ይሄ መተካካት አንጋፋዎቹ ላይ የፓርቲ ህልውና ስጋት ይፈጥርባቸው ይሆን? መተካካት በፊት የነበረና አሁንም ያለ ባህርያዊ ጉዞ ነው፡፡ ኢህአዴግ መሰረቴ ካላቸው መደቦች ውስጥ በትግል ተወልዶ በትግል እያደገ፤ በህዝብ ፊት ውጤት እያስመዘገቡ ለሚመጡ ካድሬዎች አመራርን እየተኩ እንዲሄዱ የሚያስችል አሰራር አለው፡፡ ላስቀረው ልወርውረው ብለህ እንደፈለክህ ልታደርገው የማትችል ሃይል ገንፍሎ ከታች ቢመጣ በአስተዳደራዊ እርምጃ ሳይሆን በሂደት የሚመጣ ሃይል ነው ተኪ የሚሆነው፡፡ ስለዚህ ተኪ ሃይል በተደራጀ ሂደት እንጂ በጓዳ አይፈጠርም ማለቴ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ከአምናው አመራር የዘንድሮው አመራር የሚበልጥ እንደሚሆን አያጠራጥርም፡፡ ከዘንድሮም አመራር የነገው የበለጠ እየሆነ ይሄዳል፡፡ ምክንያቱም ካለፈው ትግል ቀጣዩ ትግል ነው ከባድና ረቂቅ የሚሆነው፡፡ ከራሱ የበለጠ የአመራር አካል የማይፈጥር አመራር ሲመራ አልነበረም ማለት ነው፡፡

ጨረታ ሲገመግም ነበር ማለት ነው እንጂ ሲመራና ሰው ሲያፈራ አልነበረም ማለት ነው፡፡ አሁን ያልካቸው የተተኩ አንጋፋ አመራር የሚሰጋቸው ነገር ያለ አይመስለኝም፡፡ ላመኑበት ፖለቲካዊ ኘሮግራም በፅኑ እምነት የተሰለፉ ስለነበሩና አሁን በዚያኛው ፅናት ስለሚያምኑበት፣ ድርጅቱ በፈቀደው በሌላ መንገድና አግባብ ትግሉን እንደሚቀጥሉበት ያምናሉ፡፡ በእምነት ተገቢው ግለት የሌላቸው አንዳንድ አንጋፋዎች ካሉም /ያሉም አይመስለኝም/ ለማንኛውም የድርጅት ድክመት ተጠያቂ ስለሚሆኑ ተጠያቂነታቸው ይገፋፋቸዋል፡፡ ስለዚህ የሚያሰጋቸው ነገር ፍፁም የለም፡፡ ለነገሩ አንጋፋዎቹ ወኔያቸው ስለማያስተኛቸው ነው እንጂ፣ አዲሱም አመራር የተለመደውን ድርጅት የማጠናከር ኘሮጀክቱን ቀርፆ፣ የማያሰጋ ሁኔታ ራሱ ይፈጥራል፡፡ የአንጋፋ መሰለፍ ተጨማሪ ነው፡፡

ከ1994 እስከ 1999ዓ.ም የነበረው ኢህአዴግ፣ ካፒታሊዝም የህልውና ጉዳይ ሆኖበት የቢዝነስ መሰናክሎችን አስወግዷል ከ2000 እስከ 2005 ዓ.ም ያለው ኢህአዴግ፣ ሶሻሊዝም የእምነት ጉዳይ ሆኖበት በርካታ መሰናክሎችን በዘመቻ ተክሏል ባለፉት አስር አመታት በኢህአዴግ ላይ ካየናቸው ሁለት ተቃራኒ ባህርያት ጋር የሚመሳሰል በአንድ ሰው እውነተኛ ታሪክ ላካፍላችሁ። ተራ ታሪክ አይደለም። የስመጥር ገናና ሰው ታሪክ ነው። በጊዜው ብዙ የተነገረለትና አለምን አጃይብ ያሰኘ ታሪክ! ታሪኩ ከእንግሊዝ ስኮትላንድ የሚጀምረው አስደናቂ ታሪክ፣ ወደ አሜሪካ ኢንዲያና የሚዘልቀው በታላቅ ክብር ነው - አወዳደቁም በዚያው ልክ “እጅግ ታላቅ” ሆነ እንጂ። በዚሁ ታሪክ ውስጥ ነው፤ “አዲስ ህብር (new harmony)” የተሰኘች ከተማ የተፈጠረችው።

“በሰማዬ ሰማያት በኤዶም ገነት” ውስጥ ምን አይነት ህይወትና ማህበረሰሰብ ሊኖር እንደሚችል፣ ብዙ ብዙ መላምቶች እየተሰነዘሩ ብዙ የምናብ ምስሎች መፈጠራቸው ይታወቃል። “አዲስ ህብር” ግን እዚሁ ምድር ላይ ነው - የሰማየሰማያት የገነት ህይወትን፣ እዚሁ አለም ውስጥ በእውን ለማሳየት የተፈጠረ አዲስ ከተማ! አዲስ ፕሮጀክት! አዲስ የህይወት አቅጣጫን የሚያውጅ፤ ለአዲስ አለማቀፍ ስርዓት የማንቂያ ደወል የሚያስተጋባ የእኩልነት ማህበረሰብ በምናብ ብቻ ሳይሆን፣ በአካል እውን የሚሆንበት ጊዜ ደረሰ። የዚህ ራዕይ ባለቤት ሮበርት ኦውን ይባላል። እንግሊዛዊ የኢንዱስትሪ ባለቤትና አንቱ የተባለ ሃብት ነው - ሮበርት ኦውን። ጊዜው 1817 ዓ.ም ነው - ብዙዎች የሚናፍቁት የ“ገነት ሕይወት” እዚሁ ምድር ላይ እውን የሚሆንበት አመት። ብዙም ሳይቆይ ነው፣ የሮበርት ኦውን አድናቂዎችና ተከታዮች፣ ለዚህ ግሩም ራዕይ መጠሪያ ያወጡለት፤ ሶሻሊዝም ብለው ሰየሙት። ካፒታሊስቱ ትርፋማ የቢዝነስ ሰው በስኮትላንድ የተቋቋመውና የተስፋፋው የኦውን ኢንዱስትሪ፣ በዘመኑ እጅግ ስመጥርና ታዋቂ ነበር፤ በዝና የሚስተካከለው አልነበረም።

አዳዲስ የምርት ማሽኖችን በማዘጋጀትና ስልጡን የአመራረት ዘዴ በመፍጠር እጅግ ትርፋማ ለመሆን የበቃው የኦውን ኢንዱስትሪ፣ ለባለንብረቱ በሃብት ላይ ሃብት ደርቦለታል። ለሰራተኞቹም አስገራሚ ለውጥ አስገኝቷል። የኦውን ሰራተኞች እንደሌሎች ሰዎች፣ ከንጋት እስከ ምሽት አይለፉም። በድካም እስኪዝሉ ድረስ አይሰሩም። ውጤታማ ስራ የሚያከናውኑት ለተወሰነ ሰዓት መሆኑን በመገንዘብ፤ የስራ ሰዓት እንዲገደብ አድርጓል። ሰራተኞች ሲታመሙ፣ ደሞዝ አይቆረጥባቸውም። ቶሎ አገግመው ወደ ስራ መመለስ የሚችሉት መታከሚያ ገንዘብ ሲኖራቸው ነውና። ሁለት ሺ ለሚደርሱ ሰራተኞቹም በወቅቱ እጅግ አስደናቂ የሚባሉ ባለሶስት ፎቅ የመኖሪያ ቤቶችን አሰርቷል። ታዲያ ነዋሪዎቹም በኮንዶምኒየም ቤቶቹ ውስጥ ለመኖር የድርጅቱን ደንቦች ማክበር ይኖርባቸዋል። ደረቅ ቆሻሻ በስርዓት መያዝና በትክክለኛው ቦታ መድፋት፣ የገላና የልብስ ንፅህናን መጠበቅ፤ ልጆችን ማስተማር… አለመስከር ወዘተ። ዝናው ከዳር እስከ ዳር ቢናኝም ኦውን በዚህ አልረካም። ራዕዩን ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ወደ አሜሪካ ተጓዘ።

ያኔ አሜሪካ፣ ገና ሃምሳ አመት ያልሞላት አዲስ አገር ነች - መሬት እንደ ልብ የሚገኝባትና በጥንታዊ ባህሎች ያልተተበተበች። አዲስ ራዕይን ለመሞከር ትመቻለች። በእርግጥም፤ የኦውን ዝና እጅጉን የደመቀ በመሆኑ፣ ራዕዩን ለማስተዋወቅ አልተቸገረም። የአሜሪካ ፕሬዚደንት በተገኙበት፣ የአገሪቱ ከፍተኛ የህግ አውጪ አካላት (ኮንግረስና ሰኔት) በጋራ ስብሰባ ተጠርቶ፣ ኦውን ራዕዩን አስረዳ። ራዕዩን በተግባር ለማሳየትም፣ በኢንዲያና ግዛት በድንቅ ህንፃዎች የተገነባች ትንሽ ከተማ በራሱ ገንዘብ ገዛ። ሶሻሊስቱ የህዝብ አገልጋይ በኢንዲያና የጀመረው የ“አዲስ ህብር”ፕሮጀክት ከቀድሞው የስኮትላንድ ሙከራ በእጅጉ ይለያል። አዲስ ህብር፣ ሙሉ ለሙሉ “እውነተኛ የእኩልነት ማህበረሰብ” እንዲሆን የወሰነው ኦውን፤ የሚያምሩ 160 ህንፃዎችን ያካተተ ከተማና በዙሪያ ከአንድ ሚሊዮን ሄክታር የሚበልጥ ለም መሬት ገዝቶ አዘጋጀ። እናም “አዲስ ህብር” የተሰኘ ማህበረሰብ ለመመስረት የሚፈልጉ ሰዎች እንዲመጡ ጋበዘ። አላሳፈሩትም። ጥሪውን የሰሙ 800 ሰዎችና ቤተሰባቸው ወደ ከተማዋ ጎረፉ። በተለይ ደግሞ፣ በሶሻሊዝም ሃሳቦች የተማረኩ ምሁራን እንዲሁም በእውቀትና በችሎታ የመጠቁ ሰዎች፣ እጅጉን ደስተኞች ነበሩ። “ተስማሚ መጠለያ” ለሁሉም በነፃ ተሰጠ። “ትምህርት” ለሁሉም በነፃ ተጀመረ። ማንም ሰው በምግብ አይቸገርም ተባለ - ደግሞም ለእርሻ የሚሆን ለም መሬት ሞልቷል፤ ማንም አርሶ እህል ማምረት ይችላል። ራዕዩ እውን መሆን ጀመረ - “የገነት ማህበረሰብ” እዚህችው ምድር ላይ ሀ ብሎ ተጀመረ።

እንዲያም ሆኖ፤ ኦውን ገና የልቡ አልደረሰለትም። ሁሉም ነገር በነፃ የሚዳረስበት የእኩልነት ማህበረሰብ ሙሉ ለሙሉ ያለ አንዳች እንከን እውን ሆኗል ብሎ ለመናገር ጥቃቅን እንቅፋቶች ነበሩ። የከተማዋ ነዋሪዎች በየግላቸው እያረሱ ነበር ለየግላቸው እህል የሚያመርቱት። የቤት ቁሳቁስም እንዲሁ። ለዚህም ነው፤ ኦውን ከሁለት አመት በኋላ፤ የግል ንብረት የሚባለውን ነገር ጨርሶ ማጥፋት አለብን ያለው። የከተማዋ ነዋሪዎች አልተቃወሙም። በሆታ ደገፉት እንጂ። “ሁሉም ምርትና ንብረት፤ የሁሉም የጋራ ምርትና ንብረት ይሁን” ተብሎ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ተወሰነ። የአዲሱ ራዕይ ዋነኛው ቁልፍ፣ የግል ምርትና ንብረት ማጥፋት ነው። እናም፤ የሁሉም ሰው ምርትና ንብረት ወደ፣ “የአዲስ ህብር ምርትና ንብረት ሆኗል” ተባለ። እህሉ፣ ከብቱ፣ እንጨቱ፣ ምጣዱ … ሁሉም ነገር ይሰበሰብና ለህዝቡ እኩል ይከፋፈላል። ያኔ ሁለት ችግሮች ተፈጠሩ። ሳይውል ሳያድር የሰዎችን ውሎ የሚቀይር አንደኛው ችግር፤ “ሁሉም ነገር የህዝብ ሆኗል፤ በእኩልነት ይከፋፈላል” በተባለ ማግስት፣ ከመጀመሪያው ክፍፍል አንስቶ የተፈጠረ ችግር ነው። የከተማዋ ነዋሪዎች የዘወትር ውሎ ተቀየረ። ዋነኛ ስራቸው፣ ለወረፋ ተሰልፎ መዋል ሆነ። ጨው ለማግኘት ሰልፍ፤ ቲማቲም ለማግኘት ሰልፍ፣ የኩራዝ ዘይት ለማግኘት ሰልፍ፣ ስንዴ፣ እንጨት… ከአንድ ሰልፍ ወደ ሌላው ሰልፍ ሲሯሯጡ መዋል! ከዚሁ ጋር አብሮም መቧደንና መጋጨት ተጀመረ።

“ለኔ ጅማት የበዛበት ስጋ ተሰጠኝ”፣ “ለጎረቤቴ ግን ቅልጥም ተሰጠው”፣ “በትውውቅ፣ በአድልዎ፣ በሙስና ተበደልኩ” … ወገን ለይቶ መሻኮትና መደባደብ መጣ። እንዲህም ሆኖ “አዲስ ህብር” ወዲያው አልፈረሰም። “ራስወዳድነት”ን የሚያወግዙና “ከራስ ጥቅም በፊት ለሌላው ሰው ቅድሚያ መስጠት ያስፈልጋል” በማለት ነዋሪውን የሚገስፁ ፖሊሲ አውጪ ምሁራን ሞልተዋል። አብዛኛው ነዋሪም ያጨበጭባል። እንዲሁም፤ አዳዲስ የራሽን ክፍፍል ዘዴዎችን የሚቀይሱ ፖሊሲ አውጪ ምሁራን ሞልተዋል። ክፍፍሉን የሚያከናውኑ “የህዝብ አገልጋይ ቢሮክራቶችም” በየጊዜው እየተሻሩ ይመደባሉ። እናም ማህበረሰቡ በኑሮው ቀጠለ። የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት ፈንጠዚያ ድራሹ ቢጠፋም፤ “ለሱ ከቀይ ስጋ፣ ለኔ ከልፋጭ፤ ለሱ ከሽንጥ ለኔ ቅንጥብጣቢ” እያሉ መጣላት እየቀረ መጣ። ስጋ ጠፋ። “ለሱ ነቀዝ የበላው ስንዴ፤ ለኔም እንክርዳድ የበዛበት ስንዴ” በሚል መጣላት መጣ። ይሄኔ ነው፤ ሁለተኛው ችግር አፍጥጦ የወጣው። ለካ እስካሁን አላስተዋሉትም እንጂ፤ ነገሮች ቀስ በቀስ እየተለወጡ መጥተዋል። ከከተማው ጎተራ እህል ለመከፋፈል የሚሰለፍ ሰው እንደወትሮው ብዙ ነው። እህል አምርቶ ወደ ከተማው ጎተራ የሚያስገባ ሰው ግን ቀስ በቀስ እየተመናመነ ከነጭራጩሹ መጥፋት ጀምሯል። ኦውን ያቋቋማቸው የጨርቃ ጨርቅ፣ የብረታ ብረት፣ የእንጨት ወዘተ ፋብሪካዎችም ከአጀማመራቸው አልሆኑም። የደሞዝ ክፍያ ስለሌለ፣ “ታመምኩ፣ ቆረጠኝ፣ ፈለጠኝ” ብሎ የሚቀር ሰው በዛ።

በችሎታቸው ይታወቁ የነበሩ ሰራተኞችም፣ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ከፋብሪካው ብቻ ሳይሆን ከከተማዋም ጠፍተዋል። እናማ፤ ምግብና ቁሳቁስ ፍለጋ የሚሰለፍ፣ የክፍፍል ፖሊሲ አርቃቂዎችና ውሳኔ ሰጪዎች፤ አስፈፃሚ ቢሮክራቶችና ሹመኞች አሉ፤ የሚከፋፈል ምርት እና አምራቾች ግን የሉም። ለካ፤ ብዙ ሰው በሆዱ ይዞ ዝም እያለ ነው እንጂ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የከተማዋ የነዋሪዎች ቁጥር እየቀነሰ መጥቷል። በታታሪነታቸው ይታወቁ የነበሩ ጎበዝ ሰራተኞችና አምራቾች ከተማዋን ጥለው ሲሄዱ ከርመዋል። ሳይሰሩ ለመብላት የሚፈልጉ አጨብጫቢዎች፣ ቢሮክራቶችና ፖሊሲ አውጪዎች ብቻ ናቸው የቀሩት። ቅሬታ፣ ሃሜታ፣ ትችት ከየአቅጣጫው ቢሰነዘርም፣ ሮበርት ኦውን አንዳቸውንም ለመስማት ፈቃደኛ አልነበረም። በእርግጥ፤ ሰዎች ምንም አይነት ትችት እንዳይሰነዝሩ መከልከልና ማሰር አይችልም። አሜሪካ ውስጥ የማይቻል ነገር ነዋ። የመንግስት ስልጣን ቢኖረው ኖሮ፣ ችግሩን በቀላሉ ማስወገድ ይችል ነበር - ሶሻሊስት መንግስታት እንዳደረጉት ትችት የሚሰነዝሩ ሰዎችን ማሰርና በስፋት ፕሮፓጋንዳ ማካሄድ ነዋ። ኦውን ግን፣ ለእንዲህ አይነት አምባገነንነት “አልታደለም”። ቢሆንም ዝም አላለም። ልጆቹ ሳይቀሩ፤ “ይሄ ነገር ተበለሻሽቷል፤ ይሄ ነገር አያዋጣም” ቢሉትም፤ “በጭራሽ! ትልቅ እመርታ እያስመዘገብን ነው፤ ድል እየተቀዳጀን ነው፤ ሁሉም ነገር በታቀደለት አቅጣጫ እየሄደ ነው። አንዳንድ የአፈፃፀም ችግሮች ቢኖሩም፣ በቀላሉ በህዝቡ ሙሉ ተሳትፎ እንፈታቸዋለን” … የሚሉ አይነት ምላሾችን እያቀረበ ትችቶችን ውድቅ አድርጓቸዋል።።

“የአፈፃፀም ችግሮችን ያስወግዳሉ” ተብለው በህዝብ ተሳትፎ የተተገበሩ ከደርዘን በላይ መፍትሄዎች ግን፣ አንዳችም ውጤት አልታየባቸውም። በየወሩ ሲፐወዝ የቆየው ቢሮክራሲና እንደ አዲስ ሲዋቀር የከረመው የክፍፍል ስርዓት መፍትሄ አላስገኘም። ለ7 ጊዜ የተለወጠው የከተማዋ የሶሻሊዝም መተዳደሪያ ሰነድም ለውጥ አላመጣም። “እመርታ እያስመዘገብን ነው” በማለት እውነታውን ሲክድ የከረመው ሮበርት ኦውን፤ በዚህ ፕሮፓጋንዳው መቀጠል አልቻለም። አብዛኛው ነዋሪ፣ ከተማዋን ጥሎ ሄዷል። ግን “ስህተት ሰርቻለሁ” ብሎ አላመነም። የከተማዋ ነዋሪዎች ለአዲስ ሶሻሊስታዊ ራዕይ መስዋዕትነት ለመክፈል ፈቃደኝነት የጎደላቸው ራስወዳዶች ናቸው ብሎ ወነጀላቸው። እሱ በሚያዛቸው መንገድ እንዲሰሩ ሊያስገድዳቸውና ሊያስራቸው አይችልም።

ለመላው አለም አዲስ ራዕይን ይፈነጥቃል የተባለውና “አዲስ ህብር” የተሰኘው የሶሻሊዝም ማህበረሰብ ሶስት አመት ሳይሞላው ፈራረሰ። በመላው አለም ዝነኛ ለመሆን የበቃ ታላቁ የኢንዱስትሪና የቢዝነስ ጥበበኛ ሮበርት ኦውን፤ በአንዲ ትንሽ ከተማ ውስጥ ተሸነፈ። የተለያዩ ቁሳቁሶችን በጥራትና በቅናሽ እያመረተ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ደንበኞች እያደረሰ ትርፋማ ለመሆን የቻለ፤ ከሁለት ሺህ ለሚበልጡ ሰራተኞች ከፍተኛ ደሞዝ እየከፈለ የቤተሰባቸውን ህይወት እንዲያሻሽሉ እድል የከፈተ ታላቅ ሰው ነው - ትርፋማውና ካፒታሊስቱ የቢዝነስ ሰው ሮበርት ኦውን። “አዲስ ህብር” በተሰኘው ማህበረሰብ ውስጥ፣ ግን ለዚያውም በርካታ ምሁራንና አዋቂዎች ከጎኑ ተሰልፈው እያሉ፣ አንድ ሺህ የማይሞሉ ቤተሰቦች ደህና ኑሮ እንዲመሩ ማድረግ ተስኖት ጉዞው በአጭር የተጨበት ደካማ ሰው ሆነ - ሃብት ንብረቱን መስዋዕት ያደረገ ሶሻሊስቱ የህዝብ አገልጋይ ሮበርት ኦውን።

ከዕለታት አንድ ቀን ሁለት ሰዎች ወንጀል ፈፅማችኋል ተብለው የፐርሺያ ሱልጣን ፊት ቀረቡ፡፡ ሡልጣኑ የመጀመሪያውን አስጠርተው “ወንጀሉን ለመፈፀም ያነሳሳህ ምንድነው?” ሲሉ ጠየቁ፡፡ የመጀመሪያው ሰውም፣ “ሡልጣን ሆይ! መቼም ሰው ሆኖ የማይሳሳት የለም፡፡ በተለይ በሴት የማይሳሳት የለም፡፡ አንዲት ቆንጆ ሴት የሰጠችኝን ምክር አምኜ ነው ጥፋትን የፈፀምኩት!” ሲል መለሰ ሡልጣኑም፤ “ይሄማ የወንጀል ወንጀል ነው! ከጥፋትህ የከፋው ደግሞ የአሳሳች ምክር ማዳመጥህ ነው! ከቆንጆ ሴትም ይምጣ ከአስቀያሚ ሴት ምክሩን ሳትመረምር ወንጀል መፈፀም ከፍተኛ ጥፋት ነው፡፡ ዋጋህን ልታገኝ ይገባል፡፡ እንዲያውም የሰው ምክር ሰምቼ ከምትል ራሴ በራሴ ፈፀምኩት ብትለኝ ይሻል ነበር!” አሉና ማረፊያ ክፍል ሆኖ ፍርዱን እንዲጠብቅ አዘዙት፡፡ ሁለተኛው ወንጀለኛ የመጀመሪያውን ተከሳሽ ሡልጣን ሲያናግሩት ሰምቷል፡፡ “ሁለተኛው ወንጀለኛ ይግባ” ሲሉ አዘዙ፡፡ ተጠርቶ ቀረበ፡፡

ሡልጣኑ፤ “አንተስ፤ ምን ሆነህ ነው ወንጀል የፈፀምከው?” ሁለተኛው፤ “ሡልጣን ሆይ! እኔ ማንም ቆንጆ ወይም አስቀያሚ ሴት አላሳሳተችኝም፡፡ ራሴው በራሴው የፈፀምኩት ወንጀል ነው፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝ!” ሲል አስረዳ፡፡ ሡልጣኑም፤ “ያንተ ደግሞ ከመጀሪያውም የባሰ ነው! የሠራኸው ወንጀል ሳያንስ፤ ጭራሽ ከዚህ ችሎት በሰማኸው ክርክር ችሎቱን ለማሳሳት ትሞክራለህ! አንተ እጥፍ ቅጣት መቀጣት አለብህ፡፡ ማረፊያ ቤት ቁጭ በልና ፍርድህን ጠብቅ” አሉት፡፡ ከጥቂት ቆይታ በኋላ ወንጀለኞቹ ወደ ሱልጣኑ ተጠሩ፡፡ ሱልጣኑ፤ “የፈፀማችሁት ወንጀል ከፍተኛ ነው፡፡ ይኸውም አንተ የመጀመሪያው ምክር በመስማትህ ወንጀለኛነትህ የተረጋገጠ ሲሆን፤ አንተ ሁለተኛው ደግሞ የምክር ምክር በመስማትህ ወንጀለኛነትህ ተረጋግጧል፡፡

ስለዚህ ሁለታችሁም ሞት ተፈርዶባችኋል” አሉ፡፡ ይሄኔ የመጀመሪያው፤ “ሱልጣን ሆይ ፍርዴን የሚያስነሳልኝ አንድ ሀሳብ ላቅርብ?” ሲል ጠየቀ፡፡ “ሀሳብህን እንስማ ተፈቅዶልሃል” አሉ ሱልጣኑ፡፡ “ሱልጣን ሆይ! የሚወዱት ፈረስዎ በአንድ ዓመት ውስጥ ክንፍ አውጥቶ መብረር እንዲችል እንዳስተምረው ይፈቀድልኝ?” ሲል ጠየቀ፡፡ ሱልጣኑ ፈረሳቸው ክንፍ አውጥቶ ተቀምጠውበት ከዓለም በላይ ሲበሩ ታያቸውና፤ “መልካም፤ እስከዚያው የሞት ቅጣቱ ይዘግይ” ብለው አሻሻሉት፡፡ ወንጀለኞቹ ወደማረፊያቸው እንደደረሱ ሁለተኛው ተከሳሽ ጓደኛውን ጠየቀው፡፡ “ስማ፤ ፈረሶች ክንፍ አውጥተው እንደማይበሩ ታውቃለህ፡፡ እንዲህ ያለ የዕብድ ሀሳብ ለምን ታቀርባለህ? የማይቀርልንን ሞት ማዘግየትስ ምን ይጠቅማል?” ሲል ጠየቀው፡፡ አንደኛው ተከሳሽም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “እንደሱ አይደለም ወዳጄ፡፡ ነፃ ለመውጣት አራት ዕድል እየሞከርኩ ነው፡፡ አንደኛ - ማን ያውቃል እስከ አንድ ዓመት ንጉሱ አንድ ነገር ይሆኑ ይሆናል፡፡

ሁለተኛ - እኔም እራሴ እሞት ይሆናል ሦስተኛ - ወይ ፈረሱ ይሞት ይሆናል አራተኛ - ወይ ምናልባት ተሳክቶልኝ ፈረሱን መብረር አስተምረው ይሆናል!”

                                                  * * *

ጊዜ መግዛት የብልሆች ዘዴ ነው፡፡ ብዙ ዕድሎች እያሉን ጊዜ መግዛት ባለመቻላችን ብቻ የሚይመልጡን አያሌ ነገሮች አሉ፡፡ የዲሞክራሲያዊ ተቋማትን ያለ ዲሞክራሲ ኃይሎች መገንባት አንችልም፡፡ ዲሞክራሲን የሚያራምድ ኃይል እንደሚያስፈልግ ሁሉ፣ የሚሸከም አካልም ሊኖር ያሻል፡፡ ያ ደግሞ በፈንታው መልካም መደላድልን ይጠይቃል፡፡ ከመደላደሎቹ አንዱ ባህሉን በቅጡ ማወቅ፣ ተዛማጅ ትርጉም መስጠትና ማዋሃድ፤ ሶሲዮ-ኢኮኖሚውን መመርመርና አብሮ ዕሳቤ ውስጥ ማስገባት፤ ከሁሉም በላይ ግን፤ አስተሳሰባችንን የምንቀርፅበት ወሳኝ መሠረት ትምህርት መሆኑን መረዳት ነው፡፡ የዕውቀት ሰዎቻችንን ካላከበርን አገራችንን አናከብርም የሚባለው ለዚህ ነው! ለነዚህ ሁሉም መጠንጠኛቸው ጊዜ ነው! ጊዜን ለቅፅበትም ለዘለዓለምም አብዝቶ መጠቀም የሚችል ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ አዕምሮውን በቀለም ያነፀ “እንደወዶ-ገባ ኮርማ፣ ተነስ ሲሉት የማይነሳ፣ ተኛ ሲሉት የማይተኛ”፣ ልበ-ሙሉና በራሱ የሚተማመን ወጣት ካለን ወይም ካፈራን፤ ጊዜ የእሱ ናት፡፡

ስለ ሀገር የመቆርቆሪያ፣ ስለ ዕድገት የማሰቢያ ጊዜ ሊገባው የሚችል ተረካቢ ትውልድ አለን ማለት ነው፡፡ ለዚህ ወጣት እንደኛ ያለችው ደሀ አገር ከቶም ሜዳ አትሆንለትም፡፡ አቀበቷ፣ አባጣ ጐርባጣዋ፣ ጠመዝማዛ አንጋዳዋ ስለሚበዛ፤ ሁሌ በቀለበት መንገድ የሚሄድባት አገር አትሆንለትም፡፡ የቀደሙትን ቢከተልም፣ እነሱም በወርቅ አልጋ በእርግብ ላባ ላይ ተኝተው ያደሩባት አገር እንዳልሆነች ይረዳል፡፡ እጓለ ገብረ ዮሐንስ የተባሉ የሀገራችን የትምህርት ሊቅ፤ ታዋቂውን ገጣሚ ዳንቴን ጠቅሰው አንድ ግጥሙን እንዲህ ያቀርቡልናል፡፡ “ወጣቶች አነሱ ግንባራቸውን፤ ሊጠይቁ (እ)ኛን “ታውቁት እንደሆነ እስኪ ንገሩን ባቀበቱ ዙሪያ መንገድ ይኖረን፤ ቪርጂልዮ መለሰ እንዲህም አላቸው መስሎአችሁ ይሆናል እኛ የምናውቀው ምንገደኞች ነነ እኛም እንደናንተው ትንሽ ቀደም አልንይ የደረስን አሁን ነው መንገዳችን ሌላ፤ የባሰ ከናንተው (ቀጥ ያለ አቀበት ነው እንቅፋት የመላው) እንግዲህስ መውጣት ለኛ መቅለሉ ነው፡፡

(መካነ ንስሐ፤ መዝሙር 2) ወጣቱ የራሱ ጊዜ ይኑረው ሲባል ያባቱን ሞት ጠባቂ፣ ቅርስ ናፋቂ የማይሆንበት አትሁን ማለታችን ነው አገሩን አገር በራሱ እጅ ያንጽ፣ በራሱ ወቅት ይጠቀም ማለት ነው፡፡ “ካላለፍነው ትላንት የለም፣ ካልኖርነው ዛሬ የለም፡፡ ካላቀድነው ነገ የለም” የሚሉት ፀሐፍት ለአፍ አመል አይደለም፡፡ የማያስብ፣ የማይሰራ፣ ችግሩን አስቦ፣ መላ መትቶ የማይፈታ ትውልድ ነገ የለውም፡፡ ጠያቂ ትውልድ መፈጠር አለበት፡፡ ፖለቲካውን፣ ኢኮኖሚውን፣ ባህሉን፣ በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ የሚመረምር፣ ንቃተ - ህሊናው የዳበረ ትውልድ ሊኖር ይገባል፡፡ የአበውን ቁምነገር የማይዘነጋ፣ የሚጥል - የሚያነሳውን ኑሮ የተገነዘበ ወጣት ትውልድ፤ አገር አለኝ የማለት አቅም ይኖረዋል፡፡ “ከመሠረት ጋር አትጣላ ለሁልጊዜ ይሆንሃል፡፡ ካብ ጋ አትጠጋ እላይህ ላይ ይፈርሳል” የሚለውን የአበው አነጋገር ልቡ ላይ ሊያትም ይገባዋል፣ የምንለው፤ ያን መሳይ ወጣት ይኖረን ዘንድ አበክረን በማሰብ ነው፡፡

በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች አሸንፈናል” - ተቃዋሚዎች ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የከተማ ምክር ቤቶች ምርጫ ኢህአዴግ ጊዜያዊ ውጤት በመጥቀስ በሁሉም ቦታዎች እንዳሸነፈ የገለፀ ሲሆን በምርጫው የተሳተፉ ተቃዋሚዎች በውጤቱ እርግጠኛ ባይሆኑም በጥቂት የአዲስ አበባ ምክር ቤት ቦታዎች የምናሸንፍ ይመስለናል ብለዋል፡፡ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ አየለ ጫሚሶ “ህዝቡ ጥሩ ድምጽ እንደሰጠን እናውቃለን፡፡ ውጤቱን በተመለከተ ግን የምርጫ ቦርድ ይፋ ካደረገ በኋላ የምናየው ይሆናል” ብለዋል፡፡ አቶ አየለ አክለውም በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች እጩዎቻቸው አሸናፊ እንደሆኑ ነገር ግን የመጨረሻውን ውጤት በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የሚወሰን ስለሚሆን የምርጫ ቦርድ መግለጫ መጠበቅ የግድ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

አቶ አየለ በሂደቱ ላይ የታዩ ብዙ ችግሮች እንደነበሩ ገልፀው፣ ከነዚህ መካከል የንብ ምልክት ብቻ በየጣቢያው መቀመጡ እንዲሁም በድምጽ ቆጠራ ወቅት የእነሱ ታዛቢዎች እንዳይገኙ መደረጋቸው ተገቢ አይደለም፤ ቅሬታችንን በወቅቱ ለምርጫ ቦርድ አቅርበናል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ) ፕሬዚዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ በበኩላቸው፣ በምርጫው ውጤት እንዳልቀናቸው ማረጋገጣቸውን ጠቅሰው፣ ፓርቲያቸው በምርጫው መሳተፉን ይበልጥ ከህብረተሰቡ ጋር እንዲተዋወቅ እንዳደረገው ገልፀዋል፡፡ የምርጫው አጠቃላይ ሂደትና ውጤት በተመለከተ ያላቸውን አቋምም በምርጫ ቦርድ ውጤቱ ይፋ ከተደረገ በኋላ እንደሚያሳውቁ አቶ ተሻለ ገልፀዋል፡፡ የመላው ኢትዮጵያ ብሔራዊ ንቅናቄ (መኢብን) ሊቀመንበር አቶ መሣፍንት ሽፈራው፤ በአዲስ አበባ በሶስት የምርጫ ጣቢያዎች ቢያሸንፉም አጠቃላይ ውጤቱን ለማወቅ የምርጫ ቦርድን መግለጫ እንጠብቃለን ብለዋል፡፡

ኢህአዴግ በበኩሉ በአዲስ አበባ ሙሉ ለሙሉ የአሸናፊነት ድምጽ አግኝቻለሁ ብሏል፡፡ በኢህአዴግ ጽ/ቤት የአደረጃጀትና የአጋር ድርጅቶች ዘርፍ ሃላፊ አቶ ተመስገን ጥላሁን በሰጡት ማብራሪያ፣ የምርጫው አጠቃላይ ውጤት የሚታወቀው በቦርዱ ይፋ ሲደረግ ቢሆንም አሁን ባለው ጊዜያዊ ውጤት ግን በሁሉም የምርጫ ወረዳዎች አሸንፈናል ብለዋል፡፡ ምርጫው ኢህአዴግ ባሰበው መንገድ ዲሞክራሲያዊ ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ ተጠናቋል ያሉት አቶ ተመስገን፤ ነገ እሁድ የሚካሄደው የወረዳ ምርጫ ሲጠናቀቅና ምርጫ ቦርድ ውጤቱን ይፋ ሲያደርግ ምርጫውን በተመለከተ አጠቃላይ መግለጫ እንሰጣለን ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የአዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌታሁን ገ/መድህን በበኩላቸው በምርጫው የተገኘው አጠቃላይ ውጤት ግንቦት 2ቀን 2005 ዓ.ም ይፋ ሲደረግ በአዲስ አበባ በየክልሉ የተገኘው ደግሞ ሚያዚያ 16 ቀን 2005 ዓ.ም ይፋ እንደሚደረግ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ ባለፈው ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ የነበሩ ተቃዋሚዎች ራሳቸውን ከምርጫው ማግለላቸው ይታወቃል፡፡

የስነተዋልዶ ጤና ምንነት በአለም አቀፍ ደረጃ ተመሳሳይ ቢሆንም ምክንያቶቹ ግን በታዳጊ አገሮች በአብዛኛው የተለዩ ናቸው፡፡ በታዳጊ አገሮች የሚገኙ እናቶች በ 5/ማይል እርቀት የጤና ጣቢያ ካገኙ ደስተኞች ናቸው፡፡ በታዳጊ አገሮች የሚገኙ እናቶች ጤና ጣብያው ምንግዜም በስራ ላይ ሆኖ ከቆያቸውና ለታካሚዎች በቂ ምላሽ የሚሰጡ ሙያተኞች እንዲሁም የተሟላ አቅርቦት በጤና ተቋሙ ካለ ደስተኞች ናቸው፡፡ ብዙውን ጊዜ ከላይ የተጠቀሱት ሁነቶች ተሟልተው የሚገኙ ባለመሆኑ የስነተዋልዶ ጤና አገልግሎት የተጉዋደለ ይሆናል፡፡ በታዳጊ አገሮች የተለያዩ መሰረተ ልማቶች...ለምሳሌ...እንደ መንገድ የጤና ተቋም በቅርበት አለመኖር የትራንስፖርት ችግር የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ጉዳዮች የመሳሰሉት ካልተሙዋሉ እናቶች ወደ ጤና ተቋም በጊዜው ሄደው እርዳታ እንዳያገኙ ያደርጋቸ ዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የስነተዋልዶ ጤና በሴትና በወንድ በባልና ሚስት መካከል ባለው መቀራረብና ለውይይት መገባበዝም ሁኔታው እንደማሻሻል ሙያተኞች ይመሰክራሉ፡፡ ቀጣዩን የተሳታፊ መልእክት ታነቡ ዘንድ እንጋብዛለን፡፡

.....እህ የምትኖረው በደብረማርቆስ ከተማ ሲሆን በህመም ምክንያት ባልተቤቷ ወደ እኔ ማለትም ወደአዲስ አበባ ይዞአት መጣ፡፡ ሁኔታዋን ከተመለከትኩ በሁዋላ ለባልተቤቷ ጥያቄዬን ሰነዘርኩ፡፡ ጥ: ባልተቤትህ ምንዋን ነወ ያመማት? መ: እኔ እንጃ... ጥ: እንዴት እኔ እንጃ? ሚስትህ ምንዋን እንደሚያማት አታውቅም እንዴ? መ: አረ እኔ አላውቅም... ጥ: አልጠየቅሀትም? መ: እኔም አልጠየቅሁዋት...ብጠይቃትም አትነግረኝ... በባልተቤቷ አመላለስ በጣም ተበሳጨሁና...ፊን ወደእህ መለስኩ፡፡ ጥያቄየን ገና ሳልጀምር ...ና ተነስ አብዬ...አለችኝ እና ወደጉዋሮ ተያይዘን ሄድን፡፡ ጥ: ፈልገሽኝ ነው አልኩዋት... መ: እናስ...እንዴ...እሱ ፊት ምን ልትጠይቀኝ ነው ብዬ እኮ ነው? ጥ: እንዴ እኔ ምን እጠይቅሻለሁ...የመጣሽው ታምመሽም አይደል እንዴ? ምንሽን ነው የታመምሽው ነው የምልሽ? መ: አ...አ...ይ...ሕመሙንም ቢሆን ለሚስትህ ነግሬያት የለ...እሱዋ ትንገርህ...ዪ...እኔስ ምኑንም አላውቀውም... አለችኝ፡፡ እህን ከባለቤቴ ባገኘሁት መረጃ መሰረት ወደማህጸን ሐኪም ወሰድኩዋት፡፡

እዚህ ላይ ለመናገር የምፈልገው በተለይም በገጠር አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች በግልጽነት መነጋገር ስለማይችሉ ሕመማቸው ስር ከሰደደ በሁዋላ ወደሕክምና ይሄዳሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ካለውጤት ብዙዎች ይጎዳሉ፡፡ ተሳታፊ የስነተዋልዶ ጤና በታዳጊ አገሮች የሚለው ርእስ ሊያሳይ የፈለገው በመንግስት ወይንም ሌሎች በሚመለከታቸው አካላት ሊሟሉ የሚገባቸውን ነገሮች ሳይሆን ከዚያ ውጪ ህብረተሰቡ በልማድ የሚፈጽማቸውን ነገሮች ነው፡፡ ለዚህ ማብራሪያ የሚሰጡን ዶ/ር ዳዊት ደሳለኝ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ፋክልቲ መምህርና የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት ናቸው፡፡ እንደ ዶ/ር ዳዊት ማብራሪያ በታዳጊ አገሮች የሚገለጹ ችግሮች በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ የተለያዩ ሲሆኑ ከነዚህም መካከል ትምህርት ማጣትና ድህነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ አንዲት ሴት ትምህርትን የተቋደሰች ከሆነች በብዙ መልኩ በጤናዋ ላይ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ ነገሮችን አስቀድማ መከላከል ትችላለች፡፡

ያልተፈለገ እርግዝናን መከላከል፣ ጥንቃቄ የጎደለው ጽንስ ማቋረጥን ማስወገድ፣ ተላላፊ ኤችአይቪ የሆኑትን ሕመሞች ለመከላል የሚያስችሉ ነገሮችን አስቀድሞ ለማወቅ፣ በኢኮኖሚው ረገድ ጥገኝነትን ለማስወገድ እንዲረዳ አቅም የፈቀደውን ስራ መስራት፣ የግል ንጽህናን መጠበቅ ...ወዘተ ከላይ የተጠቀሱትንና ሌሎችንም ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ከስነተዋልዶ ጤና አኩዋያም ሆነ ለማንኛውም የአኑዋዋር ዘዴ ለማስተካከል እንዲቻል ትምህርት ወሳኝነት አለው፡፡ ድህነት ከስነተዋልዶ ጤና አጠባበቅ አንጻር ጎጂ የሚሆንባቸው መንገዶች የሚኖሩ ሲሆን በተለይም አስቀድሞውኑ ሕመሙ እንዳይከሰት ለማድረግ እና ከተከሰተም በሁዋላ በፍጥነት ወደሕክምና ተቋም ለመሄድ እንቅፋት የሚሆንበት አጋጣሚ ይስተዋላል፡፡ በኢ ኮኖሚው በዝቅተኛ ደረጃ የሚኖሩ ሰዎች እራቅ ወዳለ አካባቢ ለመሄድ ለትራንስፖርት የሚከፍሉት ስለማይኖራቸው የሚከሰተውን ችግር መቀበልን ይመርጣሉ፡፡

ይህ ደግሞ በቀጣዩ የህይወት አቅጣጫቸው ላይ አንድ እክል እንደሚሆን አያጠራጥርም፡፡ እንደ ዶ/ር ዳዊት ደሳለኝ የስነተዋልዶ ጤናን ከአገር ወደህብረተሰብ እንዲሁም ወደቤተሰብ ዘልቆ ገብቶ ሲታይ ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ ነገሮች ጫና የሚያሳድ ሩበት ሁኔታ ይታያል፡፡ የስነተዋልዶ ጤና ጉዳይ የሴቶች ብቻ ሳይሆን የወንዶችም ጉዳይ ነው፡፡ በእርግጥ በአብዛኛው ሲጎዱ የሚታዩት ሴቶች ቢሆኑም ወንዶቹም የሚያጋጥማ ቸው ችግር እንደሚኖር እሙን ሲሆን በተለይም በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመፍታት የወንዶች ተሳታፊን በእጅጉ ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ በሚፈጠሩ የጤና እክሎች ላይ በግልጽ መወያየት የአንድ ባልና ሚስት ተግባር መሆን አለበት፡፡ ሴቶችና ወንዶች ለሚያስፈልጉዋቸው ማናቸውም የኑሮ ሁኔታዎች በእኩል መወሰን መቻል አለባቸው፡፡ ሴቶች ከባሎቻቸው ጋር በተለይም ከስነተዋልዶ ጤና ጋር በተያያዘ መወሰን የሚገባቸው እና በቀጥታ ከሕይወታቸው ጋር ተያያዥ የሆኑ ነገሮች ያሉ ሲሆን ከነዚህም መካከል የሚወለዱ ልጆችን ቁጥር እና በምን ያህል የጊዜ ልዩነት መውለድ እንዳለባቸው አስቀድሞ መወሰን ይገኝበታል፡፡

አንዲት ሴት ልጅ የምትወል ድበትን ጊዜና ሊኖራት የሚገባውን የልጅ ቁጥር በወንዱ የገቢ አቅም ላይ ተመርኩዛ ብቻ ሳይሆን ከእራስዋም ጤና አንጻር ልትመለከተው ይገባታል፡፡ ይኼውም በላይ በላይና ብዙ ልጅ በመውለድ እየዋለ እያደረ የሚከሰተውን የስነተዋልዶ ጤና ችግር አስቀድማ ልትከላከል ትችላለች፡፡ የቤት ውስጥ ጥቃት ሌላው ለስነተዋልዶ ጤና ችግር የሚዳርግ ድርጊት ነው፡፡ የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያስረዱት 50 ኀ ሴቶች የቤት ውስጥ ጥቃት ሰለባ ናቸው፡፡ የቤት ውስጥ ጥቃት ሲባል አካላዊ፣ መንፈሳዊ ፣ኢኮኖሚያው ተብሎ ሊከፈል የሚችል ሲሆን አካላዊ ጥቃት ከሚባሉት ውስጥ አስገድዶ መድፈር አንዱ ነው፡፡ ይህ አጋጣሚ በሴቶች ላይ የስነአእምሮ እና የአካል ችግር ያስከትላል፡፡ በዚህ መንገድ የተጎዱ ሴቶች ባጠቃላይ እራሳቸውን ማግለልና ዝቅ ማድረግ ይታይባቸዋል፡፡ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች የሚባሉት እንደ ጠለፋ ግርዛት እና በቤት ውስጥ ልጅን ማዋለድ የመሳሰሉት ሌሎች የስነ ተዋልዶ ጤናን የሚፈታተኑ ድርጊቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ድርጊቶች በቤት ውስጥ ሚፈጸሙ ሲሆኑ በቤት ውስጥ ያለው አስተሳሰብ ሲቀየር ግን ችግሩም ሊቃለል እንደሚችል ይታመናል፡፡ ውፍረት ሴቶችን ለስነተዋልዶ ጤና ችግር ከሚያጋልጡ መካከል ናቸው፡፡ አመጋገብን ከመጠን በታችም ሆነ ከመጠን በላይ ማድረግ ጎጂ መሆኑ የተመሰከረለት ነው፡፡ ስለዚህ አካልን በተገቢው መንገድ እንቅስቃሴ በማድረግ መጠበቅ ጠቃሚ ነው፡፡

የግል ጽዳትን መጠበቅ የስነተዋልዶ ጤናን ከመጠበቅ አኩዋያ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ የመራቢያ አካልን እና አካባቢውን በተገቢው መንገድ አለማጽዳትም ሆነ ከተገቢው በላይ ማጽዳት ጎጂ መሆኑን አስቀድሞ ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ በመራቢያ አካል አካባቢ በተፈጥሮ የሚገኙ ባክሪያዎች ኢንፌክሽንን የሚከላከሉ ስለሆነ በኬሚካሎችና በመሳ ሰሉት በመጠቀም አለአግባብ ማስወገድ ለችግር ያጋልጣል፡፡ ዶ/ር ዳዊት በስተመጨረሻ እንደሚሉት የስነተዋልዶ ጤናን ሁኔታ ሰፋ አድርጎ ለመመልከት ቢሞከር በአገራችን ብዙ የተሸሻሉ ነገሮች አሉ፡፡ የእርግዝና ክትትል ማድረግ፣ በጤና ተቋም እና በህክምና ሙያተኛ እርዳታ መውለድ ፣ ከወለዱም በሁዋላ ክትትል ማድረግ፣ የቤተሰብ እቅድ ዘዴ ተጠቃሚ መሆን...ወዘተ ... ከላይ በተጠቀሱትና የጤና ኤክስንሽን ሰራተኞች በየአካባቢው መኖር እንዲሁም የጤና ጣቢያዎች መገንባት በመሳሰሉት ምክንያቶች መሻሻሎች የሚታዩ ቢሆንም ነገር ግን ገና ብዙ መሰራት ያለበቸው ነገሮች እንዳሉ ሁኔታዎች ያሳያሉ ብለዋል ዶ/ር ዳዊት ደሳለኝ፡፡

ባለፈው ረቡዕ በደሴቲቷ አገር በኢንዲያን ኦሽን ትልቅ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን ተዘጋጅቶ ነበር - ውድ ውድ የከበሩ ድንጋዮችና የአልማዝ ጌጣጌጦች የቀረቡበት፡፡ ለዚህም ከቻይና፣ ከሆንግኮንግ፣ ከታይላንድ፣ ከህንድ እና ከአውሮፓ የመጡ ገዢዎች በኤግዚቢሽኑ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ በዚህ ግርግር መሃል ነው ፖሊስ አንዱን የቻይና ቱሪስት በስርቆት ጠርጥሮት በቁጥጥር ሥር ያዋለው፡፡ ቱሪስቱ 171 ሺ ብር ገደማ የሚያወጣ አልማዝ (diamond) ውጠሃል በሚል ነበር የተጠረጠረው፡፡ “ዓላማው መስረቅ ነበር” ሲል ለሮይተርስ የተናገረው የስሪላንካ ፖሊስ ቃል አቀባይ አጂት ሮሃና፤ በኤክስሬ መመርመርያው በጉሮሮው ውስጥ የነበረውን አልማዝ ማየት እንደቻለ ገልጿል፡፡ የ32 ዓመቱ ቻይናዊ ቾው ቼንግ አልማዙን በኤግዚቢሽኑ ላይ እየተመለከተ ሳለ እንደዋጠው ታምኗል፡፡

ኤግዚቢሽኑ የተካሄደበት አዳራሽ ባለቤት ክሪስቶፈር ዊጅኩን በበኩሉ፤ ቻይናዊው ቱሪስት ኦሪጂናሌውን አልማዝ በሲንቴቲክ አልማዝ ለመለወጥ እንደሞከረ ለሮይተርስ ተናግሯል፡፡ “እኔ እንዳስተዋልኩት ገባውና ከመቅጽበት አልማዙን ዋጠው” ብሏል ዊጅኩን ለሮይተርስ፡፡ የኢንዲያን ኦሽን ደሴት በአልማዞችና በጌጣጌጥ ኢንዱስትሪዋ የታወቀች ስትሆን በ2011 እ.ኤ.አ የኤክስፖርት ገቢዋ 532 ሚ .ዶላር እንደነበር ሮይተርስ ጠቁሟል፡፡ ይሄ የፈረደበት ቻይናዊ እንግዲህ የዋጠውን አልማዝ እስኪተፋ ድረስ መከራውን መብላቱ አይቀርም፡፡ የሌብነት መዘዝ ይሄው አይደለ!!

ከ1ሺ ኪ.ግ በላይ ይመዝናል በርገሩን ለመስራት 4 ሰዓት ፈጅቷል በአሜሪካ የሚኒሶታ ግዛት ውስጥ የሚገኝ አንድ ካዚኖ ቤት (ቁማር ማጫወቻ) እጅግ በጣም ትልቁንና ከፍተኛ ክብደት ያለውን ቺዝበርገር በመስራት በጊነስ የድንቃድንቅ መዝገብ ውስጥ ስሙን አሰፈረ፡፡ ከቤከን የተሰራው ቺዝበርገር 10 ጫማ ስፋት ሲኖረው ከ1ሺ ኪ.ግ በላይ ክብደት እንዳለው ታውቋል፡፡ (ከ10 ኩንታል በላይ ማለት ነው) “ዛሬ ያየሁት አስደናቂ የቡድን ሥራ ያስገኘውን የዓለም ክብረወሰን የሰበረ በርገር ሲሆን ጣዕሙም በጣም አሪፍ ነው” ሲሉ የጊነስ ሪከርድስ ተወካይ ፊሊፕ ሮበርትሰን ለአሶሼትድ ፕሬስ ተናግረዋል፡፡ በርገሩ በአጠቃላይ ዳቦውንና ማሰማመሪያዎቹን ጨምሮ 2ሺ 14 ፓውንድ ክብደት እንዳለው የዘገበው ዱሉዝ ኒውስ ትሪቡን፣ ቀድሞ የተመዘገበው የበርገር ክብደት 881 ፓውንድ እንደ ነበር ጠቅሷል፡፡

በብላክ ቢር ካዚኖ ሪዞርት የሚሰሩ ሼፎች ግዙፉን ቺዝበርገር ለማሰናዳት አራት ሰዓታት እንደፈጀባቸው ታውቋል፡፡ በርገሩ ከ33 ኪ.ግ ቤከን፣ 23 ኪ.ግ ሰላጣ፣ 23 ኪ.ግ በስላች የተቆረጠ ሽንኩርት፣ 13 ኪ.ግ ኩከምበር እና 13 ኪ.ግ ቺዝ የተሰራ ሲሆን የበርገሩን ዳቦ ለመጋገር ብቻ ሰባት ሰዓት እንደወሰደ ታውቋል፡፡ አሶሼትድ ፕሬስ በስፍራው ተገኝቶ እንደተመለከተው፤ በርገሩን ለማንሳት ክሬን አስፈልጐአቸው ነበር፡፡ በርገሩ የተሰራውም በውጭ ምድጃ (outdoor oven) እንደሆነ ታውቋል፡፡

ቻይናዊው ሁ ሴንግ አንዲት የሚወዳት ፍቅረኛ አለችው፡ እናም ፍቅሩን ለመግለፅ ብቻ ሳይሆን Surprise ሊያደርጋት (ሊያስደምማት) ያስብና ትንሽ ይቆዝማል - ሃሳብ እያወጣ እያወረደ፡ ብዙዎቹ የመጡለትን ሃሳቦች አናንቆ ጣላቸው - ፍቅረኛውን ለማስደመም ብቃት እንደሌላቸው በመቁጠር፡፡ በአዕምሮው የሃሳብ ጅምናስቲክ ሲሰራ ቆይቶ ግን አንዲት ሃሳብ አንጀቱ ላይ ጠብ አለችለት፡፡ ሃሳቡን ለመተግበርም ሲበዛ ተጣደፈ፡፡ ፍቅረኛውን ሊያስደምምበት በወጠነው ሃሳብ እሱ ራሱ ቀድሞ ተደመመና ቁጭ አለ፡፡ ከድማሜው ሲወጣ ሃሳቡን ወደ ተግባር ለውጦ የማሰቡን በረከት ሊቋደስ ቋመጠ፡፡ በቻይና የቾንኪዊንግ ግዛት ነዋሪ የሆነው ሴንግ፤ ፍቅረኛውን በምን ሰርፕራይዝ እንደሚያደርጋት ለማንም አልተናገረም፡፡ ምስጢር ነው - እሱና እሱ ብቻ የሚያውቁት፡፡ ፍቅረኛውም የምታውቀው ሰርፕራይዝ ከተደረገች በኋላ ይሆናል፡፡ ሁሴንግ በቀጥታ የሄደው እንደ ዲኤች ኤል ያለ ፈጣን መልዕክት አድራሽ ተቋም ጋ ነበር፡፡ እዚያም እንደደረሰ ስለሚያደርሱት እቃ ወይም መልዕክት ምንነት ሳይናገር በካርቶን የታሸገ ስጦታ እፍቅረኛው ቢሮ እንዲወስዱለት ብቻ ተነጋገረና ተስማማ፡፡ የአገልግሎት ክፍያውንም ሳያቅማማ ፈፀመ፡፡

ለፍቅረኛው ሊልክላት ያሰበው ስጦታ አበባ አልነበረም፡፡ ጫማ፣ ወርቅ፣ አልማዝ ወይም ወድ አልባሳትም አይደለም፡፡ ለፍቅረኛው ለመላክ ያሰበው ራሱን ነው፡፡ በዚህ ነው የሚወዳትን ፍቅረኛውን ማዝናናትና ማስደመም ያማረው፡፡ እናም መልዕክቱን የሚያደርሱት የድርጅቱ ሠራተኞች ወደ ቤቱ ከመምጣታቸው አስቀድሞ ራሱን እንደ ስጦታ እቃ በካርቶን ውስጥ አሳሽጐ ጠበቃቸው፡፡ መልዕክት አድራሾቹ “አገር አማን” ብለው በተለመደ ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጣቸው፣ በአደራ የተሰጣቸውን እቃ ወደተባሉበት ሥፍራ ለማድረስ ከነፉ - በዘመናዊ ፈጣን አውቶሞቢላቸው፡፡ ሆኖም መሃል ላይ የቴክኒክ ችግር ገጠማቸው፡፡ የአድራሻ ስህተት ተፈጠረ፡፡ ይሄ ስህተት ደግሞ ከሁሉም በላይ ራሱን በካርቶን ውስጥ ላሳሸገው ምስኪኑ ሴንግ ከባድ ፈተና ነበር - የህይወት መስዋዕትነት እስከማስከፈል የሚደርስ፡፡ ሴንግ በካርቶኑ ውስጥ ታሽጐ የሚቆየው ቢበዛ ለ30 ደቂቃ ያህል መስሎት ነበር፡፡

በተፈጠረው የአድራሻ ስህተት ግን ጊዜው ወደ 3 ሰዓታት ተራዘመበት፡፡ ጉድ ፈላ - ሴንግ! ካርቶኑ ውስጥ በአየር እጦት ተሰቃየ፡፡ የማታ ማታ ግን እሽጉ ካርቶን እፍቅረኛው ቢሮ መድረሱ አልቀረም፡፡ ፍቅረኛው ካርቶኑን ለመክፈት ስትጣደፍ፣ የሥራ ባልደረባዋ ደግሞ ሰርፕራይዙን ቀርፃ ለታሪክ ለማስቀመጥ ካሜራዋን ደግና እየተጠባበቀች ነበር፡፡ ካርቶኑ ሲከፈት ግን ሰርፕራይዝ የሚያደርግ ሳይሆን በድንጋጤ ክው የሚያደርግ ነገር ገጠማቸው፡፡ ሁ ሴንግ ካርቶኑ ውስጥ ሩሁን ስቷል፡፡ በአየር እጥረት ታፍኖ፡፡ በስጦታ ሰርፕራይዝ ለመደረግ ቋምጣ የነበረችው ፍቅረኛው፤ ህይወቱን ለማትረፍ ተጣድፋ የድንገተኛ ህክምና ባለሙያዎችን አስጠራች፡፡ የህክምና እርዳታ ካገኘ በኋላ ሴንግ ነፍሱ ተመለሰችለት፡፡

“ጉዞው ያንን ያህል ረዥም ጊዜ ይወስዳል ብዬ አላሰብኩም ነበር” ያለው የዋሁ አፍቃሪ፤ “በእሽጉ ካርቶን ውስጥ ሆኜ አየር የማገኝበት ቀዳዳ ለማበጀት ሞክሬ ነበር፤ ሆኖም ካርቶኑ በጣም ወፍራም ስለሆነ አልቻልኩም፤ ጩኸት እንዳላሰማ የነገሩን ድንገቴነት (Surprise) ማበላሸት አልፈለግሁም” ብሏል፡፡ የመልዕክት አድራሹ ድርጅት ቃል አቀባይ በበኩሉ፤ “ገና ከመጀመርያው ምን እንዳሰበ ቢነግረን ኖሮ እሽጉን አንወስድለትም ነበር፤ እንስሳትን እንኳን ለማጓጓዝ ስንቀበል አየር ማግኘት እንዲችሉ በተለየ መያዣ ውስጥ ነው የምናደርጋቸው” ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል - ለኦሬንጅ ኒውስ፡፡ አይገርምም! ፍቅረኛውን ለማስደመም ሲል ህይወቱን ሊያጣ ለጥቂት እኮ ነው የተረፈው፡፡ ካልጠገቡ አይዘሉ፤ ካልዘለሉ አይሰበሩ የሚለው ሀገራዊ አባባል ለቻይናዊው ሁ ሴንግ አይሰራ ይሆን?!

በእባብ የተነደፈ የኔፓል ተወላጅ እባቡን መልሶ በመንከስ ብድሩን እንደመለስ ሰሞኑን ተዘግቧል፡፡ ሮይተርስ የኔፓል ዕለታዊ ጋዜጣ አናፑርና ፖስትን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ ሞሃመድ ሳልሞ ሚያ የተባለውን ግለሰብ ኮብራ እባብ የነደፈው በሩዝ ማሳ ውስጥ ነበር፡፡ ሞሃመድ ግን ዝም አላለም፡፡ የገባበት ገብቶ በመያዝ ነክሶ ገድሎታል - እባቡን፡፡ “በዱላ ልገድለው እችል ነበር፤ ነገር ግን በጥርሴ ነክሼ ገደልኩት፤ ምክንያቱም ተናድጄ ነበር” ብሏል ከአገሪቱ መዲና ከካትማንዱ ደቡብ ምስራቅ 200ኪ.ሜ ላይ በምትገኘው መንደር የሚኖረው የ55 ዓመቱ ሞሃመድ፡፡ በኔፓል “ጐማን” እየተባለ የሚጠራው ይሄ የእባብ ዝርያ “ኮመን ኮብራ” በሚል ስያሜም ይታወቃል ብሏል አናፑርና ፖስት፡፡ በእባቡ የተነደፈው ሞሃመድ ሳልሞ ሚያ፤ በመንደሩ የጤና ጣቢያ ህክምና እየተደረገለት ሲሆን ለህይወቱ እንደማያሰጋው ተገልጿል፡፡

እባቡ በኔፓል በመጥፋት ላይ ካሉ የማያጠቡ እንስሳት ዝርያ ዝርዝር ውስጥ የተካተተ ባለመሆኑ እባቡን ነክሶ የገደለው ግለሰብ ከክስ እንደዳነ የአካባቢው ፖሊስ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡ እንዲያ ባይሆን ኖሮማ እባቡን ነክሶ በመግደሉ ፍ/ቤት ይቆማት ነበር ተብሏል፡፡ ይታያችሁ … ሞሃመድ እባቡን ነክሶ የገደለው ለአደን አይደለም - ስለነደፈው እንጂ፡፡ ቢሆንም በመጥፋት ላይ ያሉ እንስሳትን መግደል በኔፖል ያስጠይቃል ብሏል - ሮይተርስ፡፡