Administrator

Administrator

 በቀጣዩ ጥቅምት 13 ቀን 2011 በሂልተን ሆቴል ለሚካሄደው “ለዛ” የአድማጮች ምርጫ ሽልማት ለመጨረሻ ዙር ያለፉ ምርጥ አምስቶች ታወቁ፡፡ በዚህም መሰረት በየአመቱ ምርጥ ፊልም ዘርፍ “ወደኋላ”፣ “እርቅይሁን”፣ “በእናት መንገድ”፣ “ትህትናና” “ድንግሉ” ሲያልፉ በምርጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ፊልም ዘርፍ ደግሞ “ምን ልታዘዝ”፣ “ዘመን”፣ “ሰንሰለት”፣ “ደርሶ መልስ” እና “ቤቶች” ተመርጠዋል፡፡ በአመቱ ምርጥ ተዋናይ ዘርፍ አለባቸው መኮንን በ“ትህትና”፣ እንግዳሰው ሀብቴ በ“ሰራችልኝ”፣ ሔኖክ ወንድሙ በ“የፈጣሪ ጊዜ”፣ አለማየሁ ታደሰ በ“ድንግሉ” እና ኤርሚያስ ታደሰ በ“ታላቅ ቅናሽ” ማለፋቸውን የሽልማቱ አዘጋጅ ለዛ ሾው አስታውቋል፡፡
በየዓመቱ ምርጥ ተዋናይት ዘርፍ አዚዛ አህመድ በ“ትህትና” ዕፀህይወት አበበ በ“አስነኪኝ”፣ ሊዲያ ተስፋዬ በ“ወደኋላ”፣ አዲስአለም ጌታነህ በ“ሀ እና ለ 2”፣ እንዲሁም ፍናን ህድሩ በ“እርቅ ይሁን” ተመርጠዋል፡፡ በምርጥ የሙዚቃ ቪዲዮ ዘርፍም “የቤት ሥራ”፣ “የመጀመሪያዬ ነው”፣ የቴዲዮ “ሎኦ ሎኦ” “ትርታዬ”፣ የአቢ ላቀው “ሆዴን ሰው ራበው”ና የሄለን በርሄ “ፊት አውራሪ” ምርጥ አምስት ውስጥ ተቀላቅለዋል፡፡
በየዓመቱ ምርጥ አልበም ዘርፍ፣ የናቲማን ቁጥር 2 አልበም፣ የእሱባለው ይታዬው “ትርታዬ” የሮፍናን “ነፀብራቅ”፣ የብስራት ሱራፌል “ቃል በቃል”፣ የሄለን በርሄ “እስኪ ልየው”ና የጃኖ ባንድ “ለራስህ ነው” ሲያልፉ በምርጥ ነጠላ ዜማ ዘርፍ የሮፍናን “ጨረቃን” የያሬድ ነጉ “ዘለላዬ”፣ የአቡሽ ዘለቀና ቤኪግዕዝ “ማሎ ኢንተሎ”፣ የብስራት ሱራፌል “የቤት ሥራ” እና የናቲ ማን “የመጀመሪያዬ ነው” ወደመጨረሻው ዙር አልፈዋል፡፡
የመጨረሻውን ተሸላሚ ለመምረጥ በwww.lezashow.com ገብተው የሚያደንቁትን አርቲስት፣ ፊልም፣ ሙዚቃ ወይም ቪዲዮ መምረጥ እንዲችሉ የለዛ የሬዲዩ ፕሮግራም አዘጋጅ ጋዜጠኛ ብርሃኑ ድጋፌ ጥሪ አቅርቧል፡፡


    ታዋቂው ደቡብ አፍሪካዊ ኮሜዲያን ትሬቨር ኖዋህ በቅድመና ድህረ አፓርታይድ ስላሳለፈው የልጅነት ጊዜው ከፃፈው “Bora a crime stories from a south African childhood” ከተሰኘው መጽሐፍ የአመፃ ልጅ በሚል ወደ አማርኛ የተተረጐመው መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡
በጥላሁን ግርማ የተተረጐመው ይሄው መፅሐፍ የአፓርታይድን አስከፊነት በቀልድና በምፀት እያዋዛ ለአንባቢው የሚያቀርብ ሲሆን፤ በመፅሐፉ ውስጥ የደራሲው እናት ሥርዓቱን በመፋለም ሕግ ጥሳ ከነጭ የወለደችውን ልጅ እንዴት እንዳሳደገችውና ጐን ለጐንም የዘረኝነትን አስከፊነት በተለያዩ የመፅሐፉ ምዕራፎች ውስጥ እንደሚያስቃኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በ256 ገፅ የተቀነበበው መፅሐፉ በ130 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

 ትዳር ሲመሰረት በጉጉት የተጠበቀ የግብዣ ወይንም የሙዚቃ በአጠቃላይም የደስታ ስነስርአት ተካሂዶ ነው። አንድን ትዳር ወደትክክለኛው መስመር ለመምራት በዙሪያው ያሉ ዘመድ አዝማዶች በእጅጉ የሚደክሙበት በመሆኑ በኢትዮጵያ አንድ አባባል አለ፡፡እሱም ‹‹…አንዱ ሊያገባ ሌላው ገገባ…›› የሚል ነው፡፡ ይህም በሰርጉ ዙሪያ ያሉ ሰዎች ምን ያህል እንደሚደክሙ የሚያሳይ ነው፡፡ የተጋቢዎች ሁኔታ ደግሞ በወዲፊት ሕይወታቸው ላይ ጥሩ ተስፋ ሰንቀው…ልጅ ሊወልዱ… ሀብት ሊያፈሩ እና ከሞት በስተቀር ምንም ላይለያቸው ለየራሳቸው ቃል ገብተው እንዲሁም መች ነው አብረን የምንውለው የምናድረው ብለው በምኞት እራሳቸውን አዘጋጅተው የሚመሰርቱት ኑሮ ነው፡፡ ነገር ግን ለደስተኛ ትዳር መንገዱ እንደዚህ እንደሚመኙት ቀላል አይደለም፡፡ እንደ Kevin Miller  የስነ ልቡና ባለሙያ እማኝነት፡፡ ስለሆነም ምናልባት በትዳር ግንኙነት ላይ ሳንካ ሲፈጠር ሰዎች የሚያማርሩዋቸው ነገሮች ብዙ ሊሆኑ ይችላሉ ፡፡ የትዳርን ግንኙነት በጎ ለማድረግ የሚያስችል የሚነበብ መጽሐፍ ወይንም ጋዜጦች አለዚያም እንደሴሚናር ያሉ ስብሰባዎች፤ውይይቶች …ወዘተ የመሳሰሉ ነገሮችን መፈለግ ወይንም መጠበቅ አይቻልም፡፡ ነገር ግን ጥሩ ጊዜ ሲኖር ይቅርታ ማድረግ እና በሰከነ መንገድ መግባባት መቻል ደስተኛ ትዳርን ለመመስረት እጅግ ተፈላጊ ከሆኑ ነገሮች መካከል መሆናቸውን መርሳት አይገባም፡፡ እነዚህንና የመሳሰሉትን ነገሮች መተግበር ካልተቻለ በትዳር ላይ ጥልቅ የሆነ ችግር ሊከሰት እንደሚችልና ይህንን ችግር ሁለቱ ሰዎች ማለትም ተጋቢዎች መፍታት ካልቻሉ በምንም አይነት መንገድ ሶስተኛ ኃይል ወይንም ሌሎች ሰዎች ጣልቃ በመግባት ምናልባት መንገድ ሊጠቁሙ ይችሉ እንደሆን እንጂ ችግሩን ሊፈቱት እንደማይችል እሙን ነው፡፡
ትዳርን በትክክለኛው እና በጣፈጠ መንገድ ለመምራት ፍቅር ዋናው መሰረቱ ነው፡፡ ማፍቀር ሲባል ደግሞ አንዱ አፍቃሪ ለሌላው ከልቡ በትክክለኛው መንፈሱና አስተሳሰቡ መሆን አለበት፡፡ የብዙዎች ትዳር ውድቀት እነዚህን ነገሮች ካለማወቅ ወይንም ካለማሰብና ካለመተግበር የሚመጣ ነው ተብሎ ይታመናል፡፡ ተጋቢዎች አንቺ ትብሽ አንተ ትብስ ከመባባል ፈንታ ስለየራሳቸው ፍላጎትና አስፈላጊ ነገሮችን ስለማሟላት ማሰብ በሚጀምሩበት ወቅት በተከታይ የትዳራቸውን መውደቅ ጅማሬ ማየት ይሆናል፡፡
ተጋቢዎች በእርስ በርስ ግንኙነታቸው ላይ ችግር እንዳይፈጠር አንዳቸው የሌላውን ስሜት መረዳት፤ ፍላጎትን ማወቅ እና መተግበር ፤የራስ ወዳድነትን በማስወገድ መተሳሰብን፤ መፋ ቀርን ከልባቸው ተግባራዊ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ስለዚህም ነው ትዳር ቁልፉ በሁለቱ ተጋቢ ሰዎች እጅ እንጂ በሌላ ሰው እጅ አይደለም የሚባለው፡፡ ይህንን የተረዱ ባልና ሚስት የግል ፍላጎትን ብቻ ከማንጸባረቅ ተቆጥበው የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን በማሻሻል አንዳቸው በአን ዳቸው ላይ የሚኖራቸውን ብስጭትና ቁጣ በመተው አብረው ጥሩ ጊዜን በማሳለፍ ትዳራቸውን በሰመረ መልክ ለመምራት ይችላሉ፡፡ በእርግጥ የተበላሸን ነገር ለማስተካከል በአንድ ምሽት የሚ ሰራ ነገር የለም፡፡ ትዳር የባልና ሚስቱ ብቻ ሳይሆን በጋራ የሚያፈሩዋቸው ልጆች፤ በዙሪያው ያሉ ቤተሰቦች፤ የሚያፈሩት ሀብት እና መሰል ጉዳዮችን አብሮ የያዘ እንደመሆኑ ለማስተካከል ጊዜ መፈ ለጉ አይቀርም፡፡
ትዳር እንዲሰምር ሁለቱ ተጋቢዎች ማለትም ባልና ሚስቱ ተከታዮቹን የምሁራን ምክሮች ልብ ሊሉአቸው ይገባል፡፡
እምነትና ፍቅር የተሞላው ጉዋደኝነት፤
ይህ በተቀዳሚነት ልብ ልንለው የሚገባን ነገር ነው። ምክንያቱ ደግሞ ለማንኛውም ግንኙነት መሰረት ስለሆነ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ የሚያልፉ ጉዋደኛሞች መቀራረባቸው ይጨምራል፤ አንዳቸው አንዳ ቸውን ቀኑን እንዴት እንዳሳለፉ…ምን እንዳጋጠማቸው ይጠያየቃሉ። ጉዋደኛ ሞቹ አንዳቸው ለሌላው ደግነት በተሞላው መንገድ በግልጽ እና ክብር በመስጠት ሊቀራረቡና አንዳቸው ከሌላው የሚጠብቁትን ዝቅ አድርገው እራሳቸው ለሌላው የትዳር ጉዋደኛ ማድረግ የሚገባቸውን ግን ከፍ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡  
እኩልነት፤
ምንም እንኩዋን ባልና ሚስት ለግንኙነታቸው ምክንያት የሚሆኑ የተለያዩ ጥንካሬዎችን፤ ዋጋዎች፤ አስተያየቶችን፤ አስተዋጽኦዎችን ቢያደርጉም የዚህ ሁሉ ውጤት በሁለቱም ላይ እኩል መሆኑን መቀበል ግድ ነው፡፡
ድጋፍ ማድረግና ማበረታታት፤
ሴትም ትሁን ወንድ የትዳር ጉዋደኛ ሲመርጡ የህይወትን መንገድ አብሮ ለመጉዋዝ ቃል መግ ባት አብሮ መኖሩን መርሳት አይገባም፡፡ በዚህ ኃላፊነት ውስጥ ሁለቱም አንዳቸው ለሌላኛው ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። አንዳቸው አንዳቸውን በማበረታት ረገድም አንዳ ቸው ለሌላኛው ተቃራኒ በመሆን ሳይሆን በመግባባት፤ በማበረታ ታት ላይ የተመሰረተ ድርጊት እንዲፈጽሙ ይጠበቃል፡፡
ማነጻጸር፤
የትዳር ጉዋደኛሞች አንዱ የሚያነሳውን ሀሳብ ሌላኛው ለመቀበል ዝግጁ መሆን ይጠበቅባ ቸዋል፡፡ ለሚነሳው ሀሳብ ጥሩ ግምት እና ዋጋ መስጠት እና የእራስንም ሀሳብ በትህትና ያለ ተቃርኖ ስሜት መግለጽ ትክክል ነው፡፡ በዚህ መሀልም ከሁለቱም ወገን የቀረበውን ሀሳብ አይተው ወደሚያስታርቃቸው መንገድ መዝለቅ የሁለቱ ተጋቢዎች ግዴታና ኃላፊነት ነው፡፡
የስነልቡና አማካሪዎች እንደሚሉትም ትዳርን ስኬታማ እንዲሆን ቁልፉን በእጃቸው የያዙ ሁለቱ ተጋቢዎች ሊፈጽሙት ከሚገባቸው ተጨማሪ ነጥቦች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
ትዳርን በአንድ ጥግ ወይንም ቦታ እንደሚቀመጥ የተተወ እቃ አድርጎ ማሰብ አይገ ባም፡፡ ምንጊዜም ሊስተካከል የሚችልበትን መንገድ ሁለቱም ተጋቢዎች ሳያሰልሱ ሊያስቡበት እና በመግባባት ሊፈጽሙት ይገባቸዋል፡፡
በትዳር ጉዋደኛ ለአንተ ወይንም ለአንቺ ሊደረግልሽ ወይንም ሊደረግልህ የሚገባውን ነገር ለትዳር ጉዋደኛህ ወይንም ጉዋደኛሽ አድርጊ ወይንም አድርግ። እንዴት ማናገር ወይንም እርዳታ ማድረግ እንደሚገባ ሁልጊዜም እራስን መጠየቅ ይገባል፡፡  
በመካከል ያለውን ልዩነት መቀበል እና የትዳር ጉዋደኛ ማለት በትክክል የእራስ ቅጂ ሊሆን እንደማይገባው በማመንም አክብሮ ኑሮን በጣመ መንገድ መቀጠል ይገባል፡፡ ልዩነትን ከማጉላት ወይንም ከማሰብ ይልቅ ተመሳሳይ የሆኑ ነገሮችን በማሰብ ማድነቅ ይጠቅማል።
ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ወይንም ጉዋደኝነት ለትዳር ይጠቅማል፡፡ እንደጉዋደኛ ቅርርብ መፍጠር አብሮ መሆንን መዝናናትን አንዱ ለአንዱ እንዲያስብ ማድረግን ሊያመጣ ይችላል፡፡
የትዳር ጉዋደኛን ለመውደድ ገደብ ሊኖረው ወይንም ከዚህ በመለስ ማለት አይጠበቅም፡፡
አንዱ ከሌላው ይህንን እፈልጋለሁ የሚል ነገር ሳይኖር መዋደድ ለተጋ ቢዎች ያስፈልጋል፡፡ በኑሮአቸው ዘመን አንዳቸው አንዳቸው ላይ ግዴታ መጣል ወይንም ይህ ያንተ/ያንቺ ድርሻ እንጂ የእኔ አይደለም በሚል ስሜት ሊነጋገሩ አይገባም፡፡
እውነተኛ ፍቅር መጠኑ ይህን ያህል ተብሎ ባልየው ይህን ያህል ወደደ ወይንም ሚስትየው የወደደችው በዚህን ያህል ነው ተብሎ ቀመር የሚወጣለት አይደለም፡፡ በባልና ሚስት መካከል መደረግ የሚገባው ነገር ስለሆነ ፍቅር አንዳቸው ለሌላቸው ይተረጎማል፤በስራ ላይ ይውላል፡፡
እውነተኛ ፍቅር ወደው እንጂ ተገድደው የሚፈጽሙት አይደለም፡፡ ስለዚህ ተጋቢዎች ትዳር ከመመስረታቸው በፊት ማሰብ ይጠቅማቸዋል፡፡

Saturday, 08 September 2018 11:56

መልካም አዲስ ዓመት

   መልካም አዲስ ዓመት! 2011 - የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅርና የብልጽግና ይሁንላችሁ!!

ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ለማፈንና ተቃውሞን ለመግታት በማሰብ የኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነትን የሚገቱ ወይም ጭራሽ የሚያቋርጡ የአለማችን አገራት መንግስታት ቁጥር እያደገ መምጣቱን የዘገበው ፎርብስ፣  በተደጋጋሚ ኢንተርኔት በመዝጋት ህንድ ከአለማችን አገራት ቀዳሚነቱን መያዟን አመልክቷል፡፡
አክሰስ ናው የተባለው አለማቀፍ ተቋም ያወጣውን ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው አንዳለው፣ የህንድ መንግስት ባለፉት ከጥር ወር 2016 እስከ ግንቦት ወር 2018 በነበረው ጊዜ ውስጥ ለ154 ጊዜያት ያህል የኢንተርኔት አገልግሎቱን ዘግቷል ወይም ፍጥነቱን ገትቷል፡፡
በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ለ19 ጊዜያት ያህል ኢንተርኔት የዘጋቺው ፓኪስታን፤ አዘውትሮ ኢንተርኔት በመዝጋት ከአለማችን አገራት ሁለተኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ኢራቅ እና ሶርያ ለተመሳሳይ 8 ጊዜያት ያህል ኢንተርኔት በመዝጋት ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጣቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
ቱርክ ለ7፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ኢትዮጵያ ለ5፣ ኢራን ለ4 እንዲሁም ቻድና ግብጽ ለ3 ጊዜያት ያህል ኢንተርኔትን በመዝጋት ተከታዮቹስ ስፍራ እንደያዙ ሪፖርቱ መግለጹንም ዘገባው ጠቁሟል።
መንግስታት የፖለቲካ ቀውስ ሲያሰጋቸው፣ ተቃውሞ ሲበዛባቸውና ወታደራዊ ጥቃት በሚፈጽሙበት ወቅት የመረጃ ፍሰትን ለመግታት ኢንተርኔት እንደሚዘጉ የጠቆመው ዘገባው፣ በተለያዩ የአፍሪካና የእስያ አገራት ደግሞ ፈተናዎች እንዳይጭበረበሩ ለማድረግ ኢንተርኔት እንደሚዘጋ አመልክቷል፡፡
አገራት ኢንተርኔትን በመዝጋት ሊከሰቱ የሚችሉ ጥፋቶችን ለመቀነስና አደጋዎችን ለማስቀረት እንደቻሉ ቢናገሩም፣ በሌላ በኩል ደግሞ ኢንተርኔት በመዝጋታቸው ሳቢያ ኢኮኖሚያቸው በከፍተኛ ሁኔታ ሲጎዳ ታይቷል ያለው ዘገባው፣ እኤ.አ ከ2012 እስከ 2017 በነበሩት ጊዚያት በድምሩ ለ16 ሺህ 315 ሰዓታት ኢንተርኔትን በመዝጋቷ ሳቢያ በኢኮኖሚዋ ላይ የ3.04 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ እንዳጋጠማት በአብነት አስታውሷል፡፡


ግብጽ በአፍሪካ በቁመቱ ቀዳሚ እንደሚሆን የተነገረለትንና የናይል ማማ የሚል ስያሜ የሰጠቺውን ሰማይ ጠቀስ ህንጻ በመዲናዋ ካይሮ፣ ከአባይ ወንዝ ዳርቻ ላይ በ600 ሚሊዮን ዶላር ልትገነባ መሆኑን ፎርብስ ዘግቧል፡፡
የዚህ ሰማይ ጠቀስ ህንጻ ፕሮጀክት የተወጠነው ከአስር አመታት በፊት በቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ የስልጣን ዘመን እንደነበረ ያስታወሰው ዘገባው፣ በ2011 በተቀሰቀሰው አብዮት ሳቢያ ፕሮጀክቱ ተቋርጦ መቆየቱንና በወቅቱ መሪ አብዱልፈታህ አልሲሲ ፈቃድ እንዲቀጥል መደረጉንም አመልክቷል፡፡
ዛሃ ሃዲድ በተባሉት ታዋቂ የአገሪቱ አርክቴክት ከ11 አመታት በፊት ንድፉ ተሰርቶ የተጠናቀቀው ህንጻው፣ 70 ወለሎች እንደሚኖሩት የጠቆመው ዘገባው፣ 36 ወለሎች ለአፓርትመንት፣ 18 ወለሎች ለሆቴል አገልግሎት የሚውሉ ሲሆን፣  የተቀሩት ወለሎች ደግሞ የገበያ ማዕከል፣ የመዝናኛ ስፍራ፣ የምሽት ክለብና ለሌሎች በርካታ ጥቅሞች እንደሚውሉ አስረድቷል፡፡

በአለማችን በየአመቱ ሩብ ሚሊዮን ያህል የተለያዩ አገራት ዜጎች በጦር መሳሪያ አማካይነት ለሚከሰት ሞት እንደሚዳረጉ አንድ አለማቀፍ ሪፖርት ማስታወቁን ደች ዌሌ ዘግቧል፡፡
የአሜሪካ ሚዲካል አሶሴሽን በ195 የአለማችን አገራት ላይ የሰራውን ጥናት መሰረት በማድረግ ያወጣውን አለማቀፍ ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ በአለማችን በየአመቱ ከ250 ሺህ በላይ ሰዎች በጦር መሳሪያዎች አማካይነት ለሞት የሚዳረጉ ሲሆን፣ 70 በመቶ ያህሉም በሌሎች ሰዎች በሚደርስባቸው ጥቃት የሚገደሉ፣ 27 በመቶው ራሳቸውን የሚያጠፉ፣ 9 በመቶው በአደጋ ለሞት የሚዳረጉ ናቸው፡፡
ተቋሙ በአገራቱ እ.ኤ.አ ከ1990 እስከ 2016 በነበሩት አመታት በጦር መሳሪያዎች አማካይነት ለሞት የተዳረጉ ሰዎችን በተመለከተ በሰራው በዚህ ጥናት፤ የሟቾች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉንና በ2016 የፈረንጆች አመት ብቻ በአለማችን 251 ሺህ ሰዎች በጦር መሳሪያዎች ለሞት መዳረጋቸውን ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡
ኤልሳልቫዶር ከአጠቃላይ የህዝብ ብዛቷ አንጻር ብዙ ሰዎች በጦር መሳሪያዎች አማካይነት ለሞት የሚዳረጉባት ቀዳሚዋ የአለማችን አገር ናት ያለው ሪፖርቱ፣ በአለማችን በጦር መሳሪያ ለሞት ከሚዳረጉት ሰዎች መካከል ግማሽ ያህሉ የብራዚል፣ ኮሎምቢያ፣ ጓቲማላ፣ ሜክሲኮ፣ ቬንዙዌላ እና የአሜሪካ ዜጎች እንደሆኑም አክሎ ገልጧል፡፡

  (ሁለተኛ ክፍል)
አርክቴክት ሚካኤል ሽፈራው “የማስጠንቀቂያ ደወል” በሚል ርዕስ ያሳተመውን መጽሐፍ፤ “የዶ/ር ዐቢይ አህመድን ህዝባዊ መሠረት የካደው መጽሐፍ” በሚል ባለፈው ሳምንት የመጀመርያውን ክፍል ሂሳዊ ጽሁፍ አቅርቤ ነበር፡፡ ሁለተኛውን ክፍል እነሆ፡
አቶ ሚካኤል ይግባቸው አይግባቸውም የኢሕዴን የቀድሞ መዝረክረክ ምንጩ፣በፓርቲው ውስጥ ያሉት ሰዎች የተወከሉበትን ብሔር ሕይወት ለመለወጥ ያልተዘጋጁና ፓርቲውም በአክሲዮን የተያዘ እንጂ ነፃ ያለመሆኑ ነው፡፡ ከጅምሩ ኢትዮጵያዊ ሆኖ መታገሉን ያልወደዱት የሕወሓት አመራሮች የበታተኑትም ለራሳቸው ጥቅምና አጀንዳ፣በስሙ የሚነግዱበት የብሔር ቡድን ለመፍጠር ተመኝተው መሆኑን የቀድሞው የኢሕዴን መሥራችና አመራር አቶ ያሬድ ጥበቡ፤ “ወጥቼ አልወጣሁም” በሚለው አዲስ መጽሐፋቸው ላይ ይገልጻሉ፡፡
ኢሕአዴጋዊ ፍቅር የተጠናወተው፣ ይልቁንም ሕወሐታዊ አድናቆት የያዘው የሚካኤል መጽሐፍ እንደሚለው፤ ብሔር-ተኮር ስራ ይሰራ ዘንድ እንዳይችል ያደረገው ጨቋኝ ለተባለው አማራ መጨቆኛ ይሆናሉ ያላቸውን የራሱን ሰዎች መሰግሰጉ እንደሆነ ማንም አያጣውም፡፡ ሌላው ቀርቶ በየትኛውም ክልል ባልታየ ሁኔታ የክልሉ ቢሮ ኃላፊዎች ሳይቀር ከዕድለኛው ቡድን መጥተው ሲሾሙበት ለምን ነፃ አይሆንም? ብሎ የጠየቀ የለም፡፡ ለመሆኑ ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት የነበረው የአማራ ፓርቲ ሰዎች፣ ምን ያህሎቹ የክልሉ ተወላጆች ነበሩ?
ምንም እንኳ የብሔር ፖለቲካ መዘዙ ሺህ ቢሆንም በዚሁ ቅኝት በተቃኘ አስተዳደር ውስጥ ሆኖ በማይመለከተው ሰው መተዳደር የሚያመጣውን ጣጣ አይተናል፡፡ ወጣቱ በስራ አጥነት መንገላታቱ ሳያንስ በእስራት ሲሰቃይና በጥይት ሲደበደብ፤እወክለዋለሁ የሚለው ድርጅት ጥይት አቀባይ እንዲሆን ያደረገው፣ ህዝቡን ልክ ለማስገባት የተመደበው ፓርቲ ነው፡፡
የአቶ ሚካኤል መጽሐፍ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮችን ቢያነሳም በጣም ጥቂት በሆኑ ገፆች ሊነካ የፈለገው አዲሱን የለውጥ መንገድ ነው፡፡ ይህ የለውጥ መንገድ ብዙዎቻችን ከአሰቃቂ ግፍ፣ አድልዎ ከበዛበት አስተዳደር፣ ዐይን ካወጣ ዘረፋ፣ ከእስራትና ከግድያ የታደገን ቢሆንም ደራሲው ሚካኤል የታየው ግን ስጋቱና አደጋው ነው፡፡ ወደ ሚካኤል ጎርባቾቭ የወሰደውም ያ ነው፡፡  
“የማስጠንቀቂያ ደወል” በሚለው መጽሐፉ፤ሚካኤል ጎርባቾቭ ሶቪየት ህብረትን እንደበታተኑ ዶክተር ዐቢይም አገራቸውን ሊበታትኑ ይችላሉ የሚል ስጋቱን አጋርቶናል፡፡ ለመሆኑ ዶክተር ዐቢይ ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት ከተሰሩት በደልና ግፎች የባሰ ምን ሰርቶ ነው አደጋ ያመጣብን? ይልቅስ ሰው በየአደባባዩ ሲታረድ፣ በእስር ቤት ሲታጎርና ጥፍሩ ሲነቀል፣ ሲኮላሽ-- ያልተፈጠረው ስጋት አሁን እንዴት ሊመጣ ቻለ? ..መንግሥት እንደ ተራ ወንበዴ ሕዝብን ከሕዝብ፣ ብሔርን ከብሔር ለማጋጨት ሀውልት ሲሰራ፣ ሸንጎ እየጠራ ፀብ ሲቀሰቅስ---ያልነበረው ስጋት፣ ዶክተር ዐቢይ መጥቶ “እንታረቅ፣ ይቅር እንባባል፣ እንደመር” ሲል እንዴት ሊፈጠር ቻለ?
ዶክተር ዐቢይ ባይመጣስ በሀገሪቱ ይፈጠር የነበረው ሁኔታ የዛሬውን ዐይነት ህዝብን የሚያረጋጋና ደስ የሚያሰኝ ይሆን ነበር? ቀጣዩን ሁኔታ የሁላችንም ልብ ያውቀዋል፡፡ ምናልባትም ቢበዛ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሀገሪቱ መያዣ መጨበጫ ወደሌለው ችግር ውስጥ ትገባ ነበር፡፡
ይህ ማለት ግን “የኛ ጥቅም ከሚነካ አገሪቱ ትበታተን!” የሚሉ ወገኖች የሉም ማለት አይደለም። የኔ ሙግት ሚካኤልን የሚያህል ትልቅ ሰው፣ ብዙ የሚያውቅና የጥበብ ልብ ያለው ሰው፣ ለምን ያንን የደምና የእንባ ዘመን ከስጋት ሳይቆጥር ቀረ? የሚል ነው፡፡
ሚካኤል በክልል ከተሞች በተለይም የአማራውንና አማርኛ ተናጋሪውን ባይተዋርነት በሚመለከት በስፋት ጽፏል፡፡ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ዕድል የሚለውን የኢሕአዴግ ሀሳብ ይዞ በ1999 ዓ.ም ከተደረገው የህዝብ ቆጠራ ስታቲስቲክስ በመነሳት፣ የተሻለ መንገድ ያሳየበት ነው ማለት ይቻላል፡፡ ለመነሻ የሀገራችን ከተሞች አመሰራረትን በሚመለከት ሚካኤል እንዲህ ይለናል፡-
“የአገራችን ከተሞች አንዳንዶቹ ቀደም ሲል የገበያ ስፍራዎችና የነባሮቹ ገዢዎችና የጎሳ መሪዎች መቀመጫዎች የነበሩ ቢሆንም ባመዛኙ ግን ኢትዮጵያን አንድ አድርገው ለመግዛት በተነሱት አጼ ምኒልክ አዳዲስ የተካተቱ ግዛቶችን በአንድነቱ ውስጥ አዲስ በተካተተው ህዝብ መካከል ሆነው ግዛት እንዲያስጠብቁ በተላኩ የገዢው መደብ የጦር መሪዎች፣ በአሽከሮቻቸውና በወታደሮቻቸው የተመሰረቱ የጦር ሰፈሮች ነበሩ፡፡ በመጪዎቹ ዘመናት ደግሞ ከጦር ሰፈርነታቸው ከፍ ብለው በተጨማሪ ያስተዳደርና የገበያ ማዕከሎች ሆኑ፡፡”
ጸሐፊው ስለ ሀገራችን ከተሞች የሕዝብ ስብጥርና ምስረታ ያነሳው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ይልቅስ በአንዳንድ የክልል ከተሞች የሚኖሩና የክልሉን “ለባለ ክልሉ” በሚል ብሔርተኛ የፖለቲካ ቅኝት መጤዎቹን ያገለለ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ስልጣን በመንሰራፋቱ ላይ የራሱን ሀሳብ ለመስጠት ነው፡፡
በቅኝቱ የሐረሪን፣ የኦሮሚያን፣ የቤኒሻንጉልን፣ የአፋርን ክልሎች ማሳያ በማድረግ በከተሞች ውስጥ የሚኖሩት አማርኛ ተናጋሪዎች በቁጥር የበዙ ሆነው ሳለ፣ በአስተዳደር ውስጥ ድምፃቸውን የሚያሰሙላቸው ወኪሎች የሏቸውም፡፡ በዚህም ምክንያት እነዚህ ከክልላቸው ውጭ የሚኖሩ፣ ኢትዮጵያውያንን በስልጣን ላይ ባሉ የክልሉ ተወላጆች የሚደርስባቸውን አስተዳደራዊ በደልና ጫና እንዳይኖር እነርሱን ወክሎ፣ መፍትሄ ለማስገኘት ዕድሉ ስለማይኖረው ውሎ አድሮ በፌደራላዊው መንግስት ላይ የሚኖረው እምነትና አመላካከት የተበላሸ ይሆናል ይለናል” መጽሐፉ፡፡
ለዚህም እንደ ማስረጃ ያቀረበው የ1999 ዓ.ም የህዝብ ቆጠራ መሰረት በማድረግ፣ ከ3.4 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ከክልላቸው ውጭ መሆኑን ያሳያል-ሚካኤል፡፡ በዚህ ርዕስ ሥር ባስቀመጠው አጠቃላይ ድምዳሜ፤ ኢሕአዴግን፣ ይልቁንም ብአዴንን ይወቅሳል፡፡ በሌላ በኩል በ1997 ዓ.ም ፓርቲው በከተሞች የመሸነፉ ምክንያት የነዚህ በሚሊየን የሚቆጠሩ ህዝቦች ከስርአቱ መንሸራተትና ማኩረፍ ነው ብሎ ያምናል፡፡ በዚያም አለ በዚህ፣ በከተሞ አካባቢ ተወላጅ ያልሆኑ ነዋሪዎችን ችግር መዝኖ መፍትሄ ይሰጣቸው ዘንድ መጠየቁን በበጎነት አሰምርበታለሁ፡፡
ለችግሩ እንደ መፍትሄ ያስቀመጣቸው ነገሮችም በጎ ናቸው፡፡
1ኛ. ዛሬ ያለበት ምዕራፍ ያለፉትን ዘመናት ጉዞዎች በአዲስ የእይታ መነጽር መርምሮ፣ የሚመራውን የአማራ ህዝብ፣ በተለይም ከክልሉ ውጭ ባሉ ከተሞች ተሰራጭቶ የሚኖረውን የአማራ ህዝብ ፖለቲካዊ መብቶች አስከብሮ ከሌሎች ህዝቦች ጋር ያለውን መልካምና ዴሞክራሲያዊ ግንኙነት ባስተማማኝ መሰረት ላይ የሚያቆምበት፤
ሁለተኛውና ሶስተኛው ነጥብም ከክልል ውጭ የሚኖረው ህዝብ ዋስትና የሚሰጥ የህግ ማዕቀፍ እንዲኖረው፣ በሚኖርበት ቦታ ላፈራውና ለሚያፈራው ሀብትና ንብረት ዋስትና እንደሚያገኝ፤ በሌላም በኩል ታሪካዊ፣ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ማንነቱን አውቆ፣ የሚኖረውን የአማራ ህዝብ ፖለቲካዊ መብቶች አስከብሮ ከሌሎች ህዝቦች ጋር ያለውን መልካምና ዴሞክራሲያዊ ግንኙነት ባስተማማኝ መሰረት ላይ የሚያቆምበት፣
ሁለተኛውና ሦስተኛው ነጥብም ከክልሉ ውጭ የሚኖረው ህዝብ ዋስትና የሚሰጥ የህግ ማዕቀፍ እንዲኖረውና፣ በሚኖርበት ቦታ ላፈራውና ለሚያፈራው ሀብትና ንብረት ዋስትና እንዲያገኝ፤ በሌላም በኩል ታሪካዊ፣ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ማንነቱን አውቆ፣ በጥንታዊና ነባሩ ማንነት ላይ ዲሞክራሲያዊና ብሔራዊ ማንነቱን ሳያምታታ፣ ድርጅቱን “የራሴ ነው” በሚል ተቀብሎ፣ ድርጅቱን እንደተጠሪው የሚቆጥር ሕዝብ መፍጠር አለበት ብሎ ያምናል፡፡ ይህ የሚካኤል ጥሩ አካሄድና ለወገን ተቆርቋሪነት ነው፡፡
ይሁንና ብዙ ነገሮቹን ስንመረምር፣ በሦስተኛው ዓለም፣ በተለይ በአፍሪካ መሪዎች አካሄድ ያየው አይመስልም፡፡ በተለይም ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት የተሸረቡትን የፖለቲካ መንግሥታዊ ሴራዎች የሚያውቃቸው አይመስልም፡፡
ለመሆኑ ብአዴን የአማራውን ህዝብ ይወክል ነበር ወይ? ተብሎ ቢጠየቅ “አዎን!” የሚልበት ምልክቶች ይታያሉ፡፡ ምናልባትም ወቀሳው ከዚሁ ባይተዋርነት የመነጨ ነው፡፡ እውነት ለመናገር ያ በእባብ፣ በእንቁራሪትና በጊንጥ ሊመሰል የሚችለው የፖለቲካ ባህር በውስጡ ከጥቂት ዓሳዎች በስተቀር በጨካኞችና በግፈኞች የተሞላ እንደነበር የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ በአንጻራዊነት ሌሎቹ ክልሎች ጥይትና ሳንጃን ሲቀበሉ፣ አብሮ ጥቂት ልማት ይመረቅላቸዋል፡፡ በብአዴን ግዞት ሥር የነበረው ሕዝብ ግን ትምህርት ቤት እንኳ የሚሰራለት አጥቶ ቁልቁል ወደ ኋላ በመሄድ በየዛፉ ስር ፊደል ሲቆጥር መኖሩን ብዙዎቻችን እናውቃለን፡፡
የአቶ ሚካኤል መጽሐፍ ትኩረትና ማስጠንቀቂያ፤ በብአዴን እጅ ለወደቀው ምስኪን የአማራ ህዝብ ሳይሆን፣ የኢህአዴግን የምር ቀውስ ወደ ፈጣሪው በየክልሉ ላለውና በራሱ ሰዎች ባለመወከሉ ቁጣ ጦስ ነገሮች አስጊ እየሆኑ መምጣታቸውም ይመስላል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የዋለልኝን የብሔር ጥያቄ አስቀምጦ፣ ኢህአዴግ መሬት ላይ ያወረደበትን መንገድ ማሳየቱ፣ እግረመንገዱን በስስ ልምጭ መንካቱ ጥሩ ነው፡፡  
ቢሆንም ክፋት የለውም … ይሁንና ሌላው ያልተመቸንና መዝጊያው ላይ የተነገረን ማስጠንቀቂያ ነው፡፡ ማስጠንቀቂያው በማህበራዊ ሚዲያ እስኪታክተን ያነበብነው ነው፡፡ “ትግራይ ልትገነጠል ትችላለች!” የሚል፡፡
ይህ ቋንቋ በእጅጉ ይዘገንነኛል፡፡ ለመሆኑ ትግራይን የፈጠራት ማነው? … የተፈጠረችውስ መቼ ነው? … ለምንስ የትናንቱ ወያኔ ጠፍጥፎ እንደሰራት ትቆጠራለች? እውነት ለመናገር የትግራይ አባቶች ኢትዮጵያን ከፈጠሯት ሰዎች ተርታ ያሉ አይደሉም እንዴ? .. ለነፃነት በፈሰሰው፣ ለብሔራዊ አንድነት በተከፈለው ዋጋ ቁንጮ ላይ ያሉ ሰዎች ምድር ታሪክ በሚያዛቡ ሰዎች ትነጠላለች ያለውስ ማነው?
እንደኔ ከዚህ ለዘብ ያለ አስተያየትና ቅሬታ ቢነሳ ቅር አይለኝም፡፡ ከዚያ ውጭ ግን መገንጠል ያቃዠውና ከትግራይ ህዝብ ልብ ያልወጣ ጩኸት ሰሚ የለውም። ዮሐንስ የሞተው ሀገር ለመገንጠል አይደለም፣ አሉላ በየጦር ግንባሩ በእሳት የተበላው፣ የጥይት ባሩድ ሲያሸት የመኖሩ ትሩፋት ሕዝብን ለመለየት አይደለም። አንዲት ጠንካራ ሀገር ለመፍጠር ነው፡፡ እንደዛሬዎቹ ሀገር ለመበተን፣ ህዝብ ለመለያየት አይደለም፡፡
ከሚካኤል ሀሳቦች የምጋራው የጋራ ጉዳይ አለኝ። ያም የትግራይ ክልል ተወላጆች የጥቃት ስጋት አለባቸው የሚለነው ነው፡፡ ይህንን በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ በሌሎች መገናኛ ብዙኃንም ሽንጤን ገትሬ ተሟግቻለሁ፡፡ አሁንም በእጅጉ እታገለዋለሁ፤ እቃወመዋለሁ፡፡ የትግራይ ህዝብ ስጋችን፣ አካላችን ነው፡፡ የአክስት ባል፣ የአጎት ልጅ ወዘተ ሆነናል፡፡ ይህንን ዝምድና ያላገናዘበ ዘረኝነትና ጥላቻ ተቀባይነት የለውም፡፡
ሚካኤል ሺፈራው (ገፅ 269 ላይ)ባሰፈረው ሃሳብ ግን አሁንም ትክክለኛ ያልሆነ ሃሳብ ነው፡፡ እዚህ ላይ አንድን የረጂም ታሪክ ባለቤት የሆነን ህዝብ ትናንት የተፈጠረ ፓርቲ ብቻውን ሊነዳው አይችልም፡፡
አገሪቱን በመምራት ላይ ያለው ኃይል የመገንጠል አማራጭ ሊወስድ የሚችል መሆኑን ሳይረፍድ መረዳት የሚገባ ይመስለኛል” ይላል ሚካኤል፡፡ እኔ ደግሞ ትግራይን ኢትዮጵያዊ አድርጎ የፈጠራት ሕወሓት ስላይደለ የመገንጠል ሀሳቡም ሆነ ስልጣኑ የለውም ባይ ነኝ፡፡ የትግራይ ህዝብ ሀገሩ ትግራይ ብቻ አይደለም፡፡ ሀገራችን የምንለው ሁሉ ሀገሩ ነው። ህዝቡ ለኦጋዴን ሞቷል፣ ለሞያሌ ነፍሱን ሰጥቷል፡፡ በሌሎች ግንባሮችም ዋጋ ከፍሏል፡፡ አሁን ደግሜ ማንሳት ባያስፈልገኝም እንደዛሬ ወያኔ በጎጥ ሳይለየን በፊት ለዚህች ሀገር ዋጋ የከፈሉ የቅርብ ሰዎቼን የአብሮ አደጎቼን ወላጆች ማስታወስ እችላለሁ፡፡
ሳጠቃልል፤ አቶ ሚካኤል የጻፉት መጽሐፍ በተለይ መግቢያና መውጫው ላይ ችኮላ ስለነበረበት፣ የአረፍተ ነገር አጠቃቀም፣ የአንቀፅ አደረጃጀት፣ የቃላት ግድፈት ጎልቶ ይታይበታል፡፡ ሌላው ቀርቶ ገፅ 217 እና 218 ላይ ተመሳሳይ ሀሳብ ማስፈሩን፣ በምስጋናው ገፅ እንኳ ከአምስት በላይ ግድፈቶች መኖሩ፣ ገፅ 192 እና 193 የሚታየው፣ “አይቻለሁ፣ አስተውያለሁ” የሚል የሪፖርት ቋንቋ ያለ ቅጥ መበዛት፣ ጉዳዩን የእነ ቶሎ ቶሎ ቤት አስመስሎታል፡፡
በመጨረሻም ለዶክተር ዐቢይ ብሎ የጻፈውንና ያሰፈረውን ሃሳብ እጋራለሁ! አሁንም ቅር የሚለኝ ግን ያ ሁሉ ግፍ ከሀገሪቱ ሰማይ ስር ሲፈፀም ጥሩ እንቅልፍ አግኝቶ፣ አሁን በለውጡ ጅማሬ “ለማስጠንቀቂያ” መባዘኑ ነው፡፡

የደቡብ ኮርያ መንግስት ተማሪዎችንና መምህራንን ቡና አብዝቶ ከመጠቀም ጋር ተያይዘው ከሚከሰቱ ችግሮች ለመጠበቅ በሚል በትምህርት ቤቶች ቅጽር ግቢ ውስጥ ቡና እንዳይሸጥ የሚከለክል ህግ ሊያወጣ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
የአገሪቱን የምግብና የመድሃኒት ደህንነት ሚኒስትር መግለጫን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ በሁሉም የአገሪቱ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከመጪው መስከረም ወር ጀምሮ ቡና ሲሸጥም ሆነ ሲገዛ የተገኘ ከፍተኛ ቅጣት ይጣልበታል፡፡
መንፈሳቸውንና ዘና ለማድረግና ለመነቃቃት በማሰብ በርካታ ተማሪዎችና መምህራን በትምህርት ቤቶች ውስጥ ቡና በብዛት እየተጠቀሙ የልብ ምት መጨመርና የእንቅልፍ ማጣትን ጨምሮ ለተለያዩ የጤና እና የስነልቦና ችግሮች እየተጋለጡ መሆናቸው አሳስቦኛል ያለው ሚኒስቴሩ፣ ይህን ችግር ለመቅረፍ በቡና ሽያጭ ላይ ክልከላ ለማድረግ መወሰኑን አስታውቋል፡፡
በመዲናዋ ሴኡል ከ18 ሺህ በላይ የቡና መሸጫዎች እንዳሉና አንድ ደቡብ ኮርያዊ በአመት በአማካይ 181 ሲኒ ቡና ይጠጣል ተብሎ እንደሚገመት የጠቆመው ዘገባው፣ ይህም አገሪቱን ከእስያ ከፍተኛው የቡና ተጠቃሚነት ያለባት አገር ያደርጋታል ብሏል፡፡

 ገዢው ፓርቲ ያልበሰሉ ፖለቲከኞች አገር እንዳያጠፉ ያሰጋል ብሏል

    በአወዛጋቢ ምርጫ ስልጣኑን ያስጠበቀው የዚምባቡዌ ገዢ ፓርቲ ዛኑ ፒኤፍ፣ ምራቃቸውን ዋጥ ያላደረጉና በወጉ ያልበሰሉ ግለሰቦች ለፕሬዚዳንትነት እየተወዳደሩ አገሪቱን ለቀውስ እየዳረጓት በመሆኑ፣ ዜጎች ለፕሬዚዳንትነት መወዳደር የሚችሉበትን የዕድሜ ገደብ ከ40 አመት ወደ 60 አመት ከፍ ለማድረግ እንደሚሰራ መግለጹን አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
በቅርቡ በተካሄደው የዚምባቡዌ አገራዊ ምርጫ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋዋ በአብላጫ ድምጽ ቢያሸንፉም፣ ዋነኛ ተቀናቃኛቸው የነበሩት ሙቭመንት ፎር ዲሞክራቲክ ቼንጅ የተባለው የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ኔልሰን ቻሜሳ፤ ምርጫው በመጭበርበሩ ውጤቱ ይሰረዝልን በሚል ለፍርድ ቤት ቢከስሱም በለስ እንዳልቀናቸው ያስታወሰው ዘገባው፣ የ40 አመት ዕድሜ ያላቸው ኔልሰን ቻሜሳ ምርጫውን የልጅ ጨዋታ አድርገውታልና ከአሁን በኋላ ለፕሬዚዳንትነት የሚወዳደሩት ቢያንስ 60 አመት የሞላቸው ዜጎች ሊሆኑ ይገባል ሲል ዛኑ ፒኤፍ ማስታወቁን አመልክቷል፡፡
የተቃዋሚው ፓርቲ መሪ ቻሜሳ በምርጫው ሲሸነፉ እንደበሳል ፖለቲከኛ ሳይሆን እንደህጻን ልጅ በማኩረፍና የማይገባ ድርጊት በመፈጸም ጉዳዩን የልጅ ዕቃ ዕቃ ጨዋታ አድርገውታል፤ ከአሁን በኋላ እንደ እሳቸው ያለ ያልበሰለ ሰው ዘልሎ ለፕሬዚዳንትነት መወዳደር የለበትም ብለዋል፤ የገዢው ፓርቲ የዛኑ ፒኤፍ የብሄራዊ ደህንነት ጸሃፊ ላሞር ማቱኬ፡፡
በአገሪቱ ክምር ቤት አብላጫ ወንበር የያዘው ፓርቲያቸው፤ ዜጎች ለፕሬዚዳንትነት መወዳደር የሚችሉበትን የዕድሜ ገደብ ከ40 አመት ወደ 60 አመት ለማድረግ በህገ መንግስቱ ላይ ማሻሻያ መደረግ የሚችልበትን ዕድል ለመፍጠር ጠንክሮ እንደሚሰራም አስታውቀዋል፡፡