Administrator

Administrator

  እስካሁን ለምን ዝም እንዳልኩኝ የምትረዱ ይመስለኛል፡፡ ድንጋጤና ሐዘን በጣም ጎድተውኛል፤ በትክክል ሁሉ ማሰብ አልቻልኩም ነበር፡፡ አሴ ቢሆን ስንት ፅፎ ነበር፡፡
በመጀመሪያ ለአባቴ የደረሰችለት ዳላስ ቴክሳስ የምትኖረው ወ/ሮ አብነት ከነቤተሰቧ፤ ተመላልሳ በመጠየቅ ከአጠገቡ የተገኘች መልካም ሴት ናት፡፡ መቼም ቢሆን አልረሳሽም፤ እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡ መላው ቤተሰብ እንዲያውቅ አብነትንም ወደ አሴ እንድትሄድ ያደረጉ የአክስታችን የእትዬ ሽታ ልጆች ትዕግስትና ኤልሳ ምክሩ በጣም ኮርቼባችኋለሁ፣ የእትዬ ሽታ ምትክ ናችሁ።
አሴ አገሩ እንዲገባ ትልቁን ሚና የተጫወቱት በዳላስ ቴክሳስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቴ፤ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ገንዘብ አሰባስበው የሚያስፈልገውን ሁሉ በማድረግ፣ ከሆስፒታል ጀምሮ እስከ አሸኛኘቱ ድረስ ለፍተው ብዙ ጥረት በማድረጋቸው እንዲሁም በአሜሪካ በተለያዩ ስቴቶች እንዲሁም በተለያዩ ውጭ አገራት ያላችሁ የአሴ ወዳጆች፣ ጓደኞች ሁሉ ያደረጋችሁትን መረባረብ ታሪክ አይረሳውም፡፡
በዳላስ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል አስተዳዳሪና የቅዱስ ተቋም ዳይሬክተር፣ ቀሲስ አንዱዓለም ዳግማዊ፣ እግዚአብሔር ብድራቱን ይክፈላችሁ እላለሁ፡፡
በድጋሚ በዳላስ ቴክሳስ የኢትዮጵያ ኮሙኒቲና በሌላውም ስቴት ያላችሁ፣ በመላው አለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እሱ እንደወጣ እንዳይቀር ስላደረጋችሁ ደግሜ ደግሜ አመሰግናለሁኝ፡፡
ኢትዮጵያ ሲገባ ደግሞ ከመግባቱ ዜና ጀምሮ እስከ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ድረስ ህዝብ እንዲያውቀው በማድረግ ትልቁን ሚና የተጫወተው ሸገር 102.1 ሬዲዮ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ እኛ ለአንድም ሰው ደውለን አልተናገርንም፤ ሁሉንም ያሰባሰባችሁት እናንተ ናችሁ። አባቴን እንዳከበራችሁት እግዚአብሔር ያክብርልኝ። በተለይ አቶ ደምሰውንና ሌሎችንም የሸገር አዘጋጆች በሙሉ፣ ወ/ሮ መዓዛንም ላመሰግን እወዳለሁ፡፡
ኢትዮጵያ ሲገባ ከቦሌ ጀምሮ አቀባበል በማድረግና በሁለተኛው ቀንም የቀብር ስነ ስርአቱን በደማቅ ሁኔታ ያስከበሩትን የኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡›
በሌላ በኩል በአርባ ምንጭና በጨንቻ የቀብር ሥነ ሥርአቱ ይፈፀማል ብለው በጣም ሰፊ ዝግጅትና ድካም ሲያደርጉ የቆዩትን የአርባ ምንጭ ህዝብና የክልሉን መንግስት ይቅርታ እጠይቃለሁኝ፡፡ ያም ሳያንሳችሁ እዚህ ድረስ በመምጣት የቀብር ሥነ ሥርአቱ በባህሉ መሰረት፣ እዚህ ካለው ህዝብ ጋር በደማቅ ሁኔታ ስለአከበራችሁ አመሰግናለሁ፡፡
ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የምትልኩልን የሐዘን መግለጫ ደርሶናል፡፡ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ ለምሁራን፣ ለባለሥልጣናት፣ ለአምባሳደሮች፣ ለሚኒስትሮች፣ ለውጭም ሆነ ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች፣ ለአሴ የቅርብ ጓደኞችና ወዳጆች ከአጠገባችን ላልተለያችሁን ሁሉ እናመሰግናለን፡፡
የአባቴ የቅርብ ጓደኛና (ወንድም) አቶ ፍቅረ ማርያም ይፍሩ፤ አባቴ አገሩ ሲገባ ከአቀባበል ጀምሮ የህይወት ታሪኩን ባመረ ሁኔታ ፅፎ ያቀረበው የቤተክርስቲያኑ ፕሮግራም እንዲያ እስከ መጨረሻው ድረስ እንደ ሰርግ አምሮ ደምቆ እንዲደረግ የለፋ በመሆኑ እግዚአብሔር እድሜና ጤና ይስጠው እላለሁ፡፡
የአክስቴ ባለቤት አቶ ባልቻ ሙሊሣ፤ የአክስት ባለቤት ሊባል አይቻልም፤ አይገባውም፡፡ ለኛ አባታችን መሰብሰቢያችን ነው፡፡ አሁንም የአሴን ማረፍ ከሰማ ቀን ጀምሮ ቤተሰቡን ከየአለበት እንዲሰባሰብ በማድረግ፣ ደከመኝ ሳይል ያንን ሁሉ ቀን ቤተሰባችንን በመሰብሰብ የቀብሩ ሥነ ስርዓት በጥሩ ሁኔታ ተፈፅሞ፣ እንግዶች በስርአት እንዲሸኙ በማድረግ ትልቅ ነገር ነው ያደረገው፡፡ እግዚአብሔር እድሜና፣ ጤና ይሰጥልን፡፡
ለቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ፣ ለካቴድራሉ ቀሳውስት፣ ካህናት ለአገልጋዮች በአጠቃላይ፣ ለቀሲስ ፀጋዬ በክብር ስለሸኛችሁት በልዑል እግዚያብሄር ስም አመሰግናለሁ፡፡
እንደ ሃሳቡና ፍላጎቱ እንደ ዶርዜ ወንድሞቼ፣ እንደ ጋሞ ዘመዶቹ በዋፈራና በሆታ ሸኙኝ ባለው መሠረት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ በድምቀት ከጥዋት ጀምራችሁ እስከ ቀብር ሥነሥርአቱ ድረስ ላሳመራችሁለት የልቡን ስለፈፀማችሁ፣ ለአቶ ሞላ ዘገየ እንደ ቤተሰብ መሀላችን ገብተህ የኢትዮጵያዊነትህን፣ የወንድምነትህን፣ የጓደኝነትህን ከሌሎች ከውጭም ከአገር ውስጥም ካሉ ጋር በመተባበር እስከመጨረሻው ከአጠገባችን ባለመለየት የሰማነውን የህይወት ታሪክ ባማረ ሁኔታ አሰማሀን፡፡
ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ አዘጋጆች (የአሴ ወዳጆች)፣ ለነብይ መኮንንና ለአለማየሁ አንበሴ እንዲሁም ለሌሎቹ ጋዜጠኞች በሙሉ ከመጀመሪያ ካረፈበት ግዜ አንስታችሁ ሰፊ ሽፋን ነው የሰጣችሁት፤ አስቀድሜ እንዲያውም በጣም ፈርቼ ማዘኔን ነግሬአችሁ ነበር፡፡ ብቻችንን ነን ብዬም ነበር፤ ኋላ ሁሉም ደረሰልን፡፡ አመሰግናለሁ፡፡
ለነባዳን የሚዲያ ማማከር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (ለዳኒና ለነብይ) ለደራሲ እንዳለ ጌታና ለወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን፣ ለዘነበ ወላ … በአሜሪካን አገር ለሚኖሩ አባቴን እንደ አባት የሚጠብቁና የሚቆረቆሩለት ዳንኤል ካሣሁንና ዶክተር ግርማ አውግቸው ደመቀ እንዲሁም ለካሣሁን ሰቦቃ … ምስጋናዬ ይድረሳችሁ፡፡
ለቤት አከራዮቼ (እንደ አባትና እናት) ለሚሆኑልኝ፣ በሐዘኔ በአጠገቤ ላልተለዩት ለአቶ ሲሳይ ወልተጂና ለወ/ሮ መለሰች ሁሪሳ ከነልጆቻቸው እንዲሁም ለጎረቤቶችና ለጓደኞቼ ለመላው ቤተሰብ ለሻምበል ሃ/ገብርኤል ጫቦና ቤተሰቡ፣ ለወ/ሮ ግንብነሽ ጫቦ ከነልጆቿ፣ ለወ/ሮ ቃልኪዳን መሸሻ፣  ለወ/ሮ ተቀባሽ አንጣልና ብርሃን አንጣል ከነልጆቻቸው፣ ለአቶ ሳምሶን አሰፋ ከነቤተሰቡ፣ ለአቶ አለማየሁ አሰፋ፣ ለአቶ ዋሴ አዛዥ ከነቤቴሰቡ ለአቶ የማነ ከነቤተሰቡ፣ ለአቶ ባንጃው ወዜ ከነቤተሰቡ፣ ለአቶ ፈለቀ በፀሎት ከነቤተሰቡ፣
ለውድ ባለቤቴ ለአቶ በላይ ይመርና ለልጆቼ እንዲሁም በስም ላልጠቀስኳቸው ብዙ ወዳጆቻችን … አመሰግናለሁ፡፡
ለድሬድዋ ነዋሪዎችና ለከተማዋ አስተዳደር ለወንድሜ የኤፍሬም አሰፋ ጫቦ ጓደኞችና ጎረቤቶች ሁሉንም… አመሰግናለሁ፡፡
ከኢትዮጵያ ውጭ ላሉ የሬዲዮና ቴሌቪዥን አዘጋጆችና ጋዜጠኞች በሙሉ …
በኢትዮጵያም ሆነ፣ በውጭ አገር ለምትኖሩ ሁሉ … ላደረጋችሁልን፣ ለአባቴ ለከፈላችሁት መስዋዕትነት ሁሉ እግዚአብሔር ይክፈላችሁ፤ አመሰግናለሁኝ፡፡
በመጨረሻ ለፍቶ እንዲያው እንዳይቀር በአገር ውስጥ አንድ የስሙ መጠሪያ እንዲደረግለትና “ቁጥር ሁለት የትዝታ ፈለግ” አባቴ ፅፎ ጨርሶ ነውና ያረፈው፤ ያንንም እቀጥላለሁኝ፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ከአጠገቤ እንደማይለይ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
እመቤት አሰፋ ጫቦና ቤተሰቦቿ

Sunday, 02 July 2017 00:00

‘የተሳሳተ ጥሪ’

  እንዴት ሰነበታችሁሳ!
ከጥቂት ሳምንታት በፊት ነው፡፡ አንድ ወዳጄ አንድ ቀን ከምሽቱ አምስት ሰዓት ገደማ ስልክ ይደወልለታል። በዛ ሰዓት ይደውልልኛል ብሎ የሚያስበው ሰው ስላልነበር፣ የልብ ምቱ ትንሽ ፈጠን ይላል፡፡
“ሄሎ፣ ማን ልበል!” ይላል፡፡
በምላሹ “ሄሎ፣ እከሌ ነኝ፣” የለ፣ “ናፍቀኸኝ ነው” የለ፣ “ድንገት ትዝ ብለኸኝ ነው፣” የለ… “ፖለቲከኛው አለቃህ አሁንም ነክሶህ እንደያዘህ ነው ወይ!” ...ብቻ የሆነች ሴት ድምጽ በአንድ ሴከንድ ስድሳ ያህል ቃላት ታርከፈክፍበታለች፣ የስድብ ቃላት። በእሷ ዐይን ኤልሱን በጣም ጭምት፣ እንደ ኤሊ እየተንቀረፈፈች የምትናገር ነች፡፡ ቂ…ቂ...ቂ… ኧረ እሱ ላይ የደረሰው ነገር አያስቅም፡፡ ሊያስበው የሚችለውንና፣ የማይችለውን የስድብ አይነት ላይ በላይ ትዘረግፍበታለች፡፡ ስድቦቹ አይደለም በዚህ ዘመን በድሮው የ‘ሬድ ላይት’ ሰፈሮች እንኳን የተረሱ ናቸው፡፡ ከእሱ ጋር ቤተሰቦቹ አልቀሩ፣ ጓደኞቹ አልቀሩ፣ ሁሉም ‘የድርሻቸው’ ተሰጣቸው። ወላ ነጠላ ሰረዝ፣ ወላ አራት ነጥብ የሌለው አጥንት ሰባሪ ዘለፋ ታወርድበታለች፡፡ ቢቸግረው ስልኩን ይጠረቅመዋል፡፡ እንደገና ስትደውል አያነሳም፡፡ ደጋግማ  ስትደውል ለክፉም ለደጉም ብሎ ያነሳዋል።
“አንተ ማን አባክ ሆንክና ነው የምትዘጋብኝ!…” ብላ የአዲስ አበባን ቀለበት መንገድ ሦስት እጥፍ የሚረዝም የስድብ መአት ትደረድርለታለች። “ምን አለች በለኝ…” ብላ ታላላቅ ባለስልጣኖች እንደምታውቅ፡ ልቡ እስኪጠፋ እንደምታስጠበጥበው ፎከራ… “አንተን ልክ ካላስገባሁ ከምላሴ ጸጉር!” ምናምን ብላ ትዘጋበታለች፡፡
እኔ የምለው መጀመሪያ ስም አይቀድምም እንዴ!  “አንተን ማን ልበል፣” ምናምን አይነት ማረጋገጫ!
በማግስቱ በጊዜ ይደወላል ያው ቁጥር፡፡ አያነሳውም። ደጋግሞ ከተደወለ በኋላ “እባክህ ስልኩን አንሳልኝ፣” የሚል የጽሁፍ መልእክት ይደርሰዋል፡፡ ቀጥሎ ሲደወል ይነሳል፡ እያለቀሰች ይቅርታ ትጠይቀዋለች፡፡ ለካስ የገዛ ጓደኛዋን ይዞ የፈነገላት ‘ቦይፍሬንዷ’ መስሏት ነው፡፡ አሀ… ‘ቦይፍሬንድ’ስ ቢሆን ይሄን ያህል መሰደብ አለበት እንዴ! ማንኛውም ጨረታ ላይ እኮ “ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ማስተላለፍም ሆነ መሰረዝ ይችላል…” ምናምን የሚባል ነገር አለው (ሴትዮዋ ከሰማችን ሁለተኛው ዙር ለእኛ ነው፡፡)
በተለይ ደግሞ ከመሸ በኋላና በሌሊት የሚደውሉ የተሳሳቱ ጥሪዎች የምር አስቸጋሪ ናቸው፡፡
ይቺን ስሙኝማ፡፡ የቴሌፎን ኩባንያው ፕሬዝደንት ሌሊት እንቅልፉን ይለጥጣል፡  ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ገደማ ስልኩ ሲጮህ ይነቃል፡፡
“ሄሎ!”
“ሄሎ፣ የቴሌፎን ኩባንያው ፕሬዝደንት ነህ?”
“አዎ ነኝ፣  ምን ልርዳዎ?”
“እስቲ ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት በተሳሳተ ጥሪ ከሚጣፍጥ እንቅልፍህ መቀስቀስ ምን እንደሚመስል አሁን ንገረኝ!” አለውና አረፈው፡፡
እናማ ‘የተሳሳተ ጥሪ’ ነገር አስቸጋሪ ነው፡፡
እናማ…ይሄ ‘የተሳሳተ ጥሪ’ ነገር የምር አስቸጋሪ ነው፡፡ የምር አሁን፣ አሁን የማትጠየቁት የሰው አይነት፣ የመሥሪያ ቤት አይነት የለም፡፡ አሁን እኔ ምኔ ‘እንትን ጋራዥ’ን ይመስላል! ቂ…ቂ…ቂ…  እናማ… ጥሪው ‘ከመሳሳቱ’ ሌላ የደዋዮቹ ባህሪይ ከአገር ሊያሰወጣን ምንም አልቀረው…  ከአገር የሚያስወጡ ነገሮች ያልበዙብን ይመስል!
ከአገር የመውጣት ነገር ካነሳን፣ ከዚህ በፊት አንስተናት ልትሆን የምትችል ነገር ላውራችሁማ። ‘በዛኛው ዘመን’ የሆነ ነው፡፡ ውጪ ተምሮ የመጣ ሰው ነው፡ ለምርምር ወደ ምዕራብ ኢትዮጵያ ይላካል። ታዲያላችሁ… “ይህ ሰውዬ ድብቅ የፖለቲካ ዓላማ ሳይኖረው አይቀርም ተብሎ  እያንዳንዱ እንቅስቃሴው በወታደር ይጠበቃል፡፡ ታዲያ ጧት፣ ጧት እየተነሳ ይሮጣል፣ ወታደሮችም ይከተሉታል። ይሀ ነገር ለተወሰነ ጊዜ ይቀጥልና ከወታደሮቹ ይላመድና በራሱ እየሮጠ መመለስ ይጀምራል። ታዲያ አንድ ቀን በወጣበት ይቀራል፡፡ በሳምንቱ ገደማ… “ሩጫ ስለፈቀዳችሁልኝ አመሰግናለሁ፣” የሚል የስልክ ጥሪ ይደርሳል...ከኖርዌይ። (ሩጫ በሸታና እድሜን ማባረሪያ ብቻ ሳይሆን ‘መብረሪያ’ ሊሆን ይችላል ለማለት ያህል ነው።)
“ሄሎ!”
“ሄሎ፣ ማን ልበል?”
“ሄለንን አቅርብልኝ፡፡”  ጥያቄ ሳይሆን ትእዛዝ፡፡
“ጌታዬ ተሳስተዋል፡ ሄለን የሚባል ሰው የለም፡፡”
“አታቀርብልኝም፣ ማለት ነው?”
“ጌታዬ እንደዛ የሚባል ሰው የለም አልኩዎት እኮ!”
“በአንተ ቤት ማታለልህ ነው! ደግሞ ንገራት፣ እናትሽ ሆድ ብትገቢ አታመልጪኝም በላት፡፡ ይሄ የምትኩራሪበትን መልክሽን የህጻናት ማስፈራሪያ ባላደርገው እኔ አይደለሁም ብሏል በላት!”  ጥርቅም!
ሰውየው ይደውልና…
“ይሄ ቁጥር ስንት ነው?” ይላል፡፡ በወዲያኛው ጫፍ ያለው ምን ብሎ ቢመልስለት ጥሩ ነው… “አንተ ንገረኝ እንጂ፣ አንተ አይደለህ እንዴ የደወልከው?” አሪፍ መልስ አይደል!
እኔ እኮ ይሄ ሞባይል የሚሉት ነገር…ፎካሪው መብዛቱ! “ተሳስተዋል፣” “ሌላ ቁጥር ነው የደወሉት፣” እያላችሁት ያለ ጋሻና ጦር ቀረርቶውን ይለቅባችኋል። ሄለን የለችም ማለት፣ “ሄለን የለችም” ማለት አይደለም እንዴ!
ሀሳብ አለን…የተሳሳተ ቁጥር በደወሉ ጊዜ ምን ማለት እንደሚገባዎ የሁለት ወር ልዩ የክረምት ስልጠና ምናምን ይዘጋጅልን፡፡ አሀ..እነሱ በተጣሉት፣ እነሱ በተፈነጋገሉት፣ እነሱ በተካካዱት…እኛ ስድቡን የመሸከም ውል ተዋውለናል እንዴ!
“ሄሎ!”
“ሄሎ!”
“እስቲ ባንጃውን አቅርብልኝ…” ቁጣ፡፡
“ይቅርታ፣ ተሳስተዋል፡፡”
“ስማ፣ ሄደህ የምታሾፍበት ላይ አሹፍ፡፡ አሁን ባንጃውን ታቀርብልኛለህ፣ አታቀርብልኝም!”
ባንጃው ምንም ያድርግ ምን ጦሱ ወደ እናንተ ይመጣል፡፡ (ስሙ ግን ብዙ ነገር ማድረግ የሚችል ያስመስለዋል፣ ቂ…ቂ..ቂ…)
“ጌታዬ ምናልባት ሲደውሉ ቁጥር ተሳስተው ይሆናል፡፡”
ጆሯችሁ ላይ ጥርቅም!
ለነገሩ ዘንድሮ የባህሪይ ነገር፣ የስነ ምግባር ነገር ግራ እየገባን “ሰውረነ ከመአቱ…” አይነት የሚያስብል ሆኗል። ስልክ ደግሞ ሳይታዩ እንደልብ ለመሆን ስለሚያመች ይኸው እንግዲህ የተነጠቀውም፣ የተፈነገለውም፣ የተጭበረበረውም…እኛ ላይ ንዴቱን ይወጣል፡፡
ለመሳሳቱ እናንተ ምክንያት የሆናችሁ ይመስላል። ከተናደደ ቴሌ ጆሮ ላይ አይጠረቅመውም እንዴ!
እንግዲህ ባንጃው ማን ይሁን፣ ምን ይሁን የሚያውቅ ይወቀው፡፡
ይቺን ስሙኝማ…ሰውየው በኦፕሬተር በኩል ይደውላል፡፡  
“ሄሎ!”
“ሄሎ፣ እንዴት ይዞሀል?”
“ደህና ነኝ፡፡ ስማ ትንሽ ብር ስለቸገረኝ መቶ ብር ያህል በባንክ ላክልኝ፡፡”
ድምጹ ይለወጣል፡፡ “ስልኩ ይንኮሻኮሻል…የምትለው አይሰማኝም፡፡”
“መቶ ብር በባንክ ላክልኝ ነው ያልኩህ…”
“ምን አይነት ስልክ ነው… የምትለው ምንም አይሰማኝም!”
ይሄኔ ኦፕሬተራ ጣልቃ ትገባና “እኔ የሚለው ይሰማኛል፣” ትላለች፡፡ ይሄኔ አጅሬው ምን ቢል ጥሩ ነው…
“እንግዲያው መቶ ብሩን አንቺ ላኪለት፡፡”
ደህና ሰንብቱልኝማ!  


ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ጐልማሣ ፈረስ መጋለብ በጣም ያምረውና ወደ ገበያ ፈረስ ሊገዛ ይሄዳል፡፡ ገበያ ውስጥ ብዙ ፈረስ የያዘና አንድ ፈረስ ብቻ የያዙ ሁለት ነጋዴዎች አሉ፡፡ ወደ ባለ ብዙው ፈረስ ይጠጋና፤
“ይሄ ስንት ነው?” ይለዋል፡፡
ባለብዙው ፈረስ - “ሁለት ሺ”
ፈረስ ገዢ - “ይሄስ?”
ባለብዙው ፈረስ - “ሁለት ሺ ሦስት”
ፈረስ ገዢ - “ይሄኛውስ?”
ባለብዙው ፈረስ  “ሁለት ሺ አራት”
ፈረስ ገዢ - “እንዴ-- አንዴ አንድ ዋጋ ከተናገርክ መቀጠል ነው ማለት ነው ሥራህ?”
ባለብዙው ፈረስ - “ጊዜው ነው ጌታዬ፡፡ የሚጨምር ነው እንጂ የሚቀንስ ነገር የለም”
ፈረስ ገዢው ይተወውና አንድ ፈረስ ወዳለው ነጋዴ ይሄዳል፡፡
ፈረስ ገዢ - “ይሄ ፈረስ ስንት ነው ዋጋው?”
ባለ አንድ ፈረስ “ስድስት ሺ”
ፈረስ ገዢ - “አሃ እዛኮ በሁለት ሺ አግኝቻለሁ”
ባለአንድ ፈረስ - “እኔ ሻጭ ነኝ፡፡ ይዤ እምወጣው አንድ ፈረስ ነው፤ እሱን ሸጬ መግባት ነው አላማዬ”
ፈረስ ገዢ - “ታዲያ በጣም አስወደድከዋ?”
ባለ አንድ ፈረስ - “የፈረሱ አይነት ነው፡፡ እንደምታየው ሠንጋ ፈረስ ነው፤ የዚህ ዓይነት ፈረስ የትም አታገኝ”
ፈረስ ገዢ - “ጥሩ፡፡ እገዛሃለሁ፡፡ ግን ልዩ ጥቅሙ ምንድነው?”
ባለአንድ ፈረስ - “እሱን ስትጋልበው ታየዋለህ”
ፈረስ ገዢ - “መልካም”
ፈረሱን ገዝቶ ይሄዳል፡፡
ቤቱ እንደደረሰ የግልቢያ ልብስ ይቀይርና ፈረሱ ላይ ወጥቶ ወደ ሠፈሩ ገና ብቅ ሲል፤ በሀብታምነቱ የሚያውቁት የሠፈሩ ሰዎች፤
“ፈረስ ማለት ይሄ ነው እንጂ!”
“ለእኛም ቢሆን ለአይናችን እንዲህ ያለ ፈረስ አይተን አናውቅምኮ፤ አለፈልን ዘንድሮ”
“የተጋጋጠ ፈረስ ለጋሪ እያሰለፉ ሲያሰቃዩን ከርመው ዛሬ ዕውነተኛ ፈረስ መጣ”
የማይሰጥ ዓይነት አስተያየት የለም፡፡ ጉድ ተባለ!
ባለፈረሱ መጋለብ ጀመረ፡፡ ለካ ፈረሱ አልተገራ ኖሮ አንዴ ሽቅብ ይዘላል፡፡ አንዴ ሳያስበው ሽምጥ ይሮጣል፡፡ በልጓም ቢለው፣ በእግሩ ቢለው፣ ከኮርቻው ቢነሳ፣ ወደፊት ቢያጐነብስ አልቆም አለ፡፡ ሩጫውን ቀጠለ፡፡
አንድ ጋላቢውን የሚያውቅ ወዳጁ ከቤቱ ሲወጣ አየውና፤
“አያ፤ ኧረ ወዴት ነው የምትሮጠው?” ሲል ይጠይቀዋል፡፡
ጋላቢውም፤
“እኔ ምን አውቃለሁ፤ ፈረሱን ጠይቀው” አለው፡፡
*   *   *
መልክና ቁመናውን ዓይተን ያልተገራ ፈረስ ከመግዛት ይሰውረን፡፡
“ስትጋልበው ታየዋለህ” እየተባልን የወጣንበት ፈረስ መጨረሻው አያምርም፡፡ በጊዜ ያልመከርንበት ገበያ ኪሣራው ብዙ ነው፡፡ ብቸኛ ሽያጫችንን ለማሳመር ብለን ያወዳደስነው ያልተጠና ነገር ጉዳቱ በርካታ ነው፡፡ የዛሬ ባለሀብትነታችንን አይቶ የሚያሞግሰን ሁሉ ዕውነተኛ ደጋፊ ነው ብለን ማሰብ አደገኛ ነው፡፡ ከሚጨምር ዋጋ ያድነን! ካልተገራ መመሪያ፣ ካልተገራ አዋጅና ካልተገራ ተከታይ ይሰውረን!
የሥልጣን ፖለቲካ ልሂቃን እንዲህ ይላሉ፡፡ መቀበል አለመቀበል እንደየመሪው ይለያያል፡፡
“ብቸኛ ተፈላጊ ለመሆን ህዝብ ባንተ እንዲተማመን እንዲመካ አድርግ፡፡ ህዝቦች ደስታና ብልጽግናን ካንተ ወዲያ ሊያገኙ እንደማይችሉ አድርገህ ቃኛቸው፡፡ ካንተ በላይ ሊያደርጋቸው የሚችል ዕውቀት አትስጣቸው”
ታዋቂው የፕሬዚዳንት ኒክሰን አማካሪ ሔንሪ ኪሲንጀር ራሱን ያቆየው፣ እዛም እዛም በሚነሱት ጉዳዮች ውስጥ ስለሚገባ፣ እሱን ማጣት ለፕሬዚዳንቱ በጣም ጐጂ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡ አይተኬ በመሆኑ ነው፡፡ አይተኬነት የራሱ ችግር አለው፡፡ አጠቃላዩ ዕምነት ግን አይተኬ ነኝ የሚል ግለሰብ፤ ውሎ አድሮ አይነኬ ነኝ ማለቱ ነው፡፡ ከእኔ በላይ ላሣር ማለቱ ነው፡፡ ከዚህ ይሰውረን!
ፀሐፍት፤ “የኮለምበስ ስትራቴጂ” የሚሉትን አንርሣ፡፡ “ሁሌ ጠንካራ ጥያቄ ይኑርህ፡፡ የራስህን ትልቅ ዋጋ አስቀምጥ፡፡ አታወላውል፡፡ በኩራት ከፍተኛው ደረጃ ካለው ሰው እኩል ቁም፡፡ አንድ ስጦታ ለበላይህ ስጥ” ይህን ስትራቴጂ የሚጠቀሙ አያሌ ናቸው፡፡ አንዱ የሙስና በርም ይሄ ነው፡፡ እኩያ ሙሰኞች፤ እኩያ የፖለቲካ አቅም እየፈጠሩ የሚከስቱት ነው፡፡ ህንፃዎቻችን፣ መኪናዎቻችን፣ መሬቶቻችን በምንና እንደምን ተገኙ ብሎ መጠየቅ የአባት ነው፡፡ መጠንቀቅ ያለብን፤ ማኪያቬሊ እንደሚለው፤ “ከመወደድ መፈራት ይሻላል፡፡ ምነው ቢሉ ፍርሃትን መቆጣጠር ይቻላል፡፡ መውደድን ግን በፍፁም ለመቆጣጠር አይቻልም፤” ከሚል አስተሳሰብ ነው፡፡ ስለዚህ ሰዎች የሚመኩብን አብረውን ለመሆን ካላቸው ፍቅር ከሚሆን ይልቅ እኛን በማጣት ከሚፈጠርባቸው ፍርሃት የተነሳ ቢሆን ይሻላል - እንደማለት ነው፡፡ ይሄ በራሱ አደጋ እንደሚሆን ልብ እንበል፡፡
ሥልጣን ላይ ለመቆየት ከሚጠቀሱ ዘዴዎች መካከል አንድ ፈረንጆች የሚጠቅሱት አባባል አለ፤ “ኦርጅናሌ ሀሳብህን ለሚቻቻሉህ ጓደኞችና ልዩ ፍጡር መሆንህን ለሚያደንቁ ወዳጆችህ ብቻ አማክር” ይላሉ፡፡ ዕውነቱ ግን ህዝቡ ከልቡ ያልመከረበት ነገር ፍሬ - አልባ መሆኑ ነው፡፡ ህዝብን ማማከር ሲባል፤ ነገር ካለቀ ከደቀቀ በኋላ መሆን የለበትም፡፡ ፈረንጆቹ “የሞተ ፈረስ መጋለብ” የሚሉት ይሆናልና (Riding a dead horse) የተበላ ዕቁብ የሚለው ነው አበሻ፡፡ ባለቀ ጉዳይ ላይ መምከር አንድም “እንዳያማህ ጥራው” ነው፡፡ አንድም “ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ ነው፡፡
ሞንጐላውያን ቻይናን በወረሩ ጊዜ መሪያቸው ጄንጂስ ካን፤ ከሁለት ሺ ዓመት በላይ የቆየው የቻይና ባህል እሴት፤ አይታየውም ነበር፡፡ ይልቁንም ለፈረሶቹ ግጦሽ የሚሆን በቂ ሣር ያልበቀለባት አገር በመሆንዋ፤ “ቻይናውያንን ከምድረ ገጽ አጥፍቶ ሣር ማብቀል ይሻላል” የሚል አቋም ነበረው፤ ሆኖም ብልሁ አማካሪው ዬሎ ቹሳይ “አገሪቱን ከማጥፋት ይልቅ እዚያ የሚኖረውን እያንዳንዱን ነዋሪ ግብር ብታስከፍለው ያገር ሃብት ትሰበስባለህ” አለው፡፡ ካን አማካሪው ያለውን ፈፀመ፡፡ ቀጥሎ ኬይፌንግ ከተማን ወረረና ነዋሪውን ላጥፋው አለ፡፡ አማካሪው ቹሳይ “አይሆንም የቻይና ጥበበኞችና መሀንዲሶች ተሰብስበው የሚገኙት እዚህ ነውና ከምታጠፋቸው ተጠቀምባቸው” አለው፡፡ ጄንጂስ ካን አማካሪው የነገረውን አደረገ፡፡ ተጠቀመ። ወገናዊነት በሌለበትና ኢ-ፍትሐዊ ባልሆነ መንገድ ግብር ማስገባት አግባብነት አለው፡፡ ምሁራንንም በአግባቡ መጠቀም ሥልጣኔ ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ግን እንደ ዬሉ ቹሳይ ያለ አማካሪ ያሻል፡፡ መካር አሳስቶኝ ከሚባልበት ዘመን መውጣት ይጠበቅብናልና!
በሀገራችን ዴሞክራሲ ሙሉ በሙሉ እንደሰፈነ የሚያስመስሉ አያሌ አማካሪዎች ናቸው፡፡ ልማት ያጠጠባት፤ ፍትህ የበለፀገባት፤ መልካም አስተዳደር ቤት ደጁን ያጣበበባት አገር ናት እያሉ፤ ራሳቸው ግን ያልለሙ፣ ከኢ-ፍትሐዊነት ያልፀዱ፣ ያስተዳደር ጉድለት የሚፈጽሙ፣ ግን በአደባባይ ችሎት ስለ ንጽህናቸው የሚጮሁ አያሌ ናቸው፡፡ “ላም የሌለው ጉረኛ፤ አፉን በወተት ይጉመጠመጣል” ማለት እኒሁ ናቸው፡፡

Saturday, 24 June 2017 11:25

ቆቅ ሆነን

እየው ኖርን ሳንዋደድ፣ እድሜም ገፋ እንደ ዘበት፣
ለሰው ይምሰል ጥላችንም፣ እንደፍቅር ተወራለት፡፡
ባንድ ማድ፣ እየበላን እየጠጣን፣
ለሚያየን አስጎምጅተን፣ እያስቀናን፤
አለን ሳንተኛ፣ ሳናንቀላፋ፣
እኛው በኛ፣ ስንጋፋ፡፡
ቆቅ ሆነን፣ ስንጠባበቅ፣
ደግሞ- የዋህ መስለን ስንሳሳቅ፤
ብዙ…. ብዙ! ዘመን፣ ተቆጠረ፣
ቂም ሳይፈታ፣ እንደከረረ!፡፡
      ጋሻው ሙሉ

Saturday, 24 June 2017 11:23

እግዜር ግንበኛ ነው

የናንተን አላውቅም፣ እኔ ግን እላለሁ
እውነቱን ለእግዚአብሔር፣ እመሰክራለሁ፡፡
ጥሩ! አድርጎ እሚያንጽ፣ እግዜር ግንበኛ ነው
ያለ ጭስ ፋብሪካ፣ ሰውን ገጣጠመው፡፡

     በአምስት የስነ ልቦና ምሩቃን ከአንድ አመት በፊት የተቋቋመው ‹‹አብርሆት›› የስነ-ልቦና አገልግሎት ማዕከል በሳለፍነው ሳምንት በይፋ ተመርቆ ስራ ጀመረ፡፡ ማዕከሉ አራት ክፍሎች ያሉት ሲሆን እነዚህም የህፃናትና የወጣቶች የአዕምሮ ህመምና የጋብቻ፣ የሚዲያ የጥናትና ምርምር እንዲሁም የስልጠና እና በአደጋ ምክንያት ሰዎች የንግግር ክህሎታቸውን ሲያጡ የሚታከሙበት የንግግር ህክምና ዲፓርትመንቶች እንደሆኑ ታውቋል። በተለይ የህፃናትና የታዳጊዎች ዲፓርትመንት የአዕምሮ እድገትና የንግግር መዘግየትን ጨምሮ ሌሎች እክሎችን ምርመራና ምዘና በማድረግ ህክምና ይሰጣል ተብሏል፡፡ የስነ-ልቦና ጉዳይ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለው ተቀባይነት፣ የስነ ልቦና መንስኤዎችና ወሳኝ መፍትሄዎች ደግሞ በጥናትና ምርምር ክፍሉ ይከናወናል ተብሏል፡፡
ስልጠናን በተመለከተ ማዕከሉ ለተቋማት፣ ለግለሰቦችና በተለይ የስነ-ልቦናና የአዕምሮ ችግር በቤተሰባቸው ውስጥ ላለ ወላጆችና አሳዳጊዎች በየደረጃው እንደሚሰጥም ከማዕከሉ መስራቾች አንዱ የሆኑት አቶ ሄኖክ ኃይሉ ገልፀዋል፡፡ ከሱስ፣ ከአዕምሮ ህመምና ከተያያዥ ችግሮች ጋር ያሉ ህሙማን ተኝተው መታከምና ማገገም የሚያስፈልጋቸው ከሆነም ለ“ቤዛ” እና “ስጦታ” ከተባሉ የስነ- አዕምሮ ህክምና ማዕከላት ጋር ማዕከሉ ባደረገው ስምምነት የሚታከሙበት ሁኔታ መመቻቸቱም ተገልጿል፡፡
ከሙያው ጋር ለ30 ዓመት እንደሚተዋወቁ የገለፁት ረዳት ፕሮፌሰር ፍሬው ከፍያለው፤ ወጣቶቹ ማዕከሉን ለማቋቋም ከፈቃድ ማውጣት ጀምሮ የገጠማቸው ውጣ ውረድ አልፈው ለዚህ መብቃታቸውን አድንቀው፤ በስራቸው ታማኝና ጠንካራ ሆነው ህዝብን በሀቅ እንደሚያገለግሉ እመተማመናለሁ ያሉ ሲሆን ወደፊትም በሚችሉት መጠን ማዕከሉንና ወጣቶቹን ለመደገፍ ቃል ገብተዋል፡፡ ‹‹አገራችን ላይ ሙያ ተሸጦ የሚተረፍበት ደረጃ ላይ አልተደረሰም›› ያሉት መስራቾቹ፤ “እኛም ሙያ ሸጠን ለማትረፍ ሳይሆን በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ ክፍተት በአቅማችን ለመሙላት በጣም መጠነኛ በሆነ ክፍያ አገልግሎቱን ለመስጠት ማዕከሉን አቋቁመናል” ብለዋል፡፡

   በደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ማንሳት ስራ ላይ ተሰማርቶ የቆየው ሮዝ ቢዝነስ ግሩፕ በሀገር ውስጥ ያመረታቸውን ባለ ሶስት እግር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል፡፡
ኩባንያው የጃፓን ቴክኖሎጂን የታጠቁ፣ ባትሪያቸውን በኤሌክትሪክ በመሙላት ብቻ የሚጓጓዙ፣ ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎችን ደብረ ዘይት አካባቢ በገነባው ፋብሪካው ማምረቱን የኩባንያው ባለቤት አቶ ሮቤል እስጢፋኖስ አስታውቀዋል፡፡
ፋብሪካውን ከአንድ ዓመት በፊት መገንባት እንደጀመሩ የጠቆሙት አቶ ሮቤል፤በአሁኑ ወቅት በአንድ ሰዓት አንድ የኤሌክትሪክ ባለ ሶስት እግር መኪና ማምረት እንደሚችል አስረድተዋል፡፡ ለ4 ሰዓት በተሞላ ባትሪ መቶ ኪሎ ሜትር ድረስ መንዳት ያስችላል ያሉት ባለቤቱ፤ ኤሌክትሪክ ለመሙላትም 7 ብር ብቻ እንደሚጠይቅ ጠቁመዋል፡፡
ተሽከርካሪው በዋናነት ከከተማ ውጪ ላሉ አካባቢዎች የሚያገለግል ሲሆን ለሰፋፊ ግቢ የውስጥ ለውስጥ እንቅስቃሴ፣ ለሽርሽር እንዲሁም ለተለያየ ዓይነት የትራንስፖርት አገልግሎት የሚውል ነው ተብሏል፡፡ ሹፌሩን ጨምሮም 7 ሰዎች የመያዝ አቅም አለው፡፡
ኩባንያው ተሽከርካሪውን ከኢትዮጵያ አልፎ ለምስራቅ አፍሪካ ገበያ ለማቅረብ ማቀዱንም ባለቤቱ ባለፈው ሰኞ፣ በተሽከርካሪው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ተናግረዋል፡፡
የኩባንያው መነሻ ካፒታል 24.9 ሚሊዮን ብር መሆኑንና ለ105 ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠሩን የጠቀሱት አቶ ሮቤል፤የተሽከርካሪውን ዋጋ በተመለከተ ገዥዎች ሲመጡ ብቻ ቢያውቁት ይሻላል በሚል ከመግለፅ ተቆጥበዋል፡፡   

 በስራ ፈጠራ፣ አዲስ ቴክኖሎጂ በመፍጠርና በመቅዳት የተለያየ ውጤታማ ደረጃ ላይ የደረሱ ስኬታማ ሰዎች ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት “የአሸናፊነት ጉዞ ወደ ስራ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂ መቅዳት፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂ ማፍለቅና ኢንተርፕረነርሺፕ” የተሰኘ የኮሌጅ ቶክ ሾው ሊጀመር ነው፡፡ ቶክ ሾውን የሚያቀርበው ኤዲቲ የንግድ ፕሮሞሽን አገልግሎት ሲሆን ይህ ቶክ ሾው የሚካሄደው ከሰኔ 2009 እስከ ሰኔ 2010 ለአንድ ዓመት እንደሆነ አዘጋጁ ገልጻል፡፡
ኮሌጅ ቶክ ሾው ዝግጅቱ በአዲስ አበባ በሚገኙ 13 የመንግስትና የግል ቴክኒክና ሞያ ኮሌጆች እንደሚካሄድም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዋና አላማው በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ኮሌጆች በተለያዩ ደረጃዎች የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ላይ የሚገኙ ተማሪዎች ተመርቀው ሲወጡ ቴክኖሎጂን በመቅዳት፣ አዲስ በመፍጠርና በመመራመር የራሳቸውን ስራ ውጤማ ሆነው እንዲሰሩ፣ የሚገጥማቸውን ችግሮች በምን መልኩ ማለፍ እንዳለባቸውና በአጠቃላይ ውጤታማነት ዙሪያ ልምድ ካላቸው ሰዎች ልምድ እንዲቀስሙ ማድረግ ነው ተብሏል፡፡

     ከሁለት ዓመታት በፊት ተከፍቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ጌትፋም ኢንተርናሽናል ሆቴል ባለ 5 ኮከብ ደረጃን አገኘ፡፡ ሁኔታውን አስመልክቶ ሰሞኑን በሆቴሉ በተካሄደው ሥነ ስርዓት ላይ እንደተገለፀው፤ ሆቴሉ ዓለም አቀፋዊ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ለደንበኞቹ ሲሰጥ ቆይቶ በቅርቡ በተካሄደ ፍተሻና ቁጥጥር መስፈርቱን አሟልቶ የተገኘ በመሆኑ ባለ 5 ኮከብ ደረጃ ተሰጥቶታል፡፡ የሆቴሉ ባለቤት አቶ ጌታሁን በሻህ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ሆቴሉ አሁን ላለበት ደረጃ እንዲበቃ ቤተሰቦቻቸውና መላው ሠራተኞች የከፈሉት መስዋዕትነት ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡ ሆቴሉ ባለ 5 ኮከብ ደረጃ ያለው መሆኑ ለእሳቸውም ሆነ ለሆቴሉ ሠራተኞች ከፍተኛ ደስታ እንደፈጠረላቸው ጠቅሰው፤ በቀጣይም ደንበኞቻቸውን በጥራትና በብቃት ለማስተናገድ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።

 የሚከተለውን የፃፉልን እጓለ ገብረ ዮሐንስ ናቸው፡፡
“የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ” በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ ነው፡፡
 በግሪክ ሜቶሎጂ የሚገኝ አንድ ትልቅ ተረት አለ፡፡
(ይህም ስለ ፕሮሚሴቭስ የሚነገረው ነው፡፡ ትልቅ ምሥጢር በውስጡ ደብቆአል፡፡ ፕሮሚሴቭስ በሚል አርእስት የቀድሞውን ተረት መሠረት በማድረግ፣ ኤስሂሎስ የሚባለው ትራጀዲን የፈጠረ ባለቅኔ፣ አንድ ትሪሎጂ - ማለት ሦስት ድራማዎች ጽፎአል፡፡ እሱን በመከተል ሸሊ ባይረን ጌቴ ጽፈዋል፡፡ የፕሮሚሴቭስ መንፈስ በአውሮፓ የመንፈስ ታሪክ ውስጥ መካከለኛውን መሥመር የያዘ ነው፡፡ አሁን የጠቀስናቸው ሰዎች በአውሮፓ የሥነ ጽሑፍ ጠፈር ላይ በጣም ጐልተው የሚታዩ ከዋክብት ናቸው፡፡)
የፕሮሚሴቭስ ተረት እንደሚቀጥለው ነው፡፡ ፕሮሚሴቭስ በከፊል አምላክ፣ በከፊል ሰው የሆነ ሕላዌ ነበር፡፡ በከፊል አምላክ እንደመሆኑ ዐሥራ ሁለቱ የግሪክ አማልክት በኦሉምቦስ ተራራ ሆነው ስለ ሰውና ስለ ዓለም አስተዳደር ሲመክሩ ይሰማ ነበር፡፡ በከፊል ሰው እንደመሆኑ የሰው ሥቃይና መከራ በጣም ያሳዝነው፣ ይጸጽተው ነበር፡፡ ሰው ቤት ንብረት ሳይኖረው በበረሃ፣ በጫካ፣ በዱር፣ በገደል፣ በዋሻ፣ በቁር፣ በሀሩር እንዲኖር ተፈርዶበት ነበር፡፡ ይህ መሆኑ አማልክት መክረው ዘክረው፣ ለሰው የዕውቀት ምንጭ የሆነውን ብርሃንን የሰጡት እንደሆን ከዕለታት ባንድ ቀን ሰጭነታቸውን ክዶ፣ በነሱ ላይ በመነሳት የሚያምፅ መሆኑን በመረዳት፣ ብርሃንን ከሰዎች ደብቀው ከማይደርሱበት ቦታ በመሠወራቸው ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ሰዎች በጭለማና የርሱ ተከታይ በሆኑት ችግሮች ሥር ሲሰቃዩ ይኖራሉ፡፡
ይህ የሰዎች መራራ ዕድል ወገናቸው በሚሆን በፕሮሚሴቭስ ላይ ርህራሄ አሳድሮበት፣ ብርሃንን አማልክት አርቀው ከደበቁበት ሰርቆ ለሰዎች ወስዶ ሰጠ፡፡ ያን ጊዜ ማናቸውም ነገር ግልጽ ሆኖ ታያቸው፡፡ በብርሃን ምክንያት ጥበብና ማናቸውም የዕውቀት ስልት ስለተገለጸላቸው፣ ራሳቸውን ከገዛ ራሳቸው በተገኘው ዘዴ ለማስተዳደር ጀመሩ፡፡
ፕሮሚሴቭስን ግን ለሰዎች ብርሃንን ሰጥቶ፣ በጐ በመሥራቱ አማልክት ቀንተው፣ በብርቱ ስቃይ ይቀጣ ዘንድ አዳኝ ከማይደርስበት ገደል ላይ ከቋጥኝ ድንጋይ ጋር በሰንሰለት ተቆራኝቶ፣ አሞራ ለዘለዓለም እንዲበተብተው ፈረዱበት፡፡
*   *   *
ከፕሮሚሴቭስ ዕጣ -ፈንታ ይሰውረን፡፡ ይህ ፕሮሚሴቭስ የሰውን ዕድል ለማሻሻል የሚታገሉት የዕውቀት ሰዎች፣ የመምህራንና የሊቃውንት ምሳሌ ነው፡፡ እሱ ብርሃንን አማልክት ከደበቁበት ቦታ ወስዶ ለሰው እንዳበረከተ ፣ የዕውቀት ሰዎችም ዕውቀት በመለኮታዊ ምሥጢርነት ከሰው ተደብቃ ስትኖር ሳለ በብዙ ትግል አግኝተው፣ ከገዛ ራሳቸው አሥርፀው የወገኖቻቸውን ዕድል ለማሻሻል ያበረክታሉ፡፡ ዋጋቸውም ሌላ ሳይሆን ስቃይ መከራ ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል ሶክራቲስ በመርዝ ተገድሎአል፡፡ ጆርዳኖ ብሩኖ የጧፍ ቀሚስ ተጐናጽፎ በእሳት ተቃጥሎአል፡፡
እነዚህ ሰዎች እንደ ጧፍ መብራት ማለት ናቸው፡፡ ራሳቸው ነደው ተቃጥለው ያልቃሉ። ለሌሎች ግን ብርሃን ይሰጣሉ፡፡ የፕሮሜሴቭስ ምሳሌ አንድ ትልቅ ሕግ ጉልህ አድርጐ ያሳያል። ይህም “ዕውቀት በሥቃይ የሚገኝ ነው” (Learn through suffering) የሚል ነው፡፡  
ልጆቻችንን ይህን ለሌሎች ስንል መታገል፣ መስዋዕት  ማድረግ እንደምን እናስተምር? ብርሃን የሚያመጡ ሰዎች ያስፈልጉናል፡፡ ዕውቀትን ለሀገር ለማጎናፀፍ የሚጥሩ መምህራን ያሹናል፡፡ የዕውቀት ብርሃን ለመጪው ትውልድ ታትሮ ለማስተላለፍ፣  ልብና ልቡና ይፈልጋል፡፡ አረፍ ብሎ ወዴት እያመራን ነው ብሎ መጠየቅን ግድ ይላል፡፡ ዕውቀት ከትምህርት ብቻ የሚገኝ አይደለም፡፡ ከኑሮአችን፣ ከልምዳችን፣ ከትግላችን እንጂ፡፡ ይህ ወረድ ብሎ አፈሩን መዳሰስን፣ ህዝቡን ማግኘትን፣ የልብ ትርታውን ማወቅን ይጠይቃል፡፡ ምን ጎደለው? ስለዚህ ጉዳይ ግንዛቤ አለ ወይ? በምን ዓይነት መንገድ የጎደለውን ዕውቀት ለማሟላት እችላለሁ? ማለትን ይጠይቃል፡፡ መንገዱን ካገኙ በኋላም፤ ጧት ማታ ሳይታክቱ መታተርን ይጠይቃል፡፡ ይህን ከልብ ካደረግን አገር መውደድ ገብቶናል፡፡ ያንድ ሰሞን ሞቅ ሞቅ ብቻ አገርን ከገባችበት ማጥ አያወጣትም፡፡ “ኦሆ በሀሊ፣ ያርጓጅ አናጓጅ፣ በደመቀበት ቦታ ሁሉ የሚያጨበጭብ አንድም የተለየ ነገር ለማስገኘት አይችልም” ይላሉ ዶክተር እጓለ፡፡ ሉቃስን በመጥቀስም እንዲህ ይሉናል፡- “ውሰብአ አቴናሰ ወእለ ይነግድ ኲሎሙ ህየ በእደ ትካዘ አልቦሙ ዘእንበለ ዳእሙ ለአፅምኦ ወነቢብ ዘሐዲስ”። አቴናውያን አዲስ ነገር ከመስማት ወይም ከመናገር በስተቀር ሌላ ምኞት አልነበራቸውም። ባለው ላይ ቆሞ አዲስ ነገር ለማግኘት የሚጣጣር ሰው ሁል ጊዜ ወደፊት ይሄዳል - ማለት ነው፡፡
እንደ አቴናውያን፤ በአለው ላይ ቆመን አዲስ ነገር ለማግኘት የምንጣጣር ከሆነ ወደፊት እንሄዳለን። ትምህርትንና ዕውቀትን መሰረቱ ያደረገ ትውልድ ከፈጠርን የራሱን ጥያቄ፣ የራሱን ነገ ራሱ ይወልዳል። የሚኖርበት ቤት ሲጠበው ቤቱን ራሱ አስፋፍቶ ይሰራዋል፡፡ ሁሉን እኛ እናድርግልህ ካልነው - ሁሉን ቀላቢ እንሁንለት ካልን፤ ዞሮ ዞሮ ተቀላቢ ትውልድ ነው የምናፈራው፡፡ ፈረንጆቹ እንደሚሉት - Spoon – Feeding mentality ይጠቀልለዋል - የአጉሩሱኝ አስተሳሰብ እንደማለት ነው፡፡
ለወጣቱ፤ የመንግሥቱ ለማን ግጥም “መርፌ - ትሰራለህን” ማንበብና በዚያ አቅጣጫ መጓዝ የአባት ነው፡፡ በየትኛውም አቅጣጫ! ወጣቱ በሥነ ምግባር ረገድ፣ የሰውን ፀባይና ችሎታ በሚመረምር መልኩ አዕምሮው መታነፅ አለበት፡፡ ዕውቀትን መሰረት ሳያደርግ ለትግል ብቻ ብናዘጋጀው፣ የፕሮፓጋንዳ ወይም የአጀንዳ ማስተላለፊያ አሸንዳ ቱቦ ነው የሚሆነው፡፡ ይህ በታሪክም የታየ ነው፡፡ በማህበራዊ ኑሮው የእያንዳንዱ መብትና ተግባር የሚጠበቅበት፣ “ሰው በንፁህ ተምኔቱ መሰረት በሰላም ተደስቶ የሚገኝበትን ሕግ” ይዞ መጓዝ እንዳለበት ሊረዳ ይገባል፡፡ ህይወት እንደ ጂኦሜትሪ ትምህርት በቀጥታ መሥመር የተሞላና የተለካ አይደለም፡፡ ቀላል ሂሳብም አይደለም። እንዴት እንደሚገነባ፣ ከራሱ ህይወት ተነስቶ እንዴት ለማደግ እንደሚችል፣ ትምህርትን ባሰላሰለ መልኩ ማጤን እንጂ “ሳይገሉ ጎፈሬ፣ ሳያረጋግጡ ወሬ” መሆን የለበትም፡፡ እስከ ዛሬ አጭር ተመልካች፣ አጭር ተጓዥ ሳናደርገው (Myopic) አልቀረንም፡፡ አጭር ግቦች አጭር ያደርጉናል!
አንድ ደራሲ እንደሚለው፤ “… የውጪ ጉዳዮችን ካገር ውስጥ ኃይሎች አሰላለፍ፣ ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ከጥበብ ሽግግርና ከውጪ ርዳታ፣ የቋንቋ መዘበራረቅና ጉራማይሌነትን ከባህላዊ ድቀት፣ የሐሳብ ነፃነትን ከጋዜጣ፣ ራዲዮና አጠቃላይ ውይይት ምህዳር መጥበብ ጋር…” የሚያነፃፅር ወጣትም ሆነ አዋቂ ያስፈልገናል፡፡
ወጣቱ አገሩን ያውቅ ዘንድ ጥልቅ አስተሳሰብ፣ ረዥም ርዕይና በግብረገብ የታነፀ ድፍረትና መስዋዕትነት ያስፈልገዋል፡፡ የሀገራዊነት፣ የወገን አሳቢነት፣ የኢ-ራስ - ወዳድነት፣ የሁሉን - አውድም አስተሳሰብ አለመያዝ፣ ሁሉን - ረጋሚ ያለመሆን አመለካከት፣ ኢ-ፅንፋዊነት ወዘተ እንደ መርህም፣ እንደ ኑሮም ሊሰርፁበት ይገባል፡፡ አለበለዚያ አፋሮች እንደሚሉት፤ “አገሩን የማያውቅ ሰው፣ መሬትን እየረገጠ መሬትን ይረግማል” ይሆናል፡፡