Administrator

Administrator

ካፒታሉን ወደ 1 ቢሊዮን ብር አሳድጓል

ብሬክስሩ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ባለፉት አራት ዓመታት ከ41 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሰብዕና ለውጥ ሥልጠና መስጠቱንና በስልጠናው በርካታ በኢኮኖሚ ራሳቸውን የለወጡ ዜጎች ማብቃቱን አስታወቀ፡፡ ድርጅቱ ይህንን የገለፀው ባለፈው ረቡዕ ጥር 15 ከሰዓት በኋላ በሸራተን አዲስ ሆቴል ላሊበላ አዳራሽ የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል  ባከበረበት ወቅት ነው፡፡ብሬክ ስሩ ትሬዲንግ በ2012 ዓ.ም “ቅን” (Genuine) በተሰኘ 17 ባለ ራእይ ሰዎች ጥምረት የተቋቋመ ሲሆን፣ አላማውም ባለ ራዕይ፣ ቅን፣ ጤናማና ባለፀጋ ትውልድን መፍጠር እንደሆነ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዱል ፈታህ ሁሴን ተናግረዋል፡፡ ድርጅቱ በአራት ዓመት ጉዞው ዜጎች በአዎንታዊ መልኩ ሰብዕናቸውን በመገንባት በኢኮኖሚ ያደጉና ሀገራቸውን የሚጠቅሙ እንዲሆኑ እየተጋ እንደሚገኙ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጨምረው ገልፀዋል፡፡ ብሬክስሩ በ2.4 ሚ ብር ካፒታል ተነስቶ በአራት ዓመታት ውስጥ ካፒታልን ወደ 1 ቢሊዮን ማሳደጉንና አሁንም አክሲዮን በመሸጥ ላይ መሆኑን የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ ከሰብዕና ግንባታ በተጨማሪም ወደ ተለያዩ ቢዝነሶች እየተሰማራ መሆኑንና በቅርቡ አንድ ት/ቤት መክፈቱን እንዲሁም “የኔ” የተሰኘ የሰብዕና ግንባታ ስልጠና ፕሮጀክት ማቅረቡንና በትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ እንደሚሰማራም ተናግረዋል፡፡
በብሬክስሩ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር አራተኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓል ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት፣ የድርጅቱ ከፍተኛ ሀላፊዎችና አባላትን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል፡፡

ይህ አልበም ቆየት ያሉ የሙዚቃ ስራዎች ድጋሚ የተሰሩበት እንደሆነ ባለፈው ቅዳሜ "የቅዳሜ ጨዋታ " ፕሮግራም ላይ መናገሩ ይታወሳል።
ሙዚቃቸው ድጋሚ ከተሰራላቸው አንጋፋ ድምፃዊያን መካከል ድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ ፣ ድምጻዊ እሳቱ ተሰማን ጨምሮ ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል።

"ህልም ነበረኝ፤ ሁለት አልበም በአንድ ቀን ማውጣት"

ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ፤ በአንድ ቀን "ሀራንቤ" እና "ኖር" የተሰኙ ሁለት አልበሞችን፣ "ዘጠኝ" በሚል አብይ ርዕስ ውስጥ ለአድማጮች እንደሚያደርስ ተጠቆመ፡፡

"ይህ አልበም ማሳረጊያ ፕሮጀክቴ ነው። በጣም ደክሜበታለሁ። ቴክኒካል ጉዳዮችን ጨምሮ ብዙ የተለፋበት ነው። የኔን እድገት የምታዩበት አልበም  ነው" ብሏል፤ድምጻዊው።

አክሎም ሲናገር፤ "ህልም ነበረኝ፤ ሁለት አልበም በአንድ ቀን ማውጣት" ብሏል፡፡

በ"ዘጠኝ" አብይ ርዕስ ውስጥ ያሉት ሁለቱ አልበሞች፣ በአጠቃላይ ሃያ አንድ ሙዚቃዎችን ይዘዋል ተብሏል።

በአልበሞቹ ላይ ሀይሌ ሩት፣ ሸዊት መዝገቡ፣ የልጅ ተመስገን ልጆችን ጨምሮ የሀገር ውስጥና የውጪ የሙዚቃ ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።

"ሀራንቤ" እና "ኖር" አልበሞች ከሦስት ሳምንት በኋላ ለሙዚቃ አድማጮች እንደሚደርሱ ታውቋል፡፡

አልበሞቹ በሮፍናን ዩቲዩብ ቻናልና በሁሉም የሙዚቃ ማሰራጫ መተግበሪያዎች በኩል ይለቀቃሉ።

ከአልበሙ ውስጥ ለሁለቱ Yሙዚቃ ቪዲዮዎች የተሰራ ሲሆን፤ ከአልበሙ የተወሰደ አንድ የሙዚቃ ቪዲዮ ዛሬ ማታ ለአድማጮች ይደርሳል ተብሏል።

Tuesday, 23 January 2024 20:11

ኢህአፓና ስፖርት part 6

https://youtu.be/k-llnz_sfro?si=Sr1-RWyz4-25MfPi

ይህ ሰው ሁሌም በመረጃ አሰባሰብ፣ በዝግጅት አቀራረቡና በሌሎች ነገሮቹ  ድንቅ ከሚሉኝ ሰዎች ውስጥ አንዱ ነው።
 ሁለገቡ ሰው ገነነ መኩሪያ( ሊብሮ)።
 ሊብሮ የምትለውን ስያሜ ያወጣለት በአብዛኛው የእግር ኳስ አፍቃሪ በአዝናኝነቱ፣ በእግር ኳስ ወዳድነቱ የሚታወቀው የኳስ ሜዳው ሰው ሀይሌ ካሴ ነው። በወቅቱ ጊዮርጊስ ከሜታ አቦ በተጫወቱበት ጊዜ አምስት ተጫዋቾችን አልፎ ግብ  ባስቆጠረበት ጊዜ ነበር የተቀፅላው መነሻ።
ሊብሮ የተወለደው ይርጋለም ከተማ ቢሆንም፣ እድገቱ ግን ሻሸመኔ ቀበሌ 09 ነው ።
በልጅነት ወቅትም እግርኳስ ይወድ የነበረው ገነነ፤ በጊዜው በየ15 ቀኑ አዲስ አበባ  የሚመጡት የሆቴላቸው  ሾፌር አብሮቸው ያቀና ነበር፤ በነበራቸው ቆይታም ካምቦሎጆ ገብተው እግር ኳስ ተመልክተው ይመጡ  ነበር፤ በዚያ  በአፍላነት ጊዜው መሆኑ ነው።
ሌላው የሚገርመው ገኔ ሻሸመኔ ውስጥ ላለ ቡድን  ለAም፣ ለBም፣ ለCም ይጫወት ነበር፤ በአንድ ቀን ውስጥ።
የቀበሌ 09 ቡድንም በወቅቱ የአቶ ሙኩሪያ ቀበሌ ቡድን ይባል ነበር። በጊዜው እሱን ጨምሮ ስድስት ወንድሞቹ እዛ ቡድኑ ውስጥ ይጫወቱ  ነበሩ። እንደዚህ እያለ ነው ወደ እግር ኳስ ተጫዋችነት ያመራው።  ወደ ክለብ ደረጃም መጀመሪያ የመጣው በ1975 ዓ.ም አካባቢ፣ የትምህርት ቤት ውደድሮች ላይ በመታየት ከእነ ታሪኩ መንጀታ፣ አስቻለው ጋር በመሆን ነበር፤ ወደ ሜታ ቢራ የተቀላቀለው።
እዚህ ጋ  በወቅቱ በአጨዋወትና በሌሎች ተዛማጅ ነገሮች  ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ከአሰልጣኞች ጋር ሙግት ይገጥም ነበር። በጊዜው ሜታን ያሰለጥን ከነበረው ስዩም ጋር ይጋጩ እንደነበር ይጠቀሳል። በእግር ኳስ ተጫዋችነቱ ወቅት እረፍት ሰአቱን በማንበብ ማሰለፍ ይወድ እንደነበር አብረውት የተጫወቱት ይመሰክራሉ።
የሊብሮ ጋዜጣው መነሻ
ከዛ በፊት በበጎ ፍቃደኝነት በተለያየ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ይሰራ ነበር። ከሰራባቸው የህትመት ሚዲያ ውስጥም መረሀ ስፖርት፣ የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ውስጥ ይጠቀሳል።
በመቀጠል ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ማለትም አበበ ወልደ ፃዲቅ፣ ሁሴን አብድልቀኒ ጋር በመሆን ሻምፕዮን የምትባል የስፖርት ጋዜጣ መስርተው ሰርተዋል።
በማስከተልም የራሱ የሆነችውን ሊብሮ ጋዜጣ አቋቋመ።  የዚህች ጋዜጣ አመሰራረት የሚገርም ነው፤ በተለይ በወቅቱ የነበሩቱ የቦሌ ማተሚያ ስራ አስኪያጂ አሰፋ ከበደ ሊመሰገኑበት የሚገባ ድርጊት ነው። በጊዜው ገነነ የሚያሳትምበት ገንዘብ እጥረት ያጋጥመዋል፤ ሁሉን ነገር ጨርሶ ከሰራ በኋላ ግን እጁን አጣጥፎ ከሰማይ መና አልጠበቀም፤ ወደ ቦሌ ማተሚያ ቤት  ሄዶ ስራ አስኪያጁን ያለበትን ነገር ሁሉ አስረድቶ  በእሳቸው ቀና ትብብር አማካኝነት ጋዜጣዋ ለመጀመሪያ ጊዜ  ለህትመት በቃች። በጊዜውም በጣም ተወዳጅ ጋዜጣ እንደነበረች በጊዜው የነበሩ ሰዎች ያስታውሳሉ፡፡ አብዛኛውን ትኩረት የምታደርገው የሀገር ውስጥ ዜናዎች ላይ ነበር። ለነገሩ አብዛኛዎቹ የዚያን ዘመን ጋዜጦች ትኩረታቸው የሀገር ውስጥ እንደነበር መመልከት ይቻላል።
በህትመት ግን ለ13 አመታት ከብዙ ችግሮች ጋር እየተጋፈጠች ለህዝብ ተደራሽ መሆን ችላ ነበር ። አብዛኛውን ስራ እራሱ  ገነነ ነበር የሚሰራው። የጋዜጣ ስራ ምን ያህል አድካሚ እንደሆነ  የሚያውቀው ያውቀዋል።
ነገር ግን ጋዜጣዋ ከተቋረጠች በኋላ ለአጭር ጊዜ በድረ ገፁ በኩል ጀምሮት ነበር። ቢሆንም ግን  ሊዘልቅ አልቻለም።  ሁሉን ነገር ገታ አድርጎ  በመተው  በመፅሐፍና ሌሎች ተዛማጅ መስኮች ላይ በመስራት በተከታታይ በእግር ኳስ ዙሪያና ፖለቲካ ላይ የሚያጠነጥኑ መፅሀፎችን አበረከተለን፡፡  ለመጥቀስ ያህል፡-
*የአሸናፊ ግርማ የህይወት ታሪክ፤ ከአሸዋ ሜዳ እስከ አርጀንቲና
*የእግር ኳስ ወጎች
*ኢህአፓና ስፖርት 1 እና 2 እዚህ ጋ በቅርብ ለእይታ የቀረበው የነገን አልወልድም የታሪኩ መነሻ ከ ኢህአፓና ስፖርት 1 የተወሰደ ነው)
እና ሌሎች በህትመት ደረጃ ያልወጡ በሙዚቃና በሌሎች ጉዳዮች ያተኮሩ መፅሐፍት ሲያሰናዳ ነበር፡፡
ሌላው በ90ዎቹ አጋማሽ ላይ በስፋት ይወራ ስለነበረው የኢትዮጵያዊ ስልጠና ሀሳብ አመንጪ ሰው ነው፡፡ በተለምዶ  Gk የሚባለውን  የስልጠና ፍልስፍና በኋላ በካሳዬ አራጌ  ዳብሮ ለአጭር ጊዜ የተሞከረው፡፡ በነገራችን ላይ በዚህ ዙሪያ ላይ በ1994 ዓ.ም ኢትዮጵያ ስልጠና መፅሀፍ ማውጣቱ አይዘነጋም። እስከ ጠቅላይ ሚኒስትር ደረጃ ደብዳቤ ፅፏል በስልጠናው ዙሪያ ላይ።
*****
ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ ) ባደረበት ህመም ህክምና ሲከታተል ቆይቶ ማረፉ ተሰምቷል፡፡ የአዲስ አድማስ ዝግጅት ክፍል፣ በታላቁ የስፖርት ሰው ገነነ መኩሪያ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ፤ ለቤተሰቦቹ ወዳጆቹና አድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡ ፈጣሪ ነፍሱን በአጸደ ገነት ያኑርለት፡፡

 

 

ጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ገነነ መኩሪያ ባደረበት ህመም ምክንያት በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ሕይወቱ ዛሬ ንጋት ላይ ማለፉን ቤተሰቦቹ አስታውቀዋል፡፡

በአዲስ አበባ "ንባብ እና አገር" የተሰኘ የንባብ ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው

የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ "ንባብና አገር" የተሰኘ የንባብ ፌስቲቫል ከጥር 16 እስከ 23ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
የባህልና ቱሪዝም ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ አስፋው ኩማ እንዳሉት፤ የንባብ ፌስቲቫሉ ዓላማ የከተማው ማህበረሰብን የንባብ ባህል ለማሻሻልና ግንዛቤ ለመስጠት ነው።
ባለፉት ሶስት ዓመታት የተለያዩ በራሪ ጽሁፎች በማዘጋጀት የስርፀት ሥራ ሲሠራ መቆየቱን የገለፁት ሃላፊው፤ በዚሁ ዝግጅት በህትመት ታሪክ ውስጥ በርካታ አስተዋፅኦ ያደረጉ ድርጅቶችና ደራሲያን ታሪካቸው ይወሳል ብለዋል።
የንባብ ፌስቲቫሉ ለ8ኛ ጊዜ የተዘጋጀ ሲሆን ዝግጅቱ በአዲስ አበባ ሙዚየም ይደረጋል።

የአንጋፋው ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈፀመ

ጋዜጠኛ አስፋው መሸሻ ባደረበት ህመም በአሜሪካ ሕክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ባለፈው ሳምንት ሕይወቱ ማለፉ ይታወቃል፡፡

በሚሊኒየም አዳራሽም የስንብት መርሐግብር ከተካሄደ በኋላ በመንበረ ጸባኦት ቅ/ሥላሴ ካቴድራል ቤተሰቦቹ፣ የሙያ አድናቂዎቹ፣ የስራ ባልደረቦቹ በተገኙበት የፍትሃት እና የቀብር ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡

የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል፣ በአንጋፋው የሬዲዮና ቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ አስፋው መሸሻ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለፀ፤ ለቤተሰቦቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹና ለወዳጆቹ ሁሉ መጽናናትን ይመኛል። ፈጣሪ ነፍሱን በአፀደ ገነት ያኑርለት።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

“ጎተ የአጭር ልቦለድ ቡፌ ነው ያቀረበልን“


መስዑድ ጀማል እባላለሁ፡፡ በ“ሠላሳዎቹ“ መድበል ውስጥ “ወሎ ሎጂ“ የተሰኘ ሥራዬ ታትሞልኛል፡፡ በሙያዬ በአማራ ሚዲያ ኮሙኒኬሽን (አሚኮ) ጋዜጠኛ ነኝ፡፡
ድርሰትህ በ“ሠላሳዎቹ“ የአጫጭር ልብወለዶች መድበል ውስጥ በመካተቱ ምን ዓይነት ስሜት ፈጠረብህ? ከዚህ በፊት ተመሳሳይ ዕድል ገጥሞህ ያውቃል? የራስህን መጽሃፍስ አሳትመሃል?
ልዩ ደስታ ነው የሚሰማህ። እስከዛሬ ትደሰተው ከነበረው ደስታ ከፍ ያለ።ትንሽ ኩራትም ቀልቀል ያለበት። ቀደም ሲል በመፅሐፍ መልክ የወጣ ሥራ የለኝም። በሌላ የጥበብ ቅርፅ ግን አለ። ከዚህ በፊት ደራሲ ሜሪ ፈለቀ  የአጭር ፊልም ወድድር አወዳድራ ነበር። ‘ሀቅ’ በሚል አጭር ፊልም ተወዳድሬ 1ኛ በመውጣት 50,000 ብር አሸንፌያለሁ። ያው ስለሚያያዝ  ብዬ ነው። በመፅሐፍ ግን ይህ የመጀመሪያዬ ነው።
የአጫጭር ልብወለዶች ስብስቡን   እንዴት አገኘኸው?
 በጎተ ፅሁፌ ከተመረጠ በኋላ መፅሐፉ ከመታተሙ በላይ በጉጉት ስጠብቀው የነበረው መፅሐፉ ወጥቶ 29 ታሪኮችን እስካነብ ነበር። መፅሐፉ ወጥቶ 29ኙን ታሪኮች ካነበብኩ በኋላም መጓጓቴ ልክ እንደነበረ ነው የገባኝ። ጎተ የአጭር ልቦለድ ቡፌ ነው ያቀረበልን። የተለያየ መልክ፣ መዓዛና ጣዕም ያላቸው አጫጭር ልቦለዶችን ነበር ያገኘሁት።  የመጣንበት አካባቢያዊ ዳራ ደግሞ ድርሰቶቹ በመቼት እንዳይገደቡ አድርጓቸዋል። ኢትዮጵያን በሁሉም መአዘን ትቃኛታለህ። ወደ ወሎ፣ ትግራይ፣ አርባምንጭ፣ ጅማ... የማትሄድበት ሀገር፤ሄደህም የምታጣው ነገር የለም። ራሳቸው ወደቆረቆሩት የምናብ ሀገር የሚወስዱህም አሉ። “ሠላሳዎቹ“ መፅሐፍ በህብረ ቀለማት ያጌጠ እንደምንለው፣ “በህብረ ታሪኮች” ያሸበረቀ መፅሐፍ ነው ማለት እንችላለን። በቋንቋ አጠቃቀም፣በአተራረክ፣በጭብጥ፣በገፀ ባህሪ አሳሳል፣በትልም አጎናጎን፣በአተያይ፣በአፃፃፍ ፍልስፍና ሁሉም የራሱን ቦይ እየቀደደ እንድትፈስ ያደርግሀል። ከአንዱ ታሪክ ወደ ሌላው ታሪክ ስትሄድ በጉጉት ነው፤ “ይሄኛው ደሞ ስለምን ይሆን?” እያልክ ነው። በሁሉም ድርሰቶች የምትደመምበት አንዳች ነገር አታጣም።
የወጣት ጸሃፍት ሥራዎች እንዲህ ተሰባስበው በጋራ መታተማቸው ምን ፋይዳ አለው ብለህ ታስባለህ?
አብዛኛው የመፅሐፉ ደራሲ “ማነህ?” በሚል ጥያቄ  በጥበብ ሸንጎ ቆሞ ነፃ ለመውጣት እየተሰቃየ ባለበት ሰዓት ጎተ  ደርሶ “እሱ እከሌ ነው...ደራሲ ነው” ብሎ ምስክር ሆኖ፣ ነፃነትና ማንነት እንደሰጠን አምናለሁ።
ወጣት እንደመሆናችን ብዙ ጥርጣሬዎችና ፍርሀቶች ወስጣችን ይኖራሉ። መመረጣችን፣ ከምናከብራቸው ደራሲዎች ጋር መገናኘታችን ማውራታችንና “ሠላሳዎቹ” መፅሐፍ መታተሙ እነኚህን ፍርሀቶቻችንና ጥርጣሬዎቻችንን እንድንጋፈጥና እንድናሸንፋቸው አድርጎናል። ሌላኛው ጉዳይ ደግሞ በብዙዎች አልቀመስ ያለውን የመፅሐፍ ህትመት ዋጋ መናርን አልፈን እንድንነበብ ሆነናል። ብዙዎች ይህንን ዕድል አላገኙም። ከዚያ ባለፈ ስራዎቻችን በጋራ መታተማቸው “Gothe 2022 winners” የሚል ቤተሰብ እንዲመሰረት እድል ከፍቷል። አዳዲስ ደራሲዎች ከዚህ በፊት የህትመት ብርሀን ካገኙ ደራሲያን ጋር እንድንተዋወቅና እንድንማማር አድርጓል። ፅሁፎችን መላላክና  አስተያየት እንድንለዋወጥ፣ ቀጣይ ሌሎች ስራዎችን  በጋራ ለመስራት እንድናቅድ አድርጓል።
በጀርመን የባህል ማዕከል ድጋፍ ከተሰጣችሁ አጭር ሥልጠና ምን አዲስ ትምህርት ቀሰምክ?
ስልጠናው ጥሩ ነበር...theory አልነበረም፤ በስልጠናው። የራሳችንን ፅሁፍ እየመዘዙ በጠንካራና በደካማ ጎኖቻችን ነበር ስንሰለጥን የነበረው። ከስልጠናው ስለ ፊደላትና ቃላት አጠቃቀም ብዙ የተማርኩት ነገር አለ። በዘመን ሂደት የተቀየሩ ቋንቋዎች አሉ። “አደረግኩ” ብለን እንፅፋለን፤ “አደረግሁ” ማለት ሲገባን።”ፀሀይ” ነው፣ “ጸሀይ” ብለን መፃፍ ያለብን? ብዙዎቻችን በዚህ ክፍተት ነበረብን። ነገር ግን በስልጠናውም ፤በአርታኢያችን ቴዎድሮስ አጥላው እገዛም የለወጥነው ነገር አለ።
ከአገራችን ወይም ከውጭ አገራት  የአጭር ልብወለድ ጸሃፍት ማንን ታደንቃለህ?
ብዙ የማደንቃቸው የአጭር ልቦለድ ደራስያን አሉ፤ሌሊሳ ግርማ፣አሌክስ አብርሀም...እና አዳም ረታን እመርጣለሁ፡፡ የግድ አንድ ከተባለ አዳም ረታ ምርጫዬ ነው፡፡ አንድን የጥበብ ሰው ስመዝን አይምሮ ውስጥ ተሰንቅረው በሚቀሩ፣ ለትውስታ ቅርብ በሆኑ ስራዎቹ የመመዘን አባዜ አለብኝ። የአዳም ረታ የ”ሎሚ ሽታ” አይምሮዬ ውስጥ የቀረ ታሪክ ነው።ከገፀ ባህሪያቱ እስከ አተራረክ ቴክኒኩ አይምሮዬ ውስጥ አለ። ከውጭ ኦ ኸነሪን  እመርጣለሁ። ያው ቅድም እንዳልኩት ነው። “The last leaf” እያደር የሚደንቀኝ ታሪክ ነው።



ባለፈው ሳምንት የ“ሠላሳዎቹ“ የአጫጭር ልብወለዶች መድበል የሃሳብ ጠንሳሽና የፕሮጀክቱ መሪ እንዲሁም በጀርመን ባህል ማዕከል የቤተ መፃህፍትና የመረጃ ሃላፊ የሆነውን ዮናስ ታረቀኝ በመጽሐፉ ዝግጅቱ ዙሪያ ማነጋገራችን ይታወሳል፡፡ ዛሬ ደግሞ በዚሁ ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ ድርሰቶቻቸው በመድበሉ የተካተተላቸው ሦስት ወጣት ጸሃፍትን አነጋግረን፣ ሃሳባቸውን እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡  




”ለአንባቢያን ምርጫን ያሰፋል ብዬ አምናለሁ“

Page 12 of 696