Administrator
“ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” ሊካሄድ ነው
ዋልያ መጻሕፍት “ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” በሚል ርዕስ ከዘርፉ ምሁራን ጋር የሚደረግ አጓጊ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። በዕለቱ ታዋቂው ኢምሬተስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ “ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” በሚለው ርዕስ ላይ ጥልቅ ማብራሪያ የሚሰጡ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና በናሳ ተመራማሪና የዶክትሬት ተማሪ የሆነው አቶ ተስፋዬ ማሞ መኮንን ደግሞ “ፊዚክስ በዕለት ተዕለት ሕይወታችን” በሚል ርዕስ ዙሪያ የዕውቀት ልውውጥ ያደርጋሉ።
ይህ ታላቅ የዕውቀት ማዕድ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሰዓት ከ8፡00 ጀምሮ በ4 ኪሎ ኢክላስ ሕንጻ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት አዳራሽ ይካሄዳል። ሁለቱን ታዋቂ ምሁራን በአንድ መድረክ በማግኘት አዳዲስ ሃሳቦችን ለመረዳት እና ከእለት ተእለት ሕይወት ጋር ለማገናኘት ይህንን ዕድል ይጠቀሙበት።
"ጦቢያ" በአውሮፓ ከተሞች ሥራዎቹን ሊያቀርብ ነው
በነፃ ሀሳብና በሰከነ መንፈስ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን በማድመቅ ላለፉት 14 ዓመታት የብዙዎችን ፍቅር ያተረፈው የ"ጦቢያ" መድረክ፣ በጀርመን መቀመጫውን ባደረገው "Hope for All" ግብረ ሰናይ ድርጅት አዘጋጅነት በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች አጓጊ ዝግጅቶቹን ሊያቀርብ ነው።
በገጣሚ ምስራቅ ተረፈ መስራችነት የሚመራው ይህ መድረክ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ኦገስት 9 በአምስተርዳም፣ ኦገስት 16 በኑረንበርግ፣ ኦገስት 23 ፍራንክፈርት፣ ኦገስት 30 ኮለን እንዲሁም ሴፕቴምበር 5 በሙኒክ ከተሞች ለታዳሚዎች ይደርሳል።
ይህ የኪነጥበብ ጉብኝት ከእጅግ ውብ መዝናኛ ባለፈ በትውልድ ሀገራቸው ለሚገኙ ወጣት ሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ትልቅ የበጎ አድራጎት ዓላማ ሰንቋል። አዘጋጆቹ በአውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና የዝግጅቱ ታዳሚዎች እየተዝናኑ ለተቸገሩ ወገኖቻቸው እንዲደርሱ በህብረት እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
"ጥቃቱን ፈጽሞ በመንግሥት ላይ ማሳበብ"፦ በትግራይ የታቀደው የሐሰት ጥቃት ሴራ
ሪያል ማድሪድ ያን ዶዮማንዴን ለማስፈረም ከስምምነት ደረሰ
በኃይለኛ ንፋስና ዝናብ የፈራረሱት የተፈናቃዮች መጠለያዎች በትግራይ
መከላከያ ሠራዊት ለመቄዶንያ ከ600 ሺህ ብር በላይ ድጋፍ አደረገ
ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለወጣቶች ጥሪ አቀረቡ
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የኤር ኢንዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
የባርነትን ሰቆቃ የሚዘክሩት አስገራሚ ሀውልቶች!
21ኛው የዓለም ከ20 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀምራል
21ኛው የዓለም ከ20 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው ዕለት በአሜሪካ ኦሪገን መካሄድ ይጀምራል፡፡
በሻምፒዮናው በ46 የውድድር ዘርፎች ከ147 ሀገራት የተወጣጡ 1 ሺህ 800 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ተመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በ5 ሺህ ሜትር፣ 3ሺህ ሜትር፣ 1 ሺህ 500 ሜትር እና በ800 ሜትር በሁለቱም ፆታዎች ትሳተፋለች፡፡
በተጨማሪም በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል እና በ400 ሜትር በሴቶች እንዲሁም በርምጃ ውድድር ደግሞ በሁለቱም ፆታዎች የምትሳተፍ ይሆናል፡፡
ዛሬ በመክፈቻው ዕለት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የፍጻሜ እና የማጣሪያ ውድድራቸውን ያደርጋሉ።
ምሽት 4 ከ 43 ላይ በ800 ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ነጋሄ እያሱ እና የሮሳን ግርማ ሲካፈሉ፤ በሴቶች ደግሞ በዚሁ ርቀት ምሽት 5 ከ 35 ሐብታም ገበየሁ እና ደራርቱ ሽብሩ ማጣሪያቸውን ያከናውናሉ።
ሌሊት 11 ከ 53 በሴቶች 5 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር እመቤት ጥላሁን እና አልማዝ ዮሃንስ የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ለማሸነፍ ብርቱ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡
ማለዳ 12 ከ 20 በወንዶች 5 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር ደግሞ ማማሩ ጎዴ እና ዳምጠው ከበደ የሚሳተፉ ይሆናል፡፡
ሻምፒዮናው በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 ቀን እስከ ነሀሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።

