Administrator

Administrator

Saturday, 29 July 2017 11:30

የአዲስ አድማስ ማሳሰቢያ

    ያለወትሮአችን ማሳሰቢያ ለመፃፍ የተገደድነው አንዲት ስማችን የተጠቀሰባት ሃሰተኛ (‹ፎርጂድ› የበለጠ ይገልፀዋል) ደብዳቤ ሰሞኑን ዝግጅት ክፍላችን በመድረሷ ነው፡፡ ደብዳቤዋ የታለመችው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ ነው፡፡ ‹‹ስፖንሰር አድርጉን›› ትላለች፡፡ መታለም ብቻ ሳይሆን ለፋብሪካውም ደርሳለች፡፡ ‹‹አፍሪካ ፖስት ሚዲያ ሴንተር›› በሚል ማህተም የተከተበችው ይህች ‹‹ጉደኛ›› ደብዳቤ፤ በአጭሩ ‹‹አዲስ አድማስ ጋዜጣ የተመሰረተበትን 15ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ሐምሌ 7 ቀን 2009 ዓ.ም ከአፍሪካ ፖስት ሚዲያ ሴንተር ጋር በመተባበር፣ በአዲስ አበባ ቲያትርና ባህል አዳራሽ በታላቅ ድምቀት ይከበራል›› በሚል መግቢያ ትጀምራለች፡፡ (ልብ በሉ! ‹‹አዲስ አድማስ›› 15ኛ ዓመቱን የዛሬ ሁለት ዓመት በብሔራዊ ቴአትር ‹‹በታላቅ ድምቀት›› አክብሯል፡፡
የሆነው ሆኖ፣ የ15ኛ ዓመት በዓላችንን እንዳከበርን ያላወቁት ወይም ያልሰሙት እነዚህ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቀ ‹‹ ቁጭ በሉዎች››፤ (‹‹ሿሿ›› ነው የሚሏቸው?!) ዝግጅቱን በርካታ ድርጅቶች ስፖንሰር እንዳደረጉ ይጠቅሱና፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራም በዓይነትም በገንዘብም ስፖንሰር እንዲያደርጋቸው ይጠይቃሉ፡፡ (የአዲስ አድማስን 15ኛ ዓመት በዓል ማለት ነው፡፡) በርግጥ የቢራውም ሆነ የገንዘቡ መጠን አልተጠቀሰም በዚህ ቢያበቃ ጥሩ ነበር፡፡ ቢራ ፋብሪካው ስፖንሰር ሲያደርግ የሚያገኘውን ጥቅማ ጥቅም ይገልፃሉ- ‹‹ድርጅታችሁን በሚታተመው ተከታታይ ሳምታዊ የጋዜጣ ዕትም ላይ በብዙ ብር ከፍለው ስፖንሰር ካደረጉን ድርጅቶች እኩል የምናስተዋውቅ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን” በማለት፡፡
በነገራችሁ ላይ በዚህ የጋዜጣችንን ስም ለማጭበርበርያነት ጠቅሰው በፃፉት ደብዳቤ ላይ እውነተኛ ወይም ትክክለኛ የሚመስል ነገር አለ ከተባለ፣ ፅሁፉ የሰፈረበት ነጭ ወረቀት ብቻ ነው፡፡ በደብዳቤው ላይ የሰፈሩት ሁለት ስልክ ቁጥሮች ጨርሶ አይሰሩም። ‹‹አፍሪካ ፖስት ሚዲያ ሴንተር›› የሚባል ድርጅት በተጨባጭ መኖሩን ለማረጋገጥም አልቻልንም (ሊኖር እንደማይችል ገምቱ!)፡፡
በመጨረሻም፤ ለውድ የአዲስ አድማስ ቤተሰቦች፣ አንባቢያን፣ ድርጅቶች፣ የመንግስት ተቋማትና ሌሎችም ልንገልፅ የምንወደው፣ የአዲስ አድማስ ህጋዊ ማህተም፣ ሎጎ፣ በቂ አድራሻዎች … ወዘተ በቅጡ ሳትመለከቱ (ሳታጣሩ) ለደብዳቤዎች ጥያቄ ምላሽ እንዳትሰጡ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኞችም ሆኑ ተወካዮች የድርጅቱ መታወቂያ እንዳላቸው እግረመንገዳችንን ልንገልፅ እንወዳለን፡፡ ራሳችንን እንጠብቅ!!

    በአውሮፓና በአሜሪካ ከ120 በላይ ስኬታማ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በማቅረብ የሚታወቀው የሬጌው አቀንቃኝ ኦጄኬን ኦሊቨር ወይም በመድረክ ስሙ “ፕሮቶጄ” ዛሬ ምሽት በላፍቶ ሞል ያቀነቅናል። “The Indignation” ተብሎ በሚጠራውና በሰባት ታዋቂ የሙዚቃ ተጫዋች የተደራጀው ሙሉ ባንዱ ታጅቦ የሚያቀነቅነው  የ33 ዓመ ከታወጀ 10 ወር ገደማ ያስቆጠረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከ5 ቀን በኋላ ይነሳ ይቀጥል የሚታወቅ ሲሆን  ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ፤የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተነሳ፣ ሐምሌ 30 እና ነሐሴ 7 ቀን 2009 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ህዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት ማቀዱን አስታውቋል፡፡
ፓርቲው ሰሞኑን ባወጣው ወቅታዊ የአቋም መግለጫው፤አስር ወራትን ያስቆጠረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የማብቂያው ጊዜ ከ5 ቀን በኋላ፣ መሆኑን በመጠቆም፣ አዋጁ ለተጨማሪ ጊዜያት እንዳይራዘም መንግስትን ጠይቋል፡፡ አዋጁ ተጥሎ በቆየባቸው ጊዜያት፤ “የዜጎችን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች የጣሰ፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ያጠበበ፣ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንዲያሽቆለቁል ያደረገና የህዝብን ማህበራዊ መስተጋብሮች የገታ ነበር” ያለው ሰማያዊ፤ “መንግስት ሀገሪቱን አረጋግቻለሁ ስላለ አዋጁን ማራዘም አያስፈልግም፤ ሊነሳ ይገባዋል” ብሏል፡፡ በቅርቡ በሚኒስትሮች ም/ቤት ተወስኖ፣ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የቀረበው የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ያለው ልዩ ጥቅም ረቂቅ አዋጅ፣ የአዲስ አበባና የኦሮሚያ ህዝብ ሳይመክርበት መውጣቱን ፓርቲው ተችቷል፡፡ የግብር አጣጣል ስርዓቱም የዜጎችን ገቢ ያገናዘበ እንዲሆን የጠየቀው ፓርቲው፤ በአጠቃላይ ህዝቡ በአግባቡ ሳይመክርባቸው እየወጡ ያሉ አዋጆች፣ በዜጎች ላይ መደናገጥ እየፈጠሩ በመሆኑ ሊታረሙ  ይገባል ሲል አሳስቧል።
“ሰማያዊ” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊነሳ ይችላል በሚል መተማመን፣ ሐምሌ 30፣ ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ ቀኑ 9 ሰዓት ሜክሲኮ አደባባይ በሚገኘው የመብራት ሃይል አዳራሽ፣ ህዝባዊ ስብሰባ እንዲሁም ነሐሴ 7፣ መነሻውን ሚኒልክ አደባባይ፣መዳረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገ፣ ሰላማዊ ሠልፍ ለመጥራት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ የስብሰባውም ሆነ የሰልፉ አጀንዳዎች፣ በዋናነት እየወጡ ባሉ አዋጆች ላይ እንደሚያተኩር ለአዲስ አድማስ ያስረዱት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አበበ አካሉ፤ሰልፉም ሆነ ስብሰባው የታቀደው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሊነሣ ይችላል በሚል ግምት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ቱ ፕሮቶጄ፤ ትላንት ከቀኑ 8፡00 ላይ በአምባሳደር ሆቴል ከኮንሰርቱ አዘጋጅ EML ኤቨንት ኦርጋናይዘርስ ጋር በጋራ በሰጠው መግለጫ፤ የዛሬው የላፍቶ ሞል ኮንሰርቱ በአፍሪካ የመጀመሪያው እንደሆነ ገልጿል፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣቱ በፊት ጣሊያን፣ ስዊድን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይና ስፔይን ትልልቅ ኮንሰርቶችን እንዳቀረበና እዚህ ያለውን ስራ ሲጨርስም ወደ አውሮፓ ተመልሶ ስራውን እንደሚያቀርብ ተናግሯል፡፡
ዘፋኝ ባይሆን ኖሮ ሯጭ ይሆን እንደነበር በመግለጫው የጠቆመው ዘፋኙ፤ አትሌት ሃይሌ ገ/ሥላሴን ጨምሮ ብዙ የኢትዮጵያ አትሌቶችን በስም ጭምር እንደሚያውቅ የተናገረ ሲሆን “አትሌት ጥሩነሽ ዲባባን ከልቤ አደንቃለሁ” ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ሰሞኑን ለራስ ተፈሪያን የትውልደ ኢትዮጵያዊነት መብትና ዕውቅና መስጠቱን በተመለከተ የተጠየቀው ዘፋኙ፡-
“በጣም ትልቅና ታላቅ እድል ነው፡፡ እኛ ወደ ኢትዮጵያ መጥተን መኖር የምንፈልገው ለአገሪቷ ሸክም ለመሆን አይደለም፡፡ አላማ አለን፤ ራዕይ አለን፡፡ ጓዛችንን ጠቅልለን ስንመጣ ከእውቀት፣ ከሰፊ ልምድና ሙያ ጋር ነው፡፡ ኢትዮጵያ መጥተን ልንዝናና ወይም ሳንሰራ ተቀምጠን ለመኖር አይደለም፡፡ ማንም ራስ ተፈሪያን ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ሲያስብ፣ የራሱን ሀሳብ ይዞ ነው፡፡ ያንን ሀሳብ የሚፈፅመውም ኢትዮጵያን ለመጥቀም ነው” ሲል መልሷል፡፡ከዚህ በፊት ይከሰት የነበረውን ትርምስና ጭንቅንቅ ለማስቀረት ሲባል ተጨማሪ ባሮች በላፍቶ ሞል መዘጋጀታቸውን የጠቆሙት አቶ ኢዩኤል፤ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ተመልካቾች ወደ አዳራሹ መግባት ይጀምራሉ ብለዋል፡፡ ኮንሰርቱ ቀድመው ትኬት ለገዙ 300 ብር፣ በዕለቱ ለሚገዙ በመደበኛው 500 ብር፣ በቪአይፒ 700 ብር የመግቢያ ዋጋ ተተምኖለታል፡፡


  ሜላት ተመስገን፣ የ15 ዓመት ታዳጊ ስትሆን የአንደኛ ደረጃ መልቀቂያ (8ኛ ክፍል) ፈተና ወስዳ አጥጋቢ ውጤት በማምጣት (85.5 በመቶ) ወደ 9ኛ ክፍል ተዛውራለች፡፡ ሜላት፣ ከአያቷ ጋር ነው የምትኖረው፡፡ አያቷ ደግሞ ሁለቱን ማኖር የሚያስችል ገቢ የላቸውም፡፡ በየሰው ቤቱ ልብስ እያጠቡ በሚያገኙት አነስተኛ ገቢ ነው የሚተዳደሩት፡፡ ይህ የአያቷ አቅመ ደካማነትና የገቢ ማነስ ነው በብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ድጋፍ እንዲደረግላት ያስመረጣት፡፡
ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ፤ ለሜላትና ለሌሎች የተመረጡ ተማሪዎች ምን ዓይነት ድጋፍ እያደረገ ይሆን? ሜላት እንዲህ ትገልጻለች፡- “ድርጅቱ አሪፍ ድጋፍ እያደረገልን ነው፡፡ ለምንማርበት እውቀት በኅብረት  ት/ቤት የዓመት  ይከፍልልናል። ለመማር አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁስ፣ ዩኒፎርም፣ ደብተር፣ መጻሕፍት፣ ቦርሳ፣ ልብስ ይሰጠናል። በትምህርታችን ጎብዘን፣ ውጤታማ ሆነን የተሻለ ደረጃ ላይ እንድንደርስ ከፍተኛ ድጋፍ ያደርግልናል፡፡ ድሮ የነበረንን የአጠናን ዘዴ ቀይረን፣ አዲስና ውጤታማ የጥናት ዘዴ እቅድ እንድናወጣ ረድተውናል፡፡ በዚህም ዘዴ ተሳክቶልኛል፡፡ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስጄ 85.5 በመቶ ነው ያመጣሁት” ብላለች።
ሲሳይ ኃይለየሱስ የ14 ዓመት ታዳጊ ሲሆን፣ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዶ ውጤት ስላልመጣለት ደጋሚ ነው፡፡ ሲሳይ እናቱ በህይወት ስለሌሉ የሚኖረው ከአባቱ ጋር ነው፡፡ አሁን እንኳ አነስተኛ ግሮሰሪ ስለከፈቱ ትንሽ ይሻላል እንጂ ከ3 ዓመት በፊት እሱ በብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ድጋፍ እንዲደረግለት ሲመረጥ የአባቱ ገቢ የሚያወላዳ አልነበረም። ዘነበወርቅ ሪፈራል ሆስፒታል (አለርት) ውስጥ ካርድ ጠሪ ስለሆኑ ገቢያቸው በጣም አነስተኛ ነበር፡፡ ሲሳይ፤ ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ስለሚያደርግላቸው ድጋፍ ሲናገር፤ ሜላት ያለቻቸውን አገልግሎቶች ጠቅሶ፤ “በየቀኑ ምሳና ራታችንን ያበላናል፡፡ 9፡30 ከት/ቤት ወጥተን ወደ ግቢ ነው የምንሄደው፡፡ እዚያ በጎ ፈቃደኞች ስላሉ ያስጠኑናል፡፡ በክረምት ደግሞ አስጠኚ መምህራን ይቀጥሩልናል፡፡ ንጽህናችንን እንድንጠብቅ በየሳምንቱ የተለያዩ ሳሙናዎች ይሰጡናል፡፡ ልብሳችንን እናጥባለን፤ ገላና ፀጉራችን እንታጠባለን፡፡ ሴት ተማሪዎች ፀጉራቸውን ተጣጥበው እርስ በርስ ይሰራራሉ” በማለት ገልጿል።
ሃዳስ ዘሩ አባቷን በሞት ስለተነጠቀች ከእናቷ ጋር ነው የምትኖረው፡፡ ወደፊት ሐኪም  የመሆን ህልም እንዳላት የጠቀሰችው ሃዳስ፣ የ16 ዓመት ታዳጊ ስትሆን  በ1ኛ ሴሚስተር 2ኛ፣ በ2ኛ ሴሚስተር ደግሞ 3ኛ ደረጃ አግኝታ በአማካይ ውጤት 86 በማምጣት፣ ወደ 10ኛ ክፍል ተዛውራለች፡፡ እናቷ ምንም ገቢ የላቸውም፡፡ “ገቢያችን የሰው እጅ ማየት ነው” ብላለች ሃዳስ፡፡ ከአምስት ዓመት በፊት ጥሩ ውጤት እያላቸው በድጋፍ እጦት ትምህርታቸውን ማቋረጥ የለባቸውም ተብሎ፣ ጥሩ ውጤት ስለነበራት መመረጧን ተናግራለች፡፡ ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ የሚያደርግላቸውን ድጋፍ፣ ቀደም ሲል ሁለቱ ተማሪዎች እንዳሉት በማድነቅ ዘርዝራ፣ ለጥናት ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጡ ገልጻለች፡፡ ‹‹ክረምት ላይ አስጠኚ መምህራን ይቀጠራሉ፤ከመስከረም-ሰኔ ድረስ ግዙበራ ሳህና በበጎ ፈቃደኞች ድጋፍ እንድታጠና ይደረጋል›› ብላለች፡፡
ተማሪዎቹን አግኝተን ያነጋገርነው በደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ ነው፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ኔልሰን ማንዴላ በሕይወት ቆይተው ቢሆን ኖሮ 99ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከብሩ ነበር፡፡ በሕይወት ባይኖሩም፤ የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ፣ በ2001 ዓ.ም ኔልሰን ማንዴላ ለደቡብ አፍሪካና ለመላው ዓለም ላበረከቱት አስተዋጽኦ፣ የልደታቸው ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲከበር በወሰነው መሠረት፣ የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲም ዕለቱን፣ እንደ ኔልሰን ማንዴላ ጥሩ ተግባር እየፈፀመ የሚገኘው ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ድጋፍ ከሚያደርግላቸውና ከ12-16 ዓመት ዕድሜ ካላቸው 39 ህፃናት ጋር አሳልፏል፡፡
የመንግሥታቱ ድርጅት፣ የኔልሰን ማንዴላ የልደት ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ እያንዳንዱ አገር እንዲያከብረው ከመወሰኑ አንድ ዓመት በፊት፣ ማንዴላ ለድርጅቱ ስልክ ደውለው፤ ‹‹እያንዳንዱ የዓለም ዜጋ ዓለምን ወደ ተሻለ ደረጃ ለመለወጥ በተለይም ለሕፃናት፣ ቢያንስ የ67 ደቂቃ መስዋዕትነት መክፈል ይጠበቅበታል›› ብለው ባሳሰቡት መሠረት፣ የኤምባሲው አባላት ጊዜአቸውንና ከግል ገንዘባቸው 85 ሺህ ብር በማውጣት ለተጠቀሱት ሕፃናት ስጦታ (የተለያዩ ልብሶችና ጫማዎች) ገዝተው ማበርከታቸውን አስታውቀዋል፡፡
‹‹የብዙ ልጆች ወላጆች አካል ጉዳተኞች ናቸው። የአምስት ልጆች ወላጆች ማየት አይችሉም፡፡ ሌሎች ደግሞ የተለያየ የአካል ጉዳት፣ ሥጋ ደዌ፣ ኤችአይቪ/ ኤድስ ያለባቸው ናቸው፡፡ ተስፋቸው ልመና ብቻ ነው፡፡ ልጆቻቸው ካልደረሱላቸው ሕይወታቸው አይለወጥም፡፡ እነዚህ ልጆች ድጋፍ አግኝተው፣ ተምረው፣ ሕይወታቸው ተለውጦና ውጤታማ ሆነው ለቤተሰቦቻቸው ሲደርሱ ማየት ነው ግባችን፡፡ ልጆቹ ተምረው ራሳቸውን ከቻሉ የቤተሰቦቻቸው ህይወት ይለወጣል የሚል እምነት አለን፡፡ ለአካባቢውም ሞዴል ይሆናሉ፡፡ ቆሬ አካባቢ የተማረ ኅብረተሰብ ማየት ነው ዓላማችን›› ያሉት ደግሞ የብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ወ/ሮ መንበረ በቀለ ናቸው፡፡
“ዋናው ትኩረታችን፣ ተማሪዎች የትምህርት እገዛ አግኝተውና  የተሻለ ውጤት አምጥተው አካባቢውን የሚለውጡ ዜጎችን መፍጠር ነው፡፡ ቆሬ አካባቢ ያለ ሰው አብዛኛው ድሃ ነው፡፡ የምንረዳቸው ልጆች ወላጆች አብዛኞቹ በልመናና ቆሻሻ በመልቀም የሚተዳደሩ ናቸው፡፡ ተማሪዎች በቂ ምግብ አያገኙም፡፡ ተምረውና ሕይወታቸው ተለውጦ የተሻለ ሰው እንዲሆኑ እገዛ እናደርጋለን ያሉት ወ/ሮ መንበረ፤ ለሰው ልጅ  ዋነኛው አስፈላጊ ነገር ምግብ ስለሆነ በየቀኑ ምሳና እራት ይመገባሉ፡፡ ደብተርና መጻሕፍት መያዣ ቦርሳን ጨምሮ የትምህርት መሳሪያ ወጪያቸው ይሸፈናል፡፡ ለሚማሩበት ት/ቤት ዓመታዊ ወጪ ይከፈላል፡፡ ዩኒፎም፣ ልብስና ጫማ ይገዛላቸዋል፡፡ ጤናቸውን እንከታተላለን፡፡ የታመመ ልጅ ካጋጠመን እናሳክማለን፡፡ ፈቃደኛ በጎ አድራጊ ሐኪም ሲገኝ ደግሞ ሁሉም የጤና ምርመራ ይደረግላቸዋል፡፡ የጥናት ፕሮግራምም ቀርፀው እንዲያጠኑ እናደርጋለን፣ በጥብቅ እንከታተላለንም›› ብለዋል ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ፡፡
ብርሃን ይሁን ኢትዮጵያ የራሱ ገቢ የለውም። ኢትዮጵያውያን ወዳጆቻችንን፣ ጓደኞቻችንንና ቤተሰቦቻችንን ድጋፍ እንዲያደርጉልን እንጠይቃለን። የአንድ ወይም የሁለት ልጅ የወር ወጪ የሚያግዙን ሰዎች አሉ፡፡ ከውጭ የምናገኘው ድጋፍ በጣም ትንሽ ስለሆነ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ በዚህ አጋጣሚ ጅምራችን እንደተገለፀው ነው፡፡ መጨረሻችንም ያማረና ስኬታማ፣ ልጆቹም ተለውጠው፣ የወላጆቻቸውን ሕይወት የሚለውጡና ጥሩ አገር ተረካቢ ዜጋ እንዲሆኑ፣ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የተቻላችሁን ድጋፍ እንድታደርጉልን እጠይቃለሁ›› ብለዋል ወ/ሮ መንበረ በቀለ፡፡
የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ ሠራተኞች ገንዘብ አዋጥተው የገዙትን ልብስ፣ ጫማ፣ የትምህርት ቁሳቁስ፣ የንጽህና መጠበቂያ፤…. ስጦታ ለተማሪዎቹ የሰጡት በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር፣ በአፍሪካ ኅብረትና በመንግሥቱ ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቋሚ ተወካይ፣ ሚ/ር አዱሚዶ ኒሺንጋ ሲሆኑ አንድ ተማሪ የሠራው ሥዕልም ተበርክቶላቸዋል፡፡

  በደራሲ ተስፋዬ አለነ የተሰናዳው “የሚስት ምርቃት” ልብ ወለድ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሐፉ በጥቅሉ በፍቅር፣ በማህበራዊና በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ
የሚያጠነጥኑ 20 አጫጭር ልብ ወለድ ታሪኮችን ያካተተ ሲሆን ከዚያ ውስጥ “ስደተኛው ፍቅር” የተሰኘው ታሪክ ግን በእውነተኛ ታሪክ ላይ ያተኮረ መሆኑን ደራሲው ተናግሯል፡፡ በ216 ገፅ የተመጠነው መፅሐፉ በ61 ብር ከ20 ሳንቲም ለገበያ የቀረበ ነው፡፡ አምስተኛ ስራውን ሰሞኑን ለአንባቢ ጀባ ያለው ደራሲ ተስፋዬ አለነ በተለያዩ ጋዜጦችና መፅሄቶች አዝናኝ ወጎችን በመፃፍ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ ቀደምም “የመንጌ ውሽሚት”፣ “እንክልካይ”፣ “ዘላለማዊ ጓደኝነት” እና “Effective English” የተሰኙ መፅሐፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወቃል፡፡

ሚዳቆ የመጻሕፍት አሳታሚዎች ደርጅት ትላንት ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ “የኮሪያ ዘመቻ”፣ “የአድዋ ድል” “የእነ ሳራ ዛፍ” እና “የሳራ ጥያቄ” የተባሉትን የህፃናት መፅሐፍ መስቀል አደባባይ ከቀይ ሽብር ሰማዕታት ሙዚየም ጀርባ በሚገኘው አዲስ አበበ ሙዚየም ውስጥ አስመረቀ፡፡ በዕለቱ የምረቃ ስነ ስርዓቱን መድረክ ደራሲ፣ ዳይሬክተርና ተዋናይት አዜብ ወርቁ የመራች ሲሆን ደራሲ እንዳለጌታ ከበደም በእንግድነት ተገኝቶ መፅሐፍቱን መመረቁ ታውቋል፡፡ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ፀሐፍት፣ ሰዓሊዎች፣ አርታኢዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመው እንደነበር ሚዳቆ አሳታሚዎች ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

 በአርቲስት ዓለምፀሐይ ወዳጆና በሙያ ባልደረቦቿ የሚመራውና መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው ዓመታዊ የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በአክሱም ሆቴል ይካሄዳል፡፡
በዕለቱ የተለያዩ ግጥሞችች፣ ወጎች፣ መነባንብ፣ በአርቲስት ታምሩ ንጉሴ የሚቀርብ የክራር ሙዚቃና ሌሎችም የኪነ ጥበብ ድግሶች ይቀርባሉ፡፡
የኢትዮጵያን ኪነ ጥበብ ለማሳደግና ለወጣት የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች መድረክ ለመፍጠር ታልሞ በየዓመቱ በሚዘጋጀው በዚህ ምሽት ላይ ምልዕቲ ኪሮስ፣ ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን፣ በላይ በቀለ ወያ፣ ሰለሞን ሞገስና ሌሎችም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ የተባለ ሲሆን በአገራችን የቅኔ ባህል ዙሪያ ባለ ቅኔው ዶ/ር ታደለ ገድሌ የቅኔ ዲስኩር ያቀርባሉም ተብሏል፡፡
በዕለቱ የኪነ ጥበብ አፍቃሪ በነፃ ምሽቱን እንዲታደም ግብዣ ቀርቧል፡፡

     70 ሺህ ሄክታር እርሻ እና ከ100 በላይ የአልማዝና ወርቅ ማምረቻ ፈቃድ አላቸው

      የኮንጎው ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ካቢላ እና ቤተሰባቸው በአገር ውስጥና በውጭ አገራት በሚንቀሳቀሱ መሪ ከ80 በላይ ታላላቅ የንግድ ኩባንያዎች ውስጥ ጠቀም ያለ የባለቤትነት ድርሻ እንዳላቸውና አጠቃላይ ሃብታቸው በአስር ሚሊዮኖች ዶላር እንደሚቆጠር ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ተቀማጭነቱ በአሜሪካ የሆነው ኮንጎ ሪሰርች ግሩፕ የተባለው የጥናት ተቋም ያወጣውን የጥናት ውጤት ጠቅሶ ሮይተርስ ከትናንት በስቲያ ባወጣው ዘገባ እንዳለው፣ ጆሴፍ ካቢላ እና ቤተሰባቸው በኩባንያዎቹ ውስጥ ካላቸው የባለቤትነት ድርሻ በተጨማሪ፣ 70 ሺህ ሄክታር የእርሻ መሬትና አልማዝና ወርቅ ማምረት የሚያስችሉ ከ100 በላይ የማዕድን ፍለጋ ንግድ ፈቃዶች አሏቸው፡፡
በ2001 አባታቸውን ተክተው ወደ ስልጣን መምጣታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ምንም እንኳን የስልጣን ዘመናቸው ያበቃው ባለፈው ታህሳስ ወር ላይ ቢሆንም፣ ስልጣኔን አልለቅም ብለው በመሪነታቸው መቀጠላቸውን አመልክቷል፡፡
በተያያዘ ዜናም በሙስና ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ መዝብረዋል በሚል ክስ የተመሰረተባቸውን የናይጀሪያ የቀድሞ የነዳጅ ሚኒስትር ዲዛኒ አሊሰን ማዱኬ ጉዳይ ሲመረምር የቆየው ፍርድ ቤት፣ የግለሰቧን 37 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ንብረት እንዳይንቀሳቀስ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈበት እጅግ ዘመናዊ ቤት ሲሆን፣ ለንደን ውስጥ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በዋስ ተፈትተው በዚያው የሚገኙት የቀድሞዋ ሚኒስትር ቤቱን የገዙት ከመንግስት ካዘና ያለአግባብ በመዘበሩት 37.5 ዶላር ነው መባሉን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

  ከዘመናችን የአለም ታላላቅ የሂሳብ ሊቃውንት አንዷ እንደሆነች የሚነገርላት እና የሂሳብ የኖቤል ሽልማት ተብሎ የሚታወቀውን የፊልድስ ሜዳል ሽልማት በማግኘት የመጀመሪያዋና ብቸኛዋ የአለማችን ሴት የሆነቺው ኢራናዊቷ መሪየም ሚርዛካኒ በጡት ካንሰር ህመም በ40 አመቷ ማረፏ ተዘግቧል፡፡ ላለፉት ለአራት አመታት ያህል በጡት ካንሰር ስትሰቃይና ህክምናዋን ስትከታተል የቆየቺው ኢራናዊቷ የስታንፎርድ የሂሳብ ፕሮፌሰር መሪየም ሚርዛካኒ ባለፈው ቅዳሜ ለህልፈተ ህይወት መዳረጓን ሜይል ኤንድ ግሎብ ዘግቧል፡፡ መሪየም ሚርዛካኒ ኮምፕሌክስ ጂኦሜትሪ እና ዳይናሚክ ሲስተምስ በተባሉ ዘርፎች ባፈለቀቻቸው እጅግ ገራሚ ግኝቶቿ የሂሳብ የኖቤል ሽልማት ተብሎ የሚታወቀውንና በመስኩ የላቀ አስተወጽኦ ላበረከቱ ላላላቅ ተመራማሪዎችና መምህራን የሚሰጠውን የፊልድስ ሜዳል ሽልማት እ.ኤ.አ በ2014 ማግኘቷን ያስታወሰው ዘገባው፣ እስከ ዕለተ ሞቷ ድረስ በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የሂሳብ መምህርት ሆና ስታገለግል መቆየቷንም አመልክቷል፡፡
በቴህራን በሚገኘው ሻሪፍ ዩኒቨርሲቲ እና በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቷን የተከታተለቺው መሪየም፣ የኢራን አለማቀፍ የሂሳብ ኦሎምፒያድ ሽልማት አሸናፊ ከመሆኗ በተጨማሪ የተለያዩ በርካታ አለማቀፍ ሽልማቶችን ማግኘቷንም ዘገባው አስታውሷል፡፡

 ባለፈው የፈረንጆች አመት 2016 በአለማችን የተለያዩ አገራት የሚገኙ 12.9 ሚሊዮን ህጻናት ምንም አይነት የክትባት አገልግሎት አለማግኘታቸውንና ይህም ክትባት ያላገኙ ህጻናትን ለከፉ በሽታዎች ያጋልጣል ተብሎ እንደሚሰጋ የአለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ ሰሞኑን ባወጣውና የ194 የአለማችን አገራትን የክትባት ሽፋን ደረጃ በሚያሳየው ሪፖርት እንዳለው በአመቱ ከአለማችን 10 ህጻናት አንዱ ምንም አይነት ክትባት ያላገኘ ሲሆን፣ በ8 የአለማችን አገራት ከሚገኙ ህጻናት በ2016 አመት የክትባት አገልግሎት ያገኙት ከግማሽ በታች ናቸው፡፡
አነስተኛ የህጻናት ክትባት አገልግሎት ካለባቸው የአለማችን አገራት መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱት የአፍሪካ አገራት እንደሆኑ የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የክትባት አገልግሎት መስፋፋት ለመቻሉ ፖሊዮን የመሳሰሉ በሽታዎች በወረርሽኝ መልክ እንዲከሰቱ ሰበብ ሊሆን ይችላል ብሏል፡፡
ተጨማሪ 6.6 ሚሊዮን ያህል የአለማችን ህጻናትም ዲቲፒ የተባለውን የክትባት አይነት ለመጀመሪያ ዙር ከወሰዱ በኋላ፣ ቀሪ ሁለት ዙር ክትባቶችን ሳያገኙ መቅረታቸውን ሪፖርቱ ጠቁሟል፡፡
ክትባት በአለማችን ተቅማጥንና ቲታነስን ጨምሮ በተለያዩ የበሽታ አይነቶች ሳቢያ በየአመቱ ሊከሰቱ ይችሉ የነበሩ 3 ሚሊዮን ያህል የህጻናት ሞቶች እንዳይከሰቱ እያደረገ ይገኛል ያለው ሪፖርቱ፣ ባለፉት 10 አመታት በአገራት መካከል ያለው የክትባት ሽፋን ልዩነት በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉንም አመልክቷል፡፡
በተያያዘ ዜናም፣ በአለማቀፍ ደረጃ የተሟላ የጤና አገልግሎት አቅርቦትን ለማሟላት የተያዘውን የዘላቂ ልማት ዕቅድ ግብ ለማሳካት፣ በየአመቱ 371 ቢሊዮን ዶላር ያህል ገንዘብ መመደብ እንደሚያስፈልግ የአለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡
መንግስታት፣ ለጋሾችና በጎ አድራጊዎች በየአመቱ የተጠቀሰውን ያህል ገንዘብ መድበው ከሰሩ እስከ 2030 ድረስ 97 ሚሊዮን ያህል ሰዎችን በበሽታ ለህልፈተ ህይወት ከመዳረግ ሊያድኑ እንደሚችሉ የጠቆመው ድርጅቱ፣ ለአብዛኞቹ አገራት ይህን ያህል ገንዘብ መመደብ አዳጋች በመሆኑ ለጋሾች ድጋፋቸውን መስጠት እንደሚኖርባቸውም አመልክቷል፡፡

    • የበቆጂ አትሌቶች ለኢትዮጵያ ባለፉት 20 ዓመታት 10 የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያዎች ተጎናፅፈዋል፡፡ 15 የዓለም አትሌቲክስ ሪከርዶች አስመዝግበዋል፡፡ እንዲሁም ከ34 በላይ        የዓለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳልያዎችን ሰብስበዋል፡፡
    • ጥሪዎች ለበቆጂ ሯጮች ትንሳዔ ከጋዜጠኛ፤ ከከንቲባ ፤ ከእውቅ አሰልጣኞች…
    • በመላው ኢትዮጵያ ትልልቅ የስፖርት መሰረተ ልማቶች ተገንብተዋል፡፡ በቆጂ ግን የረባ ስታድዬምና የመሮጫ ትራክ የላትም፡፡ ለምን ?
    • አትሌቲክስ ኢንቨስትመንት ነበር… ግን የታላላቅ አትሌቶች መቆጠብ፤ የበቆጂ የተሰጥኦ አካባቢነት መዘንጋት

     ባለፉት 25 ዓመታት በታላላቅ የዓለማችን የአትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ለኢትዮጵያ የላቁ ውጤቶችን እያስመዘገቡ ቆይተዋል፡፡  ትውልዳቸው በአርሲ  አሰላ፣ በቆጂና ሌሎች የገጠር ከተሞች ናቸው፡፡ በረጅም ርቀት  10ሺ  እና 5ሺ ሜትር፤ በመካከለኛ ርቀት የአትሌቲክስ ውድድሮች ዓለምን ተቆጣጥረዋል፡፡ በማራቶንና በጎዳና ላይ ሩጫዎች በሚያስመዘግቧቸው ውጤቶችም የገነኑ  ናቸው፡፡
አንድ ጣሊያናዊ ጋዜጠኛ የሯጮች ከተማ በሚል በሰራው የፎቶ ቡክሌት የበቆጂ ጉብኝቱን አስመልክቶ  ‹‹…. የዓለማችንንን ምርጥ ማራቶን ሯጮች የልደት ምስክር ወረቀቶች ቢመረመሩ በቆጂ ተደጋግማ ትጠቀሳለች…›› በሚል መፃፉን መጥቀስ ይቻላል፡፡
በ10ሺ ሜትር የአፍሪካን ፈር ቀዳጅ ድል ያስመዘገበችው ደራርቱ ቱሉ፤ በዓለም አትሌቲክስ የረጅም ርቀት ንጉስ ለመባል የበቃው ኃይሌ ገብረስላሴ፤ በ10ሺሜ፤ በ5ሺ ሜትር የማይሰበር ክብረወሰን የያዘው ቀነኒሳ በቀለ፤ በኦሎምፒክ ማራቶን ልዕልቷን ወደ አገራቸው የመለሱት ገዛሀኝ አበራና ፋጡማ ሮባ እንዲሁም ቲኪ ገላና፤ ፤ የዓለማችን የምንግዜም ምርጥ የረጅም ርቀት ሯጭ የተባለች ባለከፍተኛ ውጤት ባለቤት ጥሩነሽ እና የዘመኑ ምርጥ ፕሮፌሽናል ኢትዮጵያዊ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ፤ ፈጣኑ የኢትዮጵያ አትሌት መሃመድ አማን  ሌሎችም ከአርሲዎቹ የገጠር ከተሞች ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ በኦሎምፒክ፣ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና፣ በዓለም አገር አቋራጭ፣ በአፍሪካ ሻምፒዮና፤ በመላው አፍሪካ ጨዋታዎች እና ሌሎች ዓለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ ውድድሮች ከ67 በላይ የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለኢትዮጵያ ሰብስበዋል፡፡  
ከአዲስ አበባ በ230 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው በቆጂ በተለይ የምትነሳ ናት፡፡ ደራርቱ ቱሉ በጣዕሜ ፤ ፋጡማ ሮባ በመራሮ፣  ጥሩነሽ ዲባባ በጨፋ፣ ቀነኒሳ በቀለና፣ ታሪኩ በቀለ፣ ቲኪ ገላናና፣ እልፍነሽ ዓለሙ በሌሙ፣ የተወለዱባቸው የገጠር መንደሮች ናቸው፡፡ የበቆጂን ዙርያዋና ከበዋታል።  የበቆጂ አትሌቶች ለኢትዮጵያ ባለፉት 20 ዓመታት 10 የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያዎች ተጎናፅፈዋል፡፡  15 የዓለም አትሌቲክስ ሪከርዶች አስመዝግበዋል፡፡ እንዲሁም ከ34 በላይ የዓለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳልያዎችን ሰብስበዋል፡፡
 በአንድ ወቅት አንድ ታዋቂ የቱርክ ጋዜጠኛ እንደጻፈው በቆጂ እንደ  አገር በመቆጠር በዓለም የአትሌቲክስ መድረክ ምን ያህል የገዘፈች መሆኗን በንፅፅር መመልከት ይቻላል፡፡  ባለፉት 25 ዓመታት በኦሎምፒክ መድረክ ከ60ሺ ነዋሪዎች ከሚገኙባት በቆጂ የወጡ አትሌቶች የሰበሰቧቸው ሜዳልያዎች  1.2 ቢሊዮን ህዝብ ያላት ህንድ በሁሉም ስፖርቶች በኦሎምፒክ ከሰበሰበቻቸው ሜዳልያዎች የሚበልጥ፤ 247 ሚሊዮን ህዝብ ካላት ኢንዶኔዥያ በእጥፍ የሚልቅ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፡፡ ለናሙና ያህል ብቻ የዲባባ እህትማማቾች በኦሎምፒክ መድረክ ያገኟቸው የወርቅ ሜዳልያዎች ብዛት 22 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሶሪያ እና 28 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሳውዲ አረቢያ በድምር ከሰበሰቡት የሚበልጥም ነው፡፡ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ በዓለም ሻምፒዮና፤ በኦሎምፒክ እና በዓለም አገር አቋራጭ ትልቁን ውጤት ያስመዘገበችው ጥሩነሽ ዲባባ የሰበሰበችው የወርቅ ሜዳልያ ብዛት 179 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ፓኪስታን እንኳን አላስመዘገበችውም፡፡
በዚህ ከፍተኛ ስኬት የኢትዮጵያ ክብር በዓለም አትሌቲክስ በወርቃማ ቀለም እንዲሰፍር ሆኗል፡፡ በቆጂን በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅ የሯጮች ምድርም  አድርጓታል።
የአትሌቶቹ ውጤታማነት ላይ በየጊዜው በአትሌቲክስ ባለሙያዎች ምርምሮች እየተደረጉባት ይገኛል፡፡  በመላው ዓለም በሚሰራጩ ትልልቅ ሚዲያዎች  በተደጋጋሚ የምትጠቀስ ከተማ መሆኗም ቀጥሏል፡፡ በየጊዜው ልዩ ዘጋቢ ፊልሞች ተሰርተውላታል፡፡  በተለያዩ ጊዜያት ስለሚወጡባት ታላላቅ አትሌቶቿ፤ ስለመልክዓምድሯ፤ ስለአየር ንብረቷ፤ ስለ አትሌቶች አኗናር፤ ስልጠና እና የእለት ተዕለት ህይወት በስፋት እየተወሳ ነው፡፡  
ጥሪ ከጋዜጠኛው
በ1ኛው «አረንጓዴ ልማት ለአረንጓዴ ጎርፍ» የጎዳና ሩጫ መነሻነት… በቆጂን በአትሌቲክስ ለማልማት
የታላላቅ  አትሌቶች መገኛ በሆነችው በቆጂ ከተማ  ለመጀመሪያ ጊዜ  የ5ነ ኪሜ የጎዳና ላይ ሩጫ «አረንጓዴ ልማት ለአረንጓዴ ጎርፍ» በሚል መርህ ከወር በፊት ተዘጋጅቶ ነበር። ከበቆጂ 80ኛ ዓመት ክብረ በዓል ጋር ተያይዞ  በተካሄደው ውድድር ከአምስት ሺ በላይ የከተማዋ ነዋሪዎች እንዲሁም አትሌቶች ተሳትፈዋል፡፡ የከተማዋ የሩጫ ባህል ሆኖ የ5ኪ ሜትር ውድድሩ በአትሌቶች መካከል ከፍተኛ ፉክክር የተደረገበት ሲሆን ተሳታፊው ህዝብም  ችግኝ ይዞ በመሮጥ ድምቀት ሰጥቶታል፡፡
የጎዳና ላይ ሩጫው ጭላሎ ሚዲያ ፕሮሞሽን በተባለ ድርጅት የተዘጋጀ ነው፡፣፡ ጭላሎ በበቆጂ ገዝፎ የሚታይ ልዩ ግርማ ሞገስ ያለው ተራራ ነው፡፡ የድርጅቱ ባለቤት   ጋዜጠኛ እና ገጣሚ አንዱዓለም ጌታቸው ነው፡፡ ተወልዶ ያደገው በቆጂ ላይ ነው፡፡ ስለበቆጂ ልጆች አስተዳደግ እና የሩጫ ባህል ለስፖርት አድማስ ሲገልፅ‹‹ እንደማንኛውም የከተማዋ ተወላጅ ልጅነቴን ያሳለፍኩት በእረኝነት ነው ፡፡ ቤተሰብ  ሲልክህ ሮጥ ብለህ  ይባላል፡፡ ወደ ተላክበት የምትሮጠው ብዙ ርቀት ነው። ሽርካ የተባለች የገጠር ከተማ ወደ የሚኖሩ አያቶቼ ቤት ስላክ አስታውሳለሁ፡፡ 3 ሰዓታት ይወስድብኛል፡፡ አብዛኛውን እየሮጥኩ ነበር የምሸፍነው፡፡ ስለዚህ ሩጫ የልጅነት ህይወታችን አካል ነው፡፡ የከተማዋ ባህል ሆኖ አድገንበታል፡፡ …የሁሉ መነሻ  ከ25 ዓመታት በፊት የደራርቱ ቱሉ በባርሴሎና ኦሎምፒክ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ፈርቀዳጅ ድል ማስመዝገቧ ነበር። ያኔ በቆጂ የነበረ ትውልድ በሙሉ ሯጭ መሆንን ተመኘ፡፡›› ብሏል።
አንዱዓለም እነ ቀነኒሳ፤ የዲባባ እህትማቾችና ሌሎችም ምርጥ አትሌቶች በተማሩበት ትምህርት ቤት ስለነበረው የሩጫ ትጋት እና ፍቅር ትውስታ አለው፡፡ በተለይ በእረፍት ሰዓት በተማሪዎች መካከል ይደረጉ የነበሩ ውድድሮች ናቸው። በቆጂ ዛሬም ድረስ ሩጫን  ባህሏ ያደረገች  ልዩ ከተማ ናት። በትምህርት ቤቶች ብቻ አይደለም፡፡ በከተማዋ ዙርያ ገብ በሚገኙ ጫካዎች፤ የተንጣለሉ መስኮች እና ጋራዎች ልምምድ እና ስልጠና የተለመዱ ትእይንቶች ናቸው፡፡
ጋዜጠኛ አንዷለም ምንም እንኳን ገና በታዳጊነቱ የሩጫ ህልም ቢኖረውም ብዙ አልገፋበትም፡፡ በከተማዋ ሚኒ ሚዲያዎች ግን ስለ በቆጂ ታላላቅ አትሌቶች ገድል በመዘገብ ወደ ጋዜጠኝነት ሙያ አድልቶ ነበር፡፡ በከተማዋ ከአትሌቲክስ ጋር የተያያዙ ስራዎችን ለማከናወን ሲተጋ  ቆይቷል፡፡ ‹‹ በቆጂ የስሟን ያህል ትኩረት አላገኘችም፡፡ በስፖርት መሰረተ ልማቶች እጅግ ኋላ ቀር ናት፡፡ ስለዚህም ይቆጨኛል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስሟ በገነነ የሯጮች ምድር  ሁለገብ ስታድዬም፤ የማሰልጠኛ ማዕከልና የመሮጫ ትራክ አለመኖሩ ተገቢ አይደለም፡፡ የዛሬ አስር ዓመት  የኢትዮጵያ አትሌቶች ሙዚዬም በከተማዋ ሊገነባ መሰረት ተጥሎ ተግባራዊ አልሆነም፡፡ይህን ለመቀየር ነው የበኩሌን ጥረት ማድረግ የጀመርኩት፡፡›› በማለት የተነሳበትን ዓላማ ለስፖርት አድማስ አስረድቷል፡፡
ስለዚህም አንዷለም ጌታቸው ለከተማዋ ባደረበት ቁጭት የጎዳና ላይ ሩጫውን ለማዘጋጀት እንዲወስን አድርጎታል፡፡ ጭላሎ ሚዲያ የተባለ ድርጅቱን ካቋቋመ በኋላ በመጀመርያ ለ2009 የገና በዓል የአትሌቶች መንደር በሚል ልዩ የቴሌቭዥን ፕሮግራም አዘጋጀ፡፡ በቆጂ ማናት የሚለውን ጥያቄ መልስ ለመስጠት በተዘጋጀው በዚህ ልዩ ስነስርዓት እንደመዝናኛ የሙዚቃ ከንሰርት ከማዘጋጀቱም በላይ እነ ኃይሌ፤ ገዛሐኝ አበራ እና ሌሎች ትልልቅ አትሌቶች በክብር እንግድነት የተሳተፉበት ነበር፡፡ ከዚህ ተመክሮው በኋላ እንዷለም የመጀመርያውን የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በከተማዋ ሊያስተናግድ ችሏል። የአትሌቶች መገኛ የሆነች ታሪካዊ ከተማ እንዴት ስፖርተኛ ህዝቧን የሚያሳትፍ ውድድር አይኖራትም በሚል ቁጭት በቀረፀው ፕሮጀክት ነው፡፡«አረንጓዴ ልማት ለአረንጓዴ ጎርፍ» በሚል መርህ በስኬት የተካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ በየዓመቱ ለመቀጠል እንደሚፈልግ ያሳወቀው አንዷለም፤ በተለይ በአየር ንብረት ለውጥ የዓለማችን ታላላቅ አትሌቶች የተገኙባት በቆጂ ከተማ ተጎጂ መሆኗን ለዓለም ለማሳወቅ የሚያስችል ፈርቀዳጅ ሃሳብ በመሆኑ ውጤታማነቱን ያመለክታል ብሏል፡፡
አትሌቲክስ ስታድዬም በሚል ስያሜ ያልተሟላ መሰረተ ልማት እንደሆነ ቀጥሏል፡፡ ትራክ የሌለው አጥር የለሌለው የበቆጂ ስታድዬም፡፡ በሌላ በኩል የበቆጂ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከልም በተሟላ ግንባታና መሰረተ ልማት የሚንቀሳቀስ አይደለም፡፡ በአጠቃላይ እነዚህ የስፖርት መሰረተ ልማቶች በትኩረት ተገንብተው የሚንቀሳቀሱ አለመሆናቸው ከባድ ቁጭት የሚፈጥርብኝ ነው፡፡ እውነቱን ለመናገር የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የውጤት መውረድ እና የላቀ ብቃት ያላቸው አትሌቶች በተተኪነት የማፍራት እድል የተበላሸው ከእነዚህ ሁኔታዎች ጋር ተያይዞ ይመስለኛል፡፡›› በማለት አንዷለም ጌታቸው ለበቆጂ ከተማ የሚሰማውን ቁጭት ይገልፀዋል። በርግጥ የበቆጂ አትሌቶች ከስታድዬሙ እና ከማሰልጠኛ ማዕከሉ ይልቅ በተፈጥሯዊ መልክዓ ምድሮችን መስራት ይመርጣሉ ግን የስፖርት መነሰረተ ልማቶች መገንባት አለባቸው፡፡

ጥሪ ከከንቲባው
ለኢትዮጵያ ሆነ ለአፍሪካ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ  አትሌቶችን ለማፍራት
 የበቆጂ ከንቲባ አቶ ሽመልስ ተስፋዬ ለጋዜጠኞች በሰጡት አስተያየት  1ኛው «አረንጓዴ ልማት ለአረንጓዴ ጎርፍ» የጎዳና ላይ ሩጫው የበቆጂን 80 ዓመት ከመዘከሩም በላይ ከውድድሩ ጎን ትልልቅ አጀንዳዎች በማንገብ በመከናወኑ አስደስቶናል ይላሉ፡፡ የአየር ንብረት ለውጥን ለመዋጋት የሚደረግ ዘመቻን ለማፋፋም፤ በአትሌቲክስ እየተንሰራፋ የመጣውን የዶፒንግ ችግር ተመለከተ የግንዛቤ እና የማስተማርያ መድረክ ለመፍጠር እንዲሁም ዜግነታቸውን የሚቀይሩ አትሌቶች እየበዙ መምጣታቸውን ተቃውሞ ለውጥ ለመፍጠር የሚደረጉ  ጥረቶችን ያስተዋወቅንበት መድረክ ስለሆነ በማለትም ማስረጃቸውን አቅርበዋል፡፡
‹‹በቆጂ የማትነጥፍ የአትሌቲክስ ስኬት ምንጭ ሆና እንድትቀጥልና ተከታዮችን ለማፍራት ታላላቅ አትሌቶች ያላቸው ምሳሌነት አስተዋፅኦ ቢኖረውም ገና ብዙ መስራት ይጠበቅብናል፡፡›› የሚሉት ከንቲባው ‹‹አትሌቶች የሚጠበቅባቸውን ያህል ሰርተዋል ብሎ የከተማው መስተዳድርም ሆነ ህዝቡ አያምንም፡፡ ከተማዋ ጥሩ ስታድዬም፤ የልምምድ ማዕከል እንኳን የላትም፤ ይህ ደግሞ መቀየር አለበት ሲሉ ይናገራሉ፡፡ በከተማው መስተዳድር፤ በወጣቶችና ስፖርት፤ በአትሌቲክስ ፌደሬሽንነና በሌሎች ባለድርሻ አካላት የተከናወኑ ጅምር ተግባራት መኖራቸውን አያይዘው የጠቀሱት ከንቲባው በቆጂ ላይ ደረጃውን የጠበቀ ስታድዬም እንዲሁም የልምምድ እና ማሰልጠኛ ማዕከል መገንባት ለኢትዮጵያ ሆነ ለአፍሪካ ከፍተኛ ውጤት ሊያስመዘግቡ የሚችሉ አትሌቶችን ለማፍራት የሚያስችል ነው ይላሉ፡፡
‹‹ታላላቆቹ አትሌቶች በስፖርቱ ካገኙት ክብር እና አንፃር እንዲሁም በኢኮኖሚ ካላቸው አቅም ጋር ተያይዞ በቆጂ ላይ ብዙ ሊሰሩ ይችላሉ፡፡ ይህን አስመልክቶ በየጊዜው ውይይት እያደረግን ቆይተናል፡፡ የአትሌቶችን ተግባራዊ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው፡፡ ከዚህ በፊት በከተማው አስተዳደር በኩል ለአትሌቶቹ የተለያዩ ማበረታቻዎችን በማድረግ ሰርተናል፡፡ በአሰላ ከተማ የንግድ ማዕከል፤ ሆቴል የሰሩ አሉ፡፡ የከተማው መስተዳድር ከዚህ በፊት ለተለያዩ የልማት ስራዎች ይሆናል በሚል መሬቶችን ለአትሌቶች ሰጥቶ ነበር፡፡ ታላላቆቹ አትሌቶች በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች የምንሰራቸው የግንባታ ስራዎች እስኪጠናቀቁ ግዜ ስጡን ብለው ስለነበር እንጅ። አትሌቶች ለእኛ አምባሳደሮቻችን ምልክቶቻችን ናቸው። የከተማው መስተዳድር አብሯቸው ለመስራት ይፈልጋል። እነሱም ፍላጎት እንዳላቸው እናውቃለን፡፡›› ብለዋል የበቆጂ ከንቲባ አቶ ሽመልስ ተስፋዬ፡፡
የከተማው መስተዳድር በተለያዩ ክለቦች፤ በግብረሰናይ ተቋማት የተያዙ የአትሌቲክስ ፕሮጀክቶች እንደሚከታተል የከተማው ከንቲባ ተናግረው፤  የኦሮምያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የሚያንቀሳቅሰው የበቆጂ ማሰልጠኛ ማዕከልም በመንግስት በጀት ተገንብቶ ከተለያዩ ስፍራዎች ተሰጥኦ ያላቸውን አትሌቶች በመመልመል በቂ ስልጠና በመስጠት እየሰራ መሆኑን፤ የብዙ ቀደምት አትሌቶች ዛሬም ቢሆን ዋና መገኛዎች ትምህርት ቤቶች በመሆናቸው በዚያም ሰፊ ተግባር ለማከናወን እንቅስቃሴ አለ የሚሉት ከንቲባው በአጠቃላይ ግን በተሟላ ጥራት እና ብቃት እየሰራን ስላልሆንን ይህን በከፍተኛ ንቅናቄ ለመቀየር ትኩረት አድርገናል ብለዋል፡፡
ይቀጥላል

-------------------------------------------------
                          
                         የአፍሪካ ዋንጫን በቻይና ወይም በአሜሪካ የማዘጋጀት ሃሳብ ቀርቧል

      የ2023 የአፍሪካ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድርን በቻይና፣ በአሜሪካ ወይም በኳታር ለማዘጋጀት እና ከአህጉሪቱ ውጭ የሚገኙ 3 አገራት ብሄራዊ ቡድኖችን በውድድሩ ለማሳተፍ የሚያስችል ምክረ ሃሳብ በአፍሪካ የእግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ካፍ ስብሰባ ላይ መቅረቡ ተዘግቧል፡፡
ካፍ የአፍሪካ የአግር ኳስ ዋንጫን የገንዘብ አቅም ለማጠናከርና ውድድሩን የበለጠ ሳቢነት ያለው ለማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ለመምከር ባለፈው ማክሰኞ እና ረቡዕ በሞሮኮ ባካሄደው ስብሰባ ላይ የቀረበው ይህ ምክረ ሃሳብ፣ የ2023ን የአፍሪካ ዋንጫ እንዲያዘጋጁ ቻይናን፣ አሜሪካን ወይም ኳታርን የመጋበዝ አማራጭን ያቀረበ ነው፡፡ የገንዘብ አቅምን ማጠናከርንና የአፍሪካ ዋንጫን አለማቀፋዊ ማድረግን ግቡ ያደረገ ነው የተባለው ምክረ ሃሳቡ፣ በመገናኛ ብዙሃን በስፋት መሰራጨቱን ተከትሎ በበርካታ የማህበራዊ ድረገጽ ተጠቃሚዎች ትችት እየተሰነዘረበት ይገኛል፡፡
ሃሳቡ በካፍ ተቀባይነት የማግኘቱ ዕድል ጠባብ መሆኑን የዘገበው ጋና ሶከር ኔት ድረገጽ፣ የ2023 የአፍሪካ ዋንጫን የማስተናገድ ተራውን ለጊኒ ቀደም ብሎ መስጠቱንም አስታውሷል፡፡