Administrator

Administrator

በዱሮ ጊዜ በአንድ መንደር አራት ክፉ ክፉ አለቆች ይኖሩ ነበር ይባላል፡፡ እነዚህም፤ አቶ ዓለም፣ አቶ ደመና፣ አቶ ሰማይ ነህ እና አቶ በላይ ይባላሉ፡፡
አቶ ዓለም ለምጣም ሲሆን ሰውን ከሥራ ማባረር የሚወድ ቂመኛና ክፉ ሰው ነው፡፡ በማርፈድ ከሥራ ያስወጣል፡፡ ቆማችሁ ስታወሩ አገኘኋችሁ ብሎ ከሥራ ያስወጣል፡፡ ስጠራችሁ ቶሎ አልመጣችሁም ብሎ ከሥራ ያባርራል፡፡
አቶ ዓለም ደግሞ ከባላገር መጥቶ የሠለጠነ፣ ከሁሉ የምበልጥ ነኝ ባይ፣ ትኩስ ዘናጭ ነው፡፡ ሆኖም ሌላው የለበሰው ማናቸውም ልብስ ያስቀናዋል። በዚህ ምክንያት ደህና የለበሰ ሰው ላይ መጮህ ነው፡፡ ሰበብ እየፈለገ መደንፋት ነው!
አቶ ሰማይ ነህ ደግሞ የሁሉ አለቃ ነኝ ባይ ነው፡፡ ዋና ሥራው መጠራጠር ነው፡፡ ምንም ነገር ይስማ “ይቺማ ነገር አላት” ይላል፡፡ አንድ ሰው ለጨዋታ ብሎ ቀና ነገር ሲነግረውም፤ “ከጀርባው ምን አለው? ምን ቢያስብ ነው?” ይላል፡፡
የመጨረሻው አቶ በላይ ነው፡፡ በላይ እንደስሙ የበላይ ነው፡፡ የመሥሪያ ቤቱ የመጨረሻ ጣሪያ እሱ ነው፡፡ ግን መሀይም ነው! የተማረ ሲያይ ደሙ ይፈላል፡፡ “ወረቀት አደለም! ወረቀት አደለም! ዋናው ሥራ ነው! እዚህ ወረቀት እያንጋጋችሁ አትጐለቱ!” ይላል፤ ጠዋት ገና ሥራ ሲገባ!
እነዚህን ሰዎች በቅጡ የሚያውቅ ባለቅኔ እንዲህ ሲል ገጠመ ይባላል
“ዓለም ቡራቡሬ፣ ሁሉን ሰው አታላይ
ደመናውን አልፎ፣ አለ ጥቁር ሰማይ
የተማረው ከሥር፣ ያልተማረው በላይ”
                                                              * * *
የሀገራችን ቢሮክራሲ በመልካም ሰዎች ሳይሞላ መልካም አስተዳደር ማምጣት አዳጋች ነው፡፡ ከመግዛት ባህሪያችን፤ ከአለቅነት ባህሪያችን በፊት ሰው የሚያደርግ ልዩና መልካም ባህሪ ሊኖረን ይገባል፡፡ ለዚህ ደግሞ ከቤተሰብ ጀምሮ ከተኮተኮትንበት ግብረገብነት እስከ ትምህርት ወግ -ማዕረግ ድረስ የሠለጠነ አዕምሮና የበሰለ የህይወት ልምድ ውስጣችን መገንባት ይኖርበታል። ከዚያ፤ በሥራ ዓለም የምናገኘው የዕለት ተዕለት ልምድ፣ ከየሰዉ ጋር ያለንን መስተጋብር (Interaction)፣ ትዕግሥትና ሆደ - ሰፊነት፣ ትህትናና ክህሎት፤ ብሎም የአመራር ብቃት እየሠረፀብን ይመጣል፡፡
በዚህ ላይ ነው እንግዲህ ቅጥ ያለው የፖለቲካ አመለካከት ሲጨመርበት፣ በግድ እኔ ያመንኩትን እመን፣ ያን ካላረክ ጠላቴ ነህ፤ የሚል ሰው አንሆንም፤ የምንለው፡፡ ያመንከውን አምነህ፣ ተቻችለን አንድ መሥሪያ ቤት መኖር አያቅተንም ብለን ማሰብ፤ ጤናማና ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ነው። ከማቃቃር ይልቅ ያቀራርበናል፡፡ ከማራራቅ ይልቅ ያስተቃቅፈናል፡፡ ከመጠፋፋት ይልቅ ያስተራርመናል፡፡
በእስተዛሬው የፖለቲካና የማህበራዊ ጉዞአችን ወይ “ብቆጣም እመታሻለሁ፣ ብትቆጪም እመታሻለሁ” ማለት፤ አለበለዚያ ደግሞ “አሸናፊ ነኝ ያለኔ አታውራ”፤ “ተሸናፊ ነህ ስላንተ እንዳይወራ!” እንዳንል ያደርገናል፡፡
መልካም የስፖርት ድጋፍ ባህል መዳበር አለበት፡፡ በስንት ዘመን ዛሬ ያጋጠመንን ዕድል ተመስገን እንበል፡፡ ተጨዋቾቻችን በምንም መመዘኛ ዛሬ የደረሱበት ደረጃ የሚመሰገን ነው፡፡ አንድ ከተመልካቾቻችን የሚጠበቅ ባህል አለ ዘላቂነት የሙሉ ጊዜ ድጋፍ የመስጠት ልምድ! ይሄ በአንድ ቀን ሊሆን የሚችል ባህሪ እንዳልሆነ ግልጽ ነው፡፡ ሆኖም በልቦናችን ይደር ብናሸንፍ ወይም ብንመራ ቴሌቪዢናችንን የበለጠ እንደማንከፍተው ሁሉ፤ ብንሸነፍ ቴሌቪዥናችንን አንዘጋውም፡፡
ከአንድ የጭብጨባና የጩኸት ድጋፍ ድምጽ በአንድ ጊዜ ወደሚደብት የድብርት ድባብ አንግባ፡፡ በየትኛውም ማህበራዊ መስክ፣ ፖለቲካችንን ጨምሮ፤ የሞቅ ሞቅና የለብለብ አካሄድ ደግ አደለም፡፡ ዘላቂ እንሁን በአቋማችን እንግፋ፡፡
አለበለዚየ “ያደሩበት ጭቃ፣ ከጭድ ይሞቃል” ዓይነት ይሆንብናልና በአዎንታዊ ጉዟችን እንግፋ ማናቸውም ውጤት የነገ መንገዳችን መትጊየ ነው፡፡ ፈረንጆች፤ “all that had gone before was a preparation to this; And this is a preparation to this” ይላሉ፡፡ “እስካሁን ያለፍንበት ሁሉ እዚህ ለመድረስ ነበር፡፡ ይሄ ደሞ ለነገ መዘጋጃችን ነው” እንደማለት ነው፡፡
ድል ለዋሊያዎቻችን!

ጋዜጠኛ ነኝ በማለት አጭበርብሯል የተባለው ቻይናዊ የዜድቲኢ ሰራተኛ ነው ተብሏል። ZTE፣ ለስራ ወደ ጅማ የሄደ ሰራተኛ የለንም፤ የተፈላጊውን ማንነት አጣራለሁ ብሏል። በጅማ ከተማ ጋዜጠኛ ነኝ በማለት አጭበርብሯል የተባለው ቻይናዊ ኢንጂነር ዋንግ ዮንግ ለምርመራ እየተፈለገ ሲሆን፣ የጅማ ፖሊስ ተጠርጣሪውን ከአዲስ አበባ ይዞ ለመውሰድ እያፈላለገ ነው።

ዋንግ ዮንግን በሚመለከት የዜድቲኢ የህዝብ ግንኙነት ተወካይ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፣ ዜድቲኢ ለስራ ወደ ጅማ የላከው ሰራተኛ፤ የለም፤ የተፈላጊውን ማንነት እናጣራለን ብለዋል። ከጅማ ፖሊስ ለቀረበ ጥያቄ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ምላሽ፣ ዋንግ ዮንግ የቴሌኮም ኢንጂነርና የዜድቲኢ ሰራተኛ መሆኑን ገልጿል። የጅማ ፖሊስ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በመተባበር ተፈላጊውን ተጠርጣሪ ለመያዝ ሲያፈላልግ እንደቆየና ትናንት የዜድቲኢ ተወካዮችን እንዳነጋገረ ታውቋል።

ፖሊስ ዋንግ ዮንግን ለምርመራ ማፈላለግ የጀመረው፣ ጥቅምት አጋማሽ ላይ ጅማ ውስጥ “ጋዜጠኛ ነኝ በማለት አጭበርብሯል” የሚል ጥቆማ ከአካባቢው ነዋሪ ከወ/ሮ ታደለች ተመስገን ከደረሰው በኋላ ነው። ጉዳዩም ከካሳ ክፍያ ጋር መያያዙ፣ ከኩባንያዎች ተቀናቃኝነት ጋር የተሳሰረ ሊሆን እንደሚችል የሚጠቁሙ መረጃዎች አሉ። ወ/ሮ ታደለች ተመስገን፣ ከሁለት ወራት በፊት ስራ ላይ በአደጋ ህይወቱን ያጣ ሰራተኛ ቤተሰብ ናቸው። የአንድ የአገር ውስጥ ድርጅት ተቀጣሪ የነበረው ሰራተኛ በኢንተርኔት ማስፋፊያ ፕሮጀክት የፋይበር ኦፕቲክስ ዝርጋታ ላይ ነው በአደጋ የሞተው።

የሰራተኛው አሟሟት ላይ ጥያቄዎች ተነስተው እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፣ ቀጣሪው ድርጅት በበኩሉ፤ ሰራተኛው አስፈላጊ የጥንቃቄ አልባሳትና መሳሪያዎችን ሲጠቀም እንደነበር በፖሊስ ምርመራ መረጋገጡን ገልጿል። ከሟች ቤተሰብ ጋር በመነጋገር ቀጣሪው ድርጅት የመቶ ሺ ብር ካሳ የከፈለ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱን በበላይነት የሚመመራው ሁዋዌ በበኩሉ 200 ሺ ብር ድጋፍ እሰጣለሁ ብሏል። ከዚህ በኋላ ነው፣ ዋንግ ዮንግ ወደ ጅማ መጥቶ “ጋዜጠኛ ነኝ በማለት አጭበርብሯል” የተባለው።

ቻይናዊው ዋንግ ዮንግ መጥቶ እንዳገኛቸውና ሆቴል ድረስ ጠርቶ እንዳነጋገራቸው የጠቀሱት ወ/ሮ ታደለች፣ “ጋዜጠኛ ነኝ፤ ተጨማሪ ገንዘብ እንድታገኙ አደርጋለሁ፤ አዲስ አበባ እንሂድ” በማለት ሊያግባባቸው እንደሞከረ መናገራቸውን ምንጮች ገልፀዋል። ወ/ሮ ታደለች ለፖሊስ ያመለከትኩት ጥርጣሬ ስላደረብኝ ነው ማለታቸው የተገለፀ ሲሆን ፖሊስ በበኩሉ፤ ዋንግ ዮንግ ጋዜጠኛ ሳይሆን የቴሌኮም ኢንጂነርና የዜድቲኢ ሰራተኛ መሆኑን ያረጋገጠው ባለፈው ሳምንት ከሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ባገኘው መረጃ ነው ተብሏል። በእነዚህ መረጃዎች የተነሳ፣ ጉዳዩ በዜድቲኢ እና በሁዋዌ መካከል ካለው ተቀናቃኝነት ጋር የተያያዘ ሳይሆን አይቀርም የሚል ጥርጣሬ መፈጠሩ አልቀረም። የዜድቲኢ የህዝብ ግንኙነት ተወካይ ስለ ዋንግ ዮንግ ትናንት ተጠይቀው በሰጡን ምላሽ፣ ዜድቲኢ ለማንኛውም ስራ ወደ ጅማ የላከው ሰራተኛ እንደሌለ እርግጠኞች ነን፤ የሰውዬውን ማንነት አጣርተን እናሳውቃለን ብለዋል።

በ380ሺ ብር ካፒታል ፤ ከመቶሺ በላይ ተሳታፊና እስከ 10ሺ ብር ሽልማት

            በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በአይነቱ ልዩ የሆነ አዲስ የስፖርት ውርርድ ጨዋታ እንደተጀመረ ዳጉ ቤት ኢትዮጵያ ባለፈው ሳምንት በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል ባዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስተዋወቀ፡፡ ዳጉ ቤት ኢትዮጵያ በእንግሊዝና ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ አራት ኢትዮጵያዊያን የተቋቋመ ድርጅት ሲሆን ለስራው በብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ሙሉ ፈቃድ አግኝቷል፡፡ የስፖርት ውርርዱ በውጭ ሀገር በሚካሄዱ የስፖርት ውድድሮች ላይ ተመስርቶ የተጀመረ ነው፡፡ በስፖርት የተለያዩ ሁኔታዎች በመወራረድ በህጋዊ መንገድ እየተዝናኑ መጫወት ይቻላል የሚለው ዳጉ ቤት፤ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት የገቢ ምንጭ በመፍጠር ለሀገር ጥቅም የሚያስገኝ ስራ እንደሚሆን ተስፋ ያደርጋል፡፡ የስፖርት ውርርዱን በህጋዊ መንገድ መጀመሩ በህብረተሰቡ ዘንድ ህገወጥ በሆነ መንገድ በመወራረድ የሚፈጠሩ አላስፈላጊ ችግሮች እንደሚከላከል የገለፀው ዳጉ ቤት ኢትዮጵያ ከስፖርት ውርርዱ ጋር በተያያዘ በተለያዩ ሁኔታዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚንቀሳቀስም አስታውቋል።

በዚህም በሀገራችን ለሚገኙ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው የስፖርት ፌዴሬሽኖች እርዳታ በማድረግ ስፖርቱን ለማሳደግ እንደሚሰራ የገለፀው ድርጅቱ በተቋቋመበት የመጀመሪያው አመትም ከተጣራ ገቢው ሃያ በመቶውን ለቦሊንግ አሶሴሽን እርዳታ ለመስጠት መስማማቱንም አመልክቷል፡፡ የዳጉ ቤት ኢትዮጵያ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ አብርሃም ንጋቱ የስፖርት ውርርዱ መሸነፍ እና ማሸነፍ ያለበት ጨዋታ መሆኑን ሲያስረዱ ተጨዋቾች እና ተሳታፊዎች የስፖርት ውድድሮችን በመመልከት ከሚኖራቸው መዝናናት ባሻገር በሚሰጡት ግምት ተሸላሚ የሚሆኑበትን እድል በመፍጠር እንዲሰራ እና አካሄዱም በህግና ስርዓት የተመራ እንደሚሆን አብራርተዋል፡፡ ዳጉ ቤት ኢትዮጵያን የጀመርነው እንደፓይለት ፕሮጀክት ነው የሚሉት አቶ አብርሃም ንጋቱ፤ የስፖርት ውርርዱን የጀመርነው በለጋሃር አካቢ በሚገኘው ሱቅ እና በድረገፅ በሚደረግ ግንኙነት ነው ብለው ማጫወት የጀመርነው በእግር ኳስ ቢሆንም ወደፊት የቅርጫት ኳስ እና የአትሌቲክስ ውድድሮችንም በማወራረድ ለማጫወት እናስባለን ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ወደፊት የውርርዱን መንገድ በአጭር የፅሁፍ መልዕክት እና በሚፋቁ የሎተሪ ካርዶች ለማድረግ እቅድ መኖሩን ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽንን በመወከል በጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገኝተው የነበሩት የውድድሮች የስራ ሂደት ባለቤት አቶ ተድላ ዘመናዊ ውርርድ በኢትዮጵያ ስፖርት መጀመሩ እንደሚያስደስት ገልፀው፤ ዳጉ ቤት ኢትዮጵያ ባለድረሻ አካላት ከሆኑት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽንና የፌደራል ስፖርት ኮሚሽን ግልፅ በሆነ መንገድ ተግባብቶ መስራት እንደሚኖርበት መክረው አወራራጁ ድርጅቱ ስራውን ሲጀምር በውጭ ውድድሮች ላይ ከሚያተኩር ለአገር ውስጥ ውድድሮች ቅድሚያ ቢሰጥ የተሻለ ነበር ብለዋል፡፡ ለነገሩ ዳጉ ቤት ኢትዮጵያ የስፖርት ውርርዱን በውጭ አገር ውድድሮች መጀመሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻውንና የስፖርት ጋዜጠኞችንም አላስደሰተም፡፡ የብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው የስፖርት ውርርድ እጅግ አትራፊ ቢዝነስ መሆኑን ተናግረው ዳጉ ቤት ኢትዮጵያ የውርርድ ስርዓቱን በአገር ውስጥ ውድድሮች በተለይ የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦችን በማሳተፍ ቢጀመር ምርጫዬ ነበር ካሉ በኋላ ‹‹ውርርድ ካለ የምመርጠው በኢትዮጵያ እግር ኳስ ነበር፡፡

ይህን ለማሳካት ትኩረት ሰጥታችሁ መስራት አለባችሁ፡፡ እግር ኳሱ በተነቃቃ መንፈስ እንዲቀጥል፤ በወጣቶች ላይ በስፋት እንዲሰራ እና ክለቦች የገቢ ምንጮቻቸውን እንዲያሰፉ በሚያደርግ አሰራር ብትንቀሳቀሱ ጥሩ ነው፡፡ ከእነ አርሰናል አስቀድመን ለኢትዮጵያ ክለቦች ማሰብ ይገባል፡፡ የክለቦች መጠናከር ለብሄራዊ ቡድን ድጋፍ እንደሚሆን መታወቅ አለበት፡፡ በማለት ሃሳባቸውን አስረድተዋል። ከጋዜጠኞች መካከልም የዳጉ ቤት ኢትዮጵያ የስፖርት ውርርድ በውጭ አገር ውድድሮች መጀመሩ የአገር ውስጥ ውድድሮች የሚያስፈልጋቸውን ትኩረት ሊያሳጣ አይችልም ወይ በሚል ስጋት የቀረበ ጥያቄም ነበር፡፡ የዳጉ ቤት ኢትዮጵያ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ አብርሃም ንጋቱ በእነዚህ ሃሳቦች ላይ በሰጡት ምላሽ የስፖርት ውርርዱን በአገር ውስጥ ውድድሮች ለመጀመር የቅርብ ጊዜ እቅድ አለመኖሩን ሲገልፁ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረጉ የእግር ኳስ ውድድሮች ባላቸው የፉክክር ደረጃ እና ሂደት ለውርርድ በሚያመች ሁኔታ ላይ አለመገኘታቸውን በመጥቀስ የጨዋታዎችን ውጤት በህገወጥ ሁኔታ ለመቀየር የሚያስገድዱ ጥፋቶች በዚህ ምክንያት ሊያጋጥሙ መቻላቸው ሌሎች ችግሮችን ሊያመጣ መቻሉን አስበን የተውነው ነው ሲሉ አብራርተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የእግር ኳስ ውድድሮች ለስፖርት ውርርድ አመቺ ሊሆኑ እስከሚችሉበት አስተማማኝ የእድገት ደረጃ ግን ድጋፍ በማድረግ አብረን እየሰራን እንቀጥላለን በማለትም ምክትል ስራ አስኪያጁ ቃል ገብተዋል፡፡

በጋዜጣዊው መግለጫ ላይ ተገኝተው የነበሩት የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተወካይ የስፖርት ውርርድን ለማካሄድ የሚያስችል መመርያ በኢትዮጵያ መንግስት የፀደቀው ባለፈው ዓመት መሆኑን ሲገልፁ ፍቃድ የሚያገኙ ድርጅቶች በህግ ማዕቀፍ ሆነው ውርርዱን እንዲያጫውቱ እንደሚደረግና የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር አፈፃፀሙን በመከታታል በመቆጣጠር አብሮ እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡ የስፖርት ውርርድ በህጋዊ መንገድ ማከናወን ሊያጋጥሙ የሚችሉ ማህበራዊ ቀውሶችን ለመከላከል አስተዋፅኦ እንዳለው ያስገነዘቡት የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተወካይ ፤ ውርርዱን ለሚያደርግ ተቋም ፈቃድ የምንሰጠው ባለን መመርያ መሰረት ድርጅቱ ከሚያገኘው አጠቃላይ ገቢ የመንግስት 50 በመቶ ድርሻን እንዲከፍል፤ ለማህበራዊ ግልጋሎት ቢያንስ 20 በመቶ ያህል እንዲያበረክት እንዲሁም ውርርዱን ያለምንም ቅሬታዎች እና ችግሮች በትክክል እንዲያከናውን በማሳሰብ ነው ብለዋል፡፡ የትኛውም ድርጅት፤ ተቋም ወይም ግለሰብ ለስፖርት ውርርድ ህጋዊ ፈቃድን ማግኘት እንደሚችል ያስረዱት የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተወካይ ፤ የሚሰጠው ፍቃድ በየዓመቱ የሚታደስ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የስፖርት ውርርድ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተስፋፋ ሲሆን ገበያው 70 በመቶ የሚያተኩረው በእግር ኳስ ስፖርት ላይ ነው፡፡ በመላው ዓለም የሚደረጉ የስፖርት አወራራጅ እና አቋማሪ ኩባንያዎችን በመገምገም በየዓመቱ ከ55ሺ በላይ የስፖርት ግጥሚያዎችን የሚከታተለው ስፖርት ራዳር የተባለ ተቋም ይፋ ባደረገው መረጃ ኢንዱስትሪው በየዓመቱ ከ700 ቢሊዮን ዶላር እንደሚንቀሳቀስበት አመልክቷል፡፡

የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ በዓለም አቀፍ አቋማሪ እና አወራራጅ ድርጅቶች ተመራጭ መሆኑን የሚገልፁ መረጃዎች ክለቦች ከ19 የተለያዩ ኩባንያዎች ጋር በአጋርነት በመስራት በዓመት በአማካይ እስከ 6 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያገኙ ነው፡፡ በ80 የብሮድካስት ኩባንያዎች ዓለም አቀፍ የስርጭት ሽፋን ያለው የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ከሚሰሩ አቋማሪ እና አወራራጅ ድርጅቶች በአርሰናል ፓዲ ፓወር፤ በቼልሲና በማንችስተር ሲቲ 188ቤት እንዲሁም በማንችስተር ዩናይትድ ቢዊን በአጋርነት መስራታቸው ይጠቀሳል፡፡ ዳጉ ቤት ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የማጫወቻ ሱቅ ለገሃር ኮሜርስ አካባቢ ከኖክ ማደያ አጠገብ መክፈቱን የገለፁት አቶ አብርሃም ንጋቱ ፤ ዳጉ ቤት ዶት ኮም (www.DagooBet.com) ዌብ ሳይት ኦን ላይን በመጠቀም መጫወት እንደሚቻል አስታውቀዋል፡፡ ውርርዱ የሚካሄድባቸው መንገዶች - አሸናፊውን ቡድን በመገመት መወራረድ - ትክክለኛ ውጤት በመገመት መወራረድ - የጨዋታውን የመጀመሪያ አጋማሸ ውጤት በመገመት መወራረድ - ቀድሞ ጐል የሚያስቆጥረውን ክለብና ተጫዋች በመገመት መወራረድ - የማስጠንቀቂያ ካርድ የሚመለከቱ ተጫዋቾችን በመገመት መወራረድ - እንዲሁም በሌሎች መጫወት ይቻላል ህግጋት እና መመሪያዎች - በ90 ደቂቃ የእግር ኳስ ጨዋታ ውድድር ውጤት መወራረድ ይችላሉ፡፡

- ነገር ግን ውርርዱ የተጨማሪ ሰዓት (30 ደቂቃ) እና የመለያያ ምትን አያጠቃልልም፡፡ - ሁሉም ውርርድ የሚካሄደው ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት ይሆናል - 1,X,2 እነዚህ ለውርርዱ የምንጠቀምባቸው ኮዶች ሲሆኑ የሚወክሉልን ጨዋታው ይዞት ሊመጣ የሚችለውን ሦስት አይነት ውጤት ነው፡፡ - 1 ባለሜዳው ያሸንፋል X ቡድኖቹ አቻ ይወጣሉ 2 ከሜዳው ውጪ የሚጫወተው ያሸንፋል፡፡ ስለዚህ በውርርዱ ላይ መሳተፍ የሚፈልግ አንድ ሰው ቢያንስ 3 ጨዋታዎች ቢበዛ ደግሞ 10 ጨዋታዎች ላይ መወራረድ ይችላል፡፡ ለምሳሌ 1 X 2 አርሰናል vs ከማንችስተር 2፡10 3.30 2.90 ሳውዝሃፕተን vs ከፉልሃም 1.80 4.05 3.90 ቶትንሃም vs ኒውካስትል 3.60 3.10 2.75 እርስዎ የመረጡት ከመጀመሪያው ጨዋታ አርሰናል ያሸንፋል ከሆነ ኮድ 1 ሲሆን ያለውም ዋጋ 2.10 ይሆናል በሁለተኛው ጨዋታ ሳውዝሃፕተን ያሸንፋል ብለው መወራረድ ከፈለጉ ኮዱ 2 ሲሆን ያለውም ዋጋ 2.90 ይሆናል ሦስተኛው ጨዋታ በአቻ ውጤት ይጠናቀቃል በለው መወራረድ ከፈለጉ የውርርድ ኮዱ X ሲሆን የውርርድ ዋጋውም 3.10 ይሆናል፡፡ እንበልና ከላይ የመረጡት ሶስቱንም የጨዋታ ውርርድ አሸነፉ፡፡ ከላይ እንደተመለከትነው እያንዳንዱ ውረርድ የራሱ የሆነ ዋጋ አለው ስለዚህ በሶስቱም አሸናፊ ስለሆኑ የሶስቱንም ዋጋ እናበዛለን ይኸውም 2.10 X2.90 X3.10 = 18.87፡፡ መጀመሪያ ላይ ለውረርድ ያስያዙት 10 ብር ቢሆን ከላይ የተመለከተውን የሶስት ጨዋታዎች ዋጋ ብዜትን ማለትም 18.87 ባስያዙት ገንዘብ (10 ብር) በማባዛት የ188.70 አሸናፊ ይሆናሉ፡፡ ነገር ግን ይህ የጨዋታውን ግብር አያጠቃልልም፡፡ ማሳሰቢያ ከተወራረዱ በኋላ የሚሰጥዎትን ደረሰኝ በጥንቃቄ ይያዙ፡፡ አሸናፊ ከሆኑ ደረሰኙን ይዘው በቀረቡ ጊዜ ያሸነፉት ገንዘብ ይከፈልዎታል፡፡

ማራቶን የማዘጋጀት ሃሳብ አላቸው

                በሀዋሳ ከተማ የተገነባውን ገዛኸኝና እልፍነሽ ሆቴልና ሪዞርት ህዳር 14 በይፋ ሲመረቅ ልዩ የ10 ኪሎሜትር የዱላ ቅብብል ውድድር እንደሚካሄድ ታወቀ፡፡ በምረቃው ስነስርዓት ላይ በክብር እንግድነት እንዲገኙ ኡጋንዳዊው የኦሎምፒክ እና የዓለም ሻምፒዮን የማራቶን ድርብ አሸናፊ ስቴፈን ኪፕሮች እና ኬንያዊ አትሌት ጄፈሪ ሙታይ ተጋብዘዋል፡፡ በሌላ ዜና ባልና ሚስቶቹ ማራቶኒስቶች አትሌት ገዛኸኝ አበራ እና አትሌት እልፍነሽ አለሙ በሚቀጥለው ዓመት አንድ የማራቶን ውድድር በኢትዮጵያ ለማዘጋጀት ማሰባቸውን ሲያስታወቁ ተተኪ አትሌቶችን ለማግኘት የአገር ውስጥ ውድድሮች መብዛታቸው አስፈላጊ እንደሆነ ስላመኑበት የነደፉት እቅድ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አትሌት ገዛኸኝ አበራ እና አትሌት እልፍነሽ አለሙ ትናንት በዋና ፅህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ የሆቴልና ሪዞርት ምረቃው ከአትሌቲክስ ውድድር ጋር ማያያዝ ያስፈለገው ተተኪ አትሌቶች የእነሱን አርዓያ እንዲከተሉ ለማነሳሳት በማሰባቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

አትሌት እልፍነሽ አለሙ‹‹ ማንኛውም ሰው ዓላማዬ ብሎ ከሰራ ለየትኛውም ደረጃ ይደርሳል፡፡ በአሁን ዘመን ያሉ አትሌቶች ደከመን፣ ሰለቸን፤ ከሳን ፤ ጠቆርን ሳይሉ በትጋት መስራት አለባቸው፡፡ በስፖርቱ እኛ የደረስንበት ስኬት ለማግኘት ብቻ ሳይሆን ከእኛ በላይ ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ማወቅ አለባቸው›› ብላለች፡፡ አትሌት ገዛኸኝ በበኩሉ ‹‹እኛ ሮጠን ሆቴሉን ሰርተናል፤ አትሌቱም እንደማንኛውም ህብረተሰብ በትጋት ከሰራ ይሳካለታል፡፡›› በማለት ተናግሯል፡፡ በሆቴልና ሪዞርቱ ምረቃ ላይ የሚካሄደው የ10 ኪሎሜትር የዱላ ቅብብል ውድድሩ መነሻውና መድረሻው ገዛኸኝና እልፍነሽ ሆቴልና ሪዞርት እንደሆነ የገለፀው አትሌት ገዛኸኝ አበራ፤ አንድ ክለብ ሁለት ሴት እና ሁለት ወንድ ባጣመረ የአራት አትሌቶች ቡድን ይወዳደሩበታል ብሏል፡፡

በዱላ ቅብብል ውድድሩ ለመሳተፍ 8 ክለቦች ማረጋገጫ የሰጡ ሲሆን የመከላከያ፤ የማረሚያ፤ የፖሊስ፤ የሙገር እና ሌሎች የሁለተኛ ዲቪዚዮን ክለቦች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ አሸናፊ ሊሆን የሚበቃው ቡድን የመጨረሻ ሯጭ የውድድሩ ርቀት ቢያንስ 100 ሜትሮች ሲቀሩት ለገዛኸኝና እልፍነሽ ሆቴልና ሪዞርት ለሚጋበዘው የክብር እንግዳው የምረቃ ሪበኑን እንዲቆርጥ የሚያስረክበበት ሁኔታ መመቻቸቱንም አትሌት ገዛኸኝ አበራ ገልጿል። አንደኛ ለሚጨርስ ቡድን 7ሺ ብር ፤ ለሁለተኛ 5ሺ ብር እንዲሁም ሶስተኛ ለሚወጣው ቡድን 3ሺ ብር ይበረከታል፡፡ ገዛኸኝና እልፍነሽ ሆቴልና ሪዞርት አትሌት ገዛኸኝ አበራ በሲድኒ ኦሎምፒክ በማራቶን አሸንፎ ሲመጣ፣ የደቡብ ክልል መንግሥት በሃዋሳ ከተማ በሸለመው 25ሺህ ካ.ሜ ቦታ ላይ ባለ 5 ኮከብ ደረጃ በመያዝ የተገነባ ነው፡፡ ለሆቴሉ ግንባታ እስካሁን 200 ሚሊዮን ብር ወጭ መደረጉን የገለፀው አትሌት ገዛኸኝ በአሁኑ ጊዜ 150 ሠራተኞች እንዳሉትና የማስፋፊያው ስራ ሲጠናቀቅ ለ500 ሰዎች የስራ እድል እንደሚፈጥር እንጠብቃለን ብሏል፡፡ የገዛኸኝና እልፍነሽ ኢንቨስትመንት በሃዋሳ ከተማ ከሚገኘው ሆቴልና ሪዞርት ብቻ ሳይወሰን በቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ከተማም በቢሾፍቱ ሐይቅ ላይ ያሰሩት ባለ 5 ኮከብ ሪዞርት በቀጣዩ ዓመት እንደሚያስመርቁ ፤ በአዲስ አበባም በተለያዩ ቦታዎች የእንግዳ ማረፊያ ሕንፃዎችን እያስገነቡ እንደሆነና በጥቁር ውሃም ቦታ ተረክበው ምን መሥራት እንዳለባቸው እያሰቡ ናቸው፡፡

ከሥምህ እንጀምር…

አብርሃም አስመላሽ እባላለሁ፡፡ የ18 ዓመት ወጣት ነኝ፤ ትውልድና ዕድገቴ በትግራይ ክልል መቀሌ ገጠራማ አካባቢ ሲሆን ወላጆቼ ገበሬዎች ናቸው፡፡ ከቤተሰባችን አራት ልጆች አንዱ ነኝ፡፡ የትምህርት ታሪክህ ምን ይመስላል? መቀሌ እያለሁ እስከ 4ኛ ክፍል ተምሬያለሁ፡፡ አዲስ አበባ ከመጣሁ በኋላ 5ኛ ክፍል ቀጥዬ የነበረ ቢሆንም ከዚያ በላይ መማር አልቻልኩም፡፡ እንዴትና መቼ ወደ አዲስ አበባ መጣህ? ታላቅ ወንድሜ ቀደም ብሎ መጥቶ ነበር፡፡ እሱን ተከትዬ ነው የመጣሁት፡፡ አዲስ አበባ ከመጣሁ ሁለት ዓመት ያስቆጠርኩ ሲሆን ወንድሜ አራት ዓመት ሆኖታል፡፡ መቀሌ እያለህ ምን ትሰራ ነበር? ቤተሰቦቼን በሥራ ከማገዝ ውጭ ምንም አልሰራሁም፡፡ አዲስ አበባ ከመጣሁ በኋላ ከወንድሜ ጋር ሸቀጣ ሸቀጥ እያዞርኩ እሸጥ ነበር፡፡ የወንድሜ ስም ሞገስ ነው፤ የግለሰብ ቤት ተከራይተን ኳስ ሜዳ አበበ ቢቂላ ስታዲየም አካባቢ ነው የምንኖረው፡፡

በብስክሌት ላይ የመሞረድ አገልግሎት መስጠት የጀመርከው መቼ ነው? ከወንድሜ ከሞገስ ጋር ማስቲካና ሌሎች ሸቀጣ ሸቀጦችን እያዞርን በመሸጥ ላይ እያለን ሥራችንን ወዴት እናሳድግ ብለን ስናስብ፣ ይህ ሃሳብ መጣልን። ባለ ክቡን ሞረድ በእጅ በመዘወር ስለታማ ነገሮች ሲሞረዱ ያየነው በመቀሌ ከተማ ነበር፡፡ በእጅ የሚዘወረውን ለምን በብስክሌት ፔዳል አናደርገውም ብለን አዲስ ሥራ በመፍጠር ወደ ሥራው ገባን፡፡ አሁን እኔም ወንድሜም በሁለት የተለያዩ ብስክሌቶች ላይ ሞረድ አስገጥመን ከቦታ ወደ ቦታ በመንቀሳቀስ ለሕብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጠን ነው፡፡ አሰራሩ እንዴት ነው? ሞረዱን በብስክሌቱ ላይ ለማስገጠምስ ምን ያህል ገንዘብ አወጣችሁበት? ዝርዝር ወጪውን የሚያውቀው ወንድሜ ቢሆንም ለስራው የገዛነው አሮጌ ብስክሌቶችን ነው፡፡

ሞረዱ ብስክሌቱ እጀታ አካባቢ የተገጠመ ሲሆን በብስክሌቱ የኋላ ጐማ ላይ ተጨማሪ ቸርኬ በማስገጠም፤ የኋላው ጐማ መሬት ለቆ እንዲቆም ካደረግነው በኋላ የብስክሌቱን ፔዳል በመምታት ከቸርኬውና ከሞረዱ ጋር በተያያዘው ቺንጋ ሞረዱ ሲሽከረከር ነው መሞረድ የምንጀምረው፡፡ ለዚህ ሥራ መነሻ የሆነንን ገንዘብ ያገኘነው ሸቀጣ ሸቀጥ ሸጠን ካጠራቀምነው ትርፍ ነው፡፡ ቸርኬውን፣ ቺንጋውና ሞረዱን በብስክሌቱ ላይ የገጠሙልን የጋራዥ ባለሙያዎች ነው፡፡ ሞረዱ ለስንት ጊዜ ያገለግላል? የአንዱ ክብ ሞረድ ዋጋ 160 ብር ሲሆን ሁለት ወር ያህል ከቆየ ብዙ ቆየ እንላለን፡፡ ለነገሩ እኛ በእግር (ጉልበት) የብስክሌት ፔዳል እየመታን ስለምንሰራ ነው እንጂ በዲናሞ ቢሆን ኖሮ ከሁለት ወር በላይም ሊያገለግል ይችል ነበር፡፡ ይህንን ሥራ ከጀመርክ ስንት ጊዜህ ሆነህ? እኔ ሁለተኛ አመቴን ልይዝ ነው፡፡

ወንድሜ ሦስት አመት ይሆነዋል፡፡ ምን ምን ትሞርዳለህ? ቢላዎችና መቀስ የመሳሰሉ እንሞርዳለን፡፡ ለዳግመኛ አገልግሎት የሚውሉ ቁሳቁሶችን በሙሉ እሞርዳለሁ፡፡ የመሞረጃ ዋጋ ምን ያህል ነው? ቢላዋ 3 ብር፣ መቀስ 2 ብር፣ የመፋቂያ ነጋዴዎች ቢላዋ በ1 ብር እንሞርዳለን፡፡ ዋጋው እንደሚሞረደው ዕቃ ትልቅነትና ትንሽነት ሊለያይ ይችላል፡፡ የት አካባቢ ነው አገልግሎት የምትሰጠው? ተንቀሳቃሽ ነኝ፡፡ ሁሉም ቦታ እሄዳለሁ፡፡ ካዛንችስ፣ ሾላ፣ ቦሌ፣ መገናኛ፣ መርካቶ፣ ፒያሳ፣ አስኮ… ተንቀሳቅሼ ነው ስራውን የማገኘው፡፡ የሚፈልግህ ሰው የት ያገኝሃል? ለምሳሌ ዛሬ አንተ እኔን ያኘኸኝ በድንገት ነው፡፡ እኔም ወደ መርካቶ የመጣሁት በአጋጣሚ ነው፡፡ በድንገት ያገኙኝ አራት መፋቂያ አዟሪዎች ቢላቸውን አስሞርደውኛል፡፡ በአብዛኛው በዚህ መልኩ ነው እየተንቀሳቀስኩ የምሰራው፡፡ በስልክ ጠርተው የሚያሰሩኝ በተለይ ባለ ሆቴል ቤት ደንበኞችም አሉኝ፡፡ በቀን ምን ያህል ብር ትሰራለህ? እስከ 200 ብር የምሰራበት ጊዜ አለ። እንዳልኩህ ሞረዱም ቺንጋውም ቶሎ ቶሎ ስለሚቀየር ወጪ አለው፡፡ ቀጣይ የህይወት አላማህ ምንድነው? አሁን ወንድሜም እኔም ተመሳሳይ ሥራ በተለያዩ ቦታዎች እየሰራን ውለን ማታ እንገናኛለን፡፡ የመሞረዱን አገልግሎት በዲናሞ ለመሥራት እያሰብን ነው፡፡ ይህንን ሥራ እየሰራን ገጠር ያሉ ቤተሰቦቻችንን እንረዳለን፡፡ ከዚህ የተሻለ በመሥራት ህይወታችንን የመለወጥ አላማ አለን፡፡ የእረፍት ጊዜህ መቼ ነው? ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ቀኑን ሙሉ እሰራለሁ፡፡ እሁድ የእረፍት ቀኔ ነው፡፡

ኤርትራ ራሷን እያወደመች ነው የኢትዮጵያ ትምህርት ችግሮች ቋንቋና ያለ እቅደ መስፋፋት ናቸው

            ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ በስዊድን አገር በኡፕስላ ዩኒቨርሲቲ የዘመናዊ ታሪክ ፕሮፌሰር ናቸው፡፡ ፕሮፌሰሩ በኢትዮጵያ ትምህርት ላይ ከፍተኛ ምርምሮችን ያደረጉ፣ በመስኩም የታወቁ ምሁር ሲሆኑ ከከዓምናው ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ተጋባዥ ፕሮፌሰር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ1947 በአስመራ ከተማ ተወልደው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአስመራ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ ተከታትለዋል፡፡ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከአስመራ ዩኒቨርሲቲ በህግ አግኝተዋል፡፡ ከ1972 እስከ 1974 በአስመራ ዩኒቨርሲቲ ያስተማሩት ፕሮፌሰር ተከስተ፤ በለንደን ዩኒቨርሰቲ ከ“ስኩል ኦፍ ኦሪየንታል ኤንድ አፍሪካ ስተዲስ” ማስተርስ ድግሪ ያላቸውን ያገኙ ሲሆን ዶክትሬታቸውን ከስዊድን አገር ኡፕስላ ዩኒቨርስቲ በታሪክ ትምህርት ሰርተዋል፡፡ የኤርትራን ወቅታዊ ሁኔታ እንዴት ይገልፁታል? እኔ የኤርትራን ጉዳይ መከታተል ካቆምኩ አስራ ሶስት አመት ሊሆነኝ ነው፡፡ ምክንያቱም ልለው የምችለውን ሁሉ ብያለሁ፡፡

“Brothers at war” በሚል ከአንድ የኖርዌይ ተወላጅ ጋር በመሆን በፃፍነው መጽሐፍ፤ የኢትዮጵያና የኤርትራ ጦርትነት የወንድማማችነት ጦርነት ነው፤ ችግሩን ለመፍታት ሁለቱ አገሮች ወንድማማችነታቸውን ማመን አለባቸው ብለን ደምድመናል፡፡ ከዛ በኋላ ምንም ሠላም አልተገኘም፤ በኔ አስተያየት የሚገኝም አይመስለኝም፡፡ እስከአሁን በኢትዮጵያም ሆነ በኤርትራ ወንድማማችነቱን ማመን ላይ አልተደረሰም፡፡ የሁለቱ አገራት የወደፊት ግንኙነት ምን የሚሆን ይመስልዎታል? የኤርትራን ጉዳይ ማጥናት የተውኩት ተገድጄ አይደለም፡፡ በአንድ በኩል በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉ ነገሮች በጣም በጎ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ብዙ ለውጥ እየተካሄደ ነው የሚል አቋም ስላለኝ ሲሆን በሌላ በኩል የኤርትራ ጉዳይ አልቆለታል ብዬ ስላመንኩ ነው፡፡ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ኤርትራ ራሷን በራሷ እያወደመች ነው፡፡ ኤርትራ ምንም ተስፋ የላትም ብዬ አምናለሁ፡፡

ወደ ጥያቄሽ ስመለስ… የኤርትራና የኢትዮጵያ ሁኔታ እንዴት ይቀጥላል ለሚለው በኔ አስተያየት ከዚህ በኋላ ጦርነት አይካሄድም። ኤርትራ ግን የሶማሊያን አይነት የምትሆንበት፣ በአንድ ልትመራ ወደማትችልበት ደረጃ ልትደርስ ትችላለች ብዬ አምናለሁ፡፡ ከኢሳያስ አፈወርቂ በኋላ ኤርትራ ሶማሊያን ትሆናለች በሚል የሚሰጡ አስተያየቶችን ይቀበላሉ ማለት ነው? አዎ፡፡ ኢሳያስ እስካለ እሱ የፈጠረው ስርዓት ይቀጥላል፡፡

የአለም አቀፉ ማህበረሰብ አቋም እና የኢትዮጵያ መንግስት የያዙት አቋምም ለዚህ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ፡፡ ከኢሳያስ በኋላ ግን የኢኮኖሚ ችግር ብቻ ሳይሆን የብሔር ግጭቶች አሉ፡፡ ቆላማው የኤርትራ ክፍል የራሱ አጀንዳ አለው፤ ደገኞቹ ደግሞ እርስበርሳቸው በጣም የተከፋፈሉ ናቸው፡፡ ይህን መያዝ የሚችለው ኢሳያስ ብቻ ነው፡፡ ከሱ በኋላ አገሪቱን አንድ አድርጐ ወደፊት ሊያራምድ የሚቻል ይመጣል ብዬ አላምንም፡፡ የኤርትራ ጥያቄ ለምርጫ በቀረበበት ወቅት ከነበሩ አማራጮች ዋነኞቹ፤ መገንጠል፣ በፌዴሬሽን መቆየት እና አንድነት የሚሉ ነበሩ፡፡ በውድም ይሁን በግድ ሁሉም አማራጮች ተግባራዊ ሆነዋል፡፡ ኤርትራ ከተገነጠለች 23 አመት ሊሆናት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት አንድነት የሚለው አቋም ቅሪት አለ ወይስ ሙሉ በሙሉ ተሸርሽሯል? የደጋው ኤርትራ ባህል በመሠረቱ ኢትዮጵያዊነቱን እንደያዘ ነው፡፡ ኢሳያስ ስልጣን እንደያዘ በሶስተኛ አመቱ ሆላንድ መጥቶ ባደረገው ውይይት፤ እኔም እድሉን አግኝቼ ሰምቼዋለሁ፡፡ እኛ ሠላሳ አመት ሙሉ ታግለን ብዙ ሰው ሞቶብን፣ ባለፉት ሁለት አመታት ውስጥ የኤርትራ ህዝብ የከፈልነውን መስዋዕትነት ረስቶ ከኢትዮጵያ ጋር ወዲያ ወዲህ ይላል ብሎ ተናገረ፡፡ ኤርትራ ነፃ ከወጣች ጊዜ ጀምሮ እስከ ጦርነቱ ድረስ የኤርትራ ህዝብ ከኢትዮጵያ ተለይተናል የሚል ብዙ ስሜት አልነበረውም፡፡ ደርግ መሸነፉ ላይ ነበር እንጂ ከኢትዮጵያ ጋር የመለየቱ ብዙ ግንዛቤ አልነበረውም፡፡ ጦርነቱ ሲጀመር ስሜቱ መቀዛቀዙን መናገር ይችላል፡፡

ሌላው በደጋው ኤርትራ ያለው ትግርኛ ተናጋሪ ከጣሊያን ጊዜ የጀመረ የገዢና የተገዢ ግንኙነት ነበረው፡፡ እኛን ጣልያን ነው የገዛን በሚል፣ ትግራይ ያሉትን ትግሪኛ ተናጋሪዎች “እናንተ ከአዲግራት፣ ከመቀሌ፣ ከአድዋ የምትመጡ…” የሚል ነገር ነበር፡፡ ከጦርነቱ በኋላ የትግራይ ህዝብ የራሱን ማንነት ኢኮኖሚ በማሻሻል ላይ ስለሚገኝ በነዚህ ሁለት ትግሪኛ ተናጋሪዎች መካከል ያለው ፉክክር ማን ትግሬን ይወክላል የሚል ነው፡፡ ይህ ለጊዜው ችግር ሊፈጥር ይችላል፤ ግን እኔ እስከምረዳው ድረስ ኢትዮጵያዊነት ስሜት፣ ባህል፣ አስተሳሰብ አለ የምንል ከሆነ በደጋማው ኤርትራ አሁንም አለ። ከዛ ደግሞ ከአፋር ጋር ያለውን ትስስር ማየት ይቻላል፡፡ በኤርትራ ያሉ ቢለኖች አገዎች እንደሆኑ አይጠራጠሩም፤ አሁን ባለው ሁኔታ ምንም ማድረግ አይችሉም፡፡ ኩናማዎችንም ካየሽ ተመሳሳይ ነው፡፡ ወቅታዊውን የአፍሪካ ቀንድ ሁኔታ እንዴት ይገልፁታል? በአፍሪካ ቀንድ የኢትዮጵያ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ሶማሊያ እና ኢትዮጵያን ካየን፣ ለሁለቱም የሚጠቅማቸው የሶማሊያ አንድ መሆን ነው፡፡ አሁን ያለው ሁለት ሶማሊያ በኔ አስተያየት ረጅም የሚጓዝ አይደለም፡፡ ከጥቅም አንፃር ካየነውም፣ ለኢትዮጵያም ሆነ ለሶማሊያ አይጠቅምም፡፡ በኤርትራና በኢትዮጵያ በኩል ስናየው፣ ኤርትራ የምትፈልገው ድንበር ሊኖር አይችልም፡፡ ይህን ደግሞ ሁለቱም አገሮች ያውቁታል፡፡

የኤርትራ ሁኔታ ከኢሳያስ በኋላ አዲስ መልክ ይይዛል፡፡ በአዲሱ ሁኔታ የኢትዮጵያ ሚና ምን ሊሆን እንደሚችል በሚገባ ማጤን ያስፈልጋል፡፡ የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ጥቅም ለመጪው ሁለት መቶ ሶስት መቶ አመት ሊያራምድ የሚችል ሆኖ መቀረፅ ይገባዋል፡፡ የኢትዮጵያን የፌደራል አወቃቀር እንዴት ያዩታል? አወቃቀሩ በፌደራል መሆኑ ጥሩ ነው፡፡ በብሔር መሆኑ ግን መጥፎ ነው፡፡ የኢህአዴግ መንግስት ያደረገው ትልቁ ስህተት ነው፡፡ ፌደራል ስርአት በፊትም የነበረ ነው፡፡ የኢትዮጵያን የኋላ ታሪክ ካየሽ የፌደራል አወቃቀር አዲስ አይደለም፡፡ ንጉሠ ነገስት ስንል እኮ ንጉሶች አሉ፡፡ ከበላያቸው ንጉሠነገስት አለ ማለት ነው፡፡ አካባቢያዊ ፌደራሊዝም ነበር፡፡ የኤርትራ ህዝብ አሁን ያሉበትን የነፃነት ሁኔታ ከቀድሞው ጋር ሲያስተያዩት ምን ትርጉም ይሰጥዎታል? እኔ እኮ በመጀመሪያም ኤርትራውያኖች ከማን ነው የሚገነጠሉት የሚል አቋም ነው ያለኝ። ማነው ከማን የሚገነጠለው? የደቡብ ወይም የኦሮሞ ህዝቦች እንገነጠላለን ቢሉ ኖሮ ምክንያት ነበራቸው፡፡ የኤርትራ የነፃነት ጥያቄ በተነሳበት ወቅት ኤርትራውያኑና ከላይ የጠቀስኳቸው ህዝቦች በኢትዮጵያ ውስጥ ያገኙትን እድል (Comparative advantage) ስናይ፣ ኤርትራውያኑ በጣም ተጠቃሚ ነበሩ፡፡ (በጣሊያን፣ በእንግሊዝ፣ በፌዴሬሽኑ ዘመን) በ1960ዎቹ የአዲስ አበባ ሀብታሞቹ እነሱ ነበሩ። በትምህርት መስክ ሃያ አምስት በመቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዎች ኤርትራውያን ነበሩ። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችንም ካየሽ 25 በመቶ የሚሆኑት ኤርትራውያን ነበሩ፡፡ ከተማረው ሰላሳ አምስት በመቶው ክፍል ኤርትራውያን ነበሩ፡፡

ይህን እድል ያገኙ ሰዎች ከኢትዮጵያ እንገነጠላለን ሲሉ ምክንያቱን ለማግኘት አስቸጋሪ ነው፡፡ ምንም ምክንያት አልነበራቸው፡፡ ለነፃነት የተደረገው እንቅስቃሴ 30 አመት ቢፈጅም ስልሳ ሺህ ሰው ቢሞትም በቂ ምክንያት አልነበረውም። የኔ ጥናት የጣልያን ቅኝ አገዛዝ በኤርትራ የሚል ነው። እንዲገባኝ ሞክሬያለሁ፡፡ ኤርትራ ከኢትዮጵያ መገንጠል እንዳለበት የሚያሳይ ምንም ነጥብ አላገኘሁም፡፡ ነፃ ወጣን አሉ፡፡ ሁለት አመት ሳይቆዩ እኛ የታገልነው ለነፃነት ብቻ አይደለም፤ የኛ ዕድል ከኢትዮጵያ ጋር ነው ማለት ጀመሩ፡፡ ይህን የሚሉት ተገደው ነው፤ ምክንያቱም የኤርትራ ኢኮኖሚ ከኢትዮጵያ ተገንጥሎ በራሱ ሊቆም የሚችል አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ ልዩ አገር ነች፤ ነፃነቷን ጠብቃ የቆየች አገር ናት፡፡ የኤርትራ ቴሌቪዥን በቅርቡ “Ancient Eritreans” (የጥንት ኤርትራውያን) የሚል ዶክመንተሪ አቅርቦ ነበር፡፡ አይተውታል? (ረጅም ሳቅ) አላየሁትም፡፡ ግን ምንም አዲስ ነገር አይፈጥርም፡፡ ወጣቶቹ ኢትዮጵያን አያውቋትም፤ ነገር ግን መንግስት የሚያደርገው አንድ ነገር ነው፣ ህዝቡ የሚያስበው ሌላ ነገር ነው፡፡

መንግስት በቴሌቪዥን የሚየሳየውና ህዝቡ የሚመኘውና የሚያስበው ሌላ ነው፡፡ እስከቅርብ ጊዜ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከኢትዮጵያ ብትለያይም በድብቅ ወጣቶቻቸውን ለትምህርት ወደ ቤጌምድር (ጐንደር) ይልኩ ነበር፡፡ የኢሳያስን መረጃ በማየት ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም፡፡ ኤርትራዊውን ማን አገኘው፡፡ የተለየን ነን የሚል አቋም የት ነው ያለው? በኤርትራ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ምን ያህል አለ ለሚለው መልስ ለማግኘት ድንበሩ መፍረስ አለበት፡፡ ለሁለቱ ህዝቦች መፍትሔ የሚሆነው በኤርትራ በኩል እየተጠየቀ ያለው ድንበር ሲሰመር ሳይሆን ከደርግ ሽንፈት በኋላ የተሰመረው መስመር ሲፈርስ ነው፡፡ ትናንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋ፣ እውቀት እና የጋራ ህልውና በሚል የውይይት መነሻ ጥናት አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ትምህርት ላይ ጥናቶችን አድርገዋል፡፡ ዕይታዋ ምንድን ነው? ዋና ጥናቴ እሱ ነው፡፡ ትምህርት በጣም ተዳክሟል፡፡ የተዳከመው በሁለት ምክንያት ነው ብዬ አስቀምጣለሁ፡፡ አንዱ ያለዕቅድ መስፋፋቱ ነው። የሚፈለጉ ህንፃዎች፣ አስተማሪዎች፣ መፃሕፍቶች ሳይሟሉ እንዲሁ ሠፍቷል፡፡ ሌላው ዋነኛ ምክንያት የቋንቋ ጉዳይ ነው፡፡ እንግሊዝኛ ቋንቋ አያዋጣንም፡፡ በራስ ቋንቋ መማር የህልውናና የመበት ጥያቄ ነው፡፡ ዜግነትዎ ከየትኛው ነው? ስዊድናዊ ነኝ፡፡

የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ አለምን ከዳር ዳር በሚያዳርስ የመረጃ መረብ፣ የውጭ ዜጎችን (የጠቅላይ ሚኒስትሮችና የፕሬዚዳንቶች ጭምር) የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን የቱን ያህል በስፋት እንደሚሰልል ሲታይ ጉድ ያሰኛል። በእርግጥ የስለላ ተቋሙ የአሜሪካ ዜጐችን በዘፈቀደ አልሰልልም ብሏል፡፡ የዜጐች የግል ሕይወትና የመልእክት ልውውጥ በመንግስት መነካት እንደሌለበት በአገሪቱ ሕገመንግስት ታውጇላ። የዜጐችን የስልክ እና የኢሜይል መልእክት የምበረብረው፣ በተጠርጣሪዎች ላይ በማተኮርና ፍርድ ቤትን በማስፈቀድ ብቻ ነው ይላል - የአሜሪካ የስለላ ተቋም። ታዲያ “ፍርድ ቤት” ሲባል፣ የወትሮው አይነት አይደለም። በሚስጥር የሚሰራ ልዩ ፍርድ ቤት ነው። ማዘዣ ወረቀቱም በሚስጥር የሚጠበቅ ስለሆነ፣ ከጊዜ በኋላ የፍርድ ቤቱን ውሳኔዎችና ትዕዛዞች መመርመር ያስቸግራል። ፍርድ ቤትን ማስፈቀድ በኢትዮጵያ አይሰራም በእውነቱ፣ እንዲህ አይነቱ ድብቅ የፍርድ ቤት አሰራር፣ ከታላቋ የነፃነት አገር (ከአሜሪካ) የሚጠበቅ አይደለም።

ለማንኛውም፣ የስለላ ተቋሙ “የፍርድ ቤት” ማዘዣ በማቅረብ ባለፉት አምስት አመታት የተለያዩ መረጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፡፡ ጉግል፣ ያሁ፣ ሆትሜይል፣ ፌስቡክ እንዲሁም ኤቲኤንድ ቲ የመሳሰሉ የኢንተርኔት እና የስልክ ኩባንያዎችም፣ የመቶ ሺ ገደማ ደንበኞች መረጃ ለስለላ ተቋሙ ለማስረከብ መገደዳቸውን ገልፀዋል። ኩባንያዎቹ የሕግ ግዴታ ሆኖባቸው እንጂ፣ የአንድም ሰው መረጃ አሳልፈው መስጠት አይፈልጉም - እንጀራቸው ነዋ። በደንታ ቢስነት የደንበኞችን መረጃ እያወጣ ለመንግስት የሚዘረግፍ ኩባንያ፣ የቱንም ያህል ግዙፍ ቢሆን መንኮታኮቱና በአጭር መቀጨቱ አይቀርም። ደንበኞቹ ይሸሹታል፤ ፊታቸውን ወደ ሌላ አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ በማዞር ጀርባቸውን ሲሰጡት፣ በኪሳራ ይፈራርሳል። ኩባንያዎቹ እንጀራቸውን ማጣት አይፈልጉም፤ እናም በተቻላቸው መጠን የደንበኞቻቸውን መረጃ ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለመንግስት ትልቅ ፈተና መሆናቸው አይገርምም።

በእኛ አገር ግን፣ መንግስት ይሄ ሁሉ ጣጣ አይኖርበትም። የኢንተርኔትና የስልክ አግልግሎት ሁሉ በመንግስት እጅ ነዋ። በፈለገ ጊዜ ባሰኘው መጠን፣ የስልክ ንግግሮችን ሲያዳምጥ ቢያድር፣ የፅሁፍ መልእክቶችን ሲበረብር ቢውል ማንም አያውቅም። ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ይሸሹኛል ብሎ አይሰጋም። ከቴሌ ሸሽተን የት ልንደርስ! ሌላ አማራጭ የለንም። እናም፣ ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞችን መረጃ አሳልፎ ላለመስጠትና ጠብቆ ለመያዝ የሚገፋፋ ጫና የለበትም። በአጭሩ፤ የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኙነታችን በሙሉ በመንግስት እጅ ነው። የሰዎችን የስልክ እና የኢሜይል ግንኙነትን ለመጥለፍ ፖሊስ ፍ/ቤትን ማስፈቀድ እንደማያስፈልገው፣ የፀረ ሽብር ህጉ ይደነግጋል “ሁሉም በእጄ ሁሉም በደጄ” ነው ነገሩ፡፡ በፍ/ቤት ያልተፈቀደ ድብቅ ስለላስ? የአሜሪካ የስለላ ተቋም በ“ፍርድ ቤት” ማዘዣ አማካኝነት የሚሰበስባቸው መረጃዎች አያረኩትም። ተጨማሪ ብዙ መረጃ ለመሰብሰብ፣ በተለያዩ የኢንተርኔትና የስልክ ኩባንያዎች ላይ በድብቅ ስለላ እንደሚያካሂድ ባለፈው ሳምንት የተሰራጩ ዘገባዎች ገልጸዋል።

እንዴት በሉ። የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ ያለ “ፍርድ ቤት” ማዘዣ የጐግል ወይም የማይክሮሶፍት የመረጃ ማዕከላትን መበርበር አይችልም። በድብቅ መሰለልም ቀላል አይሆንለትም። በቴክኖሎጂ የተራቀቁት ኩባንያዎች፣ የየራሳቸው የመረጃ ማዕከላት ላይ ከፍተኛ ጥበቃ ያካሂዳሉ። የመረጃ ማዕከላትን የሚያገናኙ የስልክና የኢንተርኔት ማስተላለፊያ (የፋይበር ኦፕቲክስ) መስመሮችስ? አገር አቋራጭ መስመሮች ላይ፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ ጥበቃ ማካሄድ ከባድ ነው። የስለላ ተቋሙም፣ የኢንተርኔት ኩባንያዎች ዋና ዋና የግንኙነት መስመሮችን በድብቅ በመጥለፍ ነው መረጃዎችን እንደሚሰበስብ የተዘገበው። በእርግጥ፣ በዘገባዎቹ ምክንያት ከፍተኛ ጫና እንደሚደርስበት የተገነዘበው የስለላ ተቋሙ፣ ሳይውል ሳያድር ዘገባዎቹን አስተባብሏል - “የኩባንያዎቹ የመረጃ ማዕከላት ላይ ስለላ አላካሄድኩም” በማለት። “የግንኙነት መስመሮች ላይስ ስለላ አካሂደሃል ወይ?” ተብሎ ሲጠየቅም የተቋሙ ምላሽ ተመሳሳይ ነው። “የመረጃ ማዕከላት ላይ ስለላ አላካሄድኩም” የሚል ሆኗል የተቋሙ ምላሽ፡፡ አጣብቂኝ ውስጥ የገባ ይመስላል፡፡

በአገራችን ግን፣ መንግስት በድብቅ መሰለል አያስፈልገውም፤ ውዝግብና ጭቅጭቅ ውስጥ የሚገባበት ምክንያትም የለም። የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኝነቶቻችንን የሚያከማቹ የመረጃ ማዕከሎች በሙሉ በመንግስት እጅ ናቸው። የስልክ ንግግሮችን ጨምሮ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የምናካሂዳቸው ግንኝነቶችን የሚያመላልሱ ዋና ዋና የመረጃ ማስተላለፊያ (የፋይበር ኦፕቲክስ) መስመሮችም የመንግስት ናቸው። ያሻውን ቢያደርግ ማን ይጠይቀዋል? “1ለ5” ማደራጀት ያልቻሉ፣ ለስለላ ይደክማሉ መቼም፣ የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን እየጠለፈ የሚሰበስበው፣ ማን መቼ ከማን ጋር እንደተገናኘና ምን እንዳወራ ለመሰለል ነው። የኛ አገር መንግስት ግን፣ መረጃ ለመሰብሰብ መባተል አያስፈልገውም። ማን መቼ ከማን ጋር እንደሚገናኝ ለማወቅ አይደክምም። ይልቁንስ፣ በ“1ለ5” አደረጃጀት ማን ከማን ጋር መገናኘት እንዳለበት ትዕዛዝ ያስተላልፋል። በትምህርት ቤትም ሆነ በስራ ቦታ፣ በገጠርም ሆነ በከተማ፣ “1ለ5” እንዲደራጁ የታዘዙ ዜጎች፣ በሳምንት ሁለት ቀን በየትኛው ሰዓት መገናኘት እንዳለባቸው መመሪያ የሚመጣባቸው ከመንግስት አካላት ነው። ተገናኝተው ምን ምን ማውራት እንዳለባቸውም ጭምር ትዕዛዝ ይደርሳቸዋል።

ታዲያ፣ የዜጎችን ህይወት በእጁ አስገብቶ ኑሯቸውን በትዕዛዝ የሚመራ መንግስት፣ ለምን ብሎ ይሰልላቸዋል? የአሜሪካ መንግስት የሰዎችን የመኪናና የአፓርትመንት ኪራይ በድብቅ ለመሰለል ይጣጣራል፡፡ ሰዎች የት እንዳደሩ ወዴት እንደተጓዙ ለማወቅም በስውር ይጣጣራል፡፡ የአገራችን መንግስት ግን ለድብብቆሽ ጊዜ አያጠፋም፡፡ እያንዳንዱ የቤት እና የመኪና አከራይ፣ የየእለቱን መረጃ መዝግቦ፣ በራሱ ወጪ መጥቶ ያስረከበኝ በማለት በኢቲቪ መመሪያ ያስተላልፋል፡፡ አዋጅ ማርቀቅና ማጽደቅ፣ ወይም ደንብ ማዘጋጀት እንኳ አያስፈልገውም፡፡ የዜጐች የመንቀሳቀስ ነፃነት በህገመንግስት በግልጽ እውቅና ቢሰጠውም፤ ሰዎች ከከተማ ከተማ በማታ እንዳይንቀሱ በመግለጫ ተከልክለው የለ! በትራንስፖርት ሚኒስቴር ተግባራዊ የተደረገ “የሰዓት እላፊ” ልንለው እንችላለን፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ ወደ አረብ አገራት መሄድ ተከልክሏል የሚል መግለጫ አውጥቷል፡፡ ህጋዊውን ስርዓት ተከትለው ምዝገባ በማካሄድ በየአመቱ በአማካይ 130ሺ ኢትዮጵያውያን ለስራ ወደ አረብ አገራት ሲሄዱ ቆይተዋል፡፡

በዚህ መሃል ነው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ድንገት ተነስቶ፣ “ጉዳት እንዳይደርስባችሁ ስለምጨነቅላችሁ እንዳትጓዙ አዝዣለሁ” የሚል መግለጫ ያወጣው፡፡ የመንቀሳቀስ ነፃነት የሚባለው የህገመንግስት አንቀጽ የት ደረሰ? የገንዘብ ሚኒስቴርስ፣ “ደሞዛችሁን እንዳታባክኑ ስለምጨነቅላችሁ፣ ግማሽ ደሞዛችሁን እንድትቆጥቡ አዝዣለሁ” ብሎ መግለጫ ማውጣት አይችልም? “በራሴ ደሞዝና ገቢ መንግስት ምን አገባው” ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ በእርግጥም የንብረት ባለቤትነትና ነፃነት የሚሉ የህገመንግስት አንቀፆች አሉ፡፡ ግን በርካታ አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት፣ ለቁጠባ ገንዘብ ለማስቀመጥ እንደሚገደዱ አታውቁም? የግል ባንኮችም፣ በየአመቱ ከሚሰጡት የብድር መጠን ከሩብ በላይ የሚሆነውን የመንግስት ቦንድ በመግዛት እንዲቆጥቡ ግዴታ ከተጣለባቸው ሁለት አመት አልፏቸዋል፡፡ በአጭሩ፣ መንግስት የዜጐችን እንቅስቃሴና የገንዘብ ልውውጥን ለመሰለል የሚደክምበት ምክንያት የለም፡፡

በየትኛው ሰዓት እና ወዴት አገር መጓዝ እንደምችል፣ ከደሞዛችን ምን ያህል መቆጠብና ለአስቤዛ እንደሚፈቀድልን ወይም እንደማይፈቀድልን በመግለጫ ማዘዝ እየቻለ፣ መንግስት የስለላ ጣጣ ውስጥ መግባት አይኖርበትም፡፡ የትምህርት ቤት ምዝገባና የስራ ስምሪትን፣ የሸቀጦች ግዢና ሽያጭን በተመለከተ መረጃ ለመሰብሰብ እነ አሜሪካ መከራቸውን ሊያዩ ይችላሉ፡፡ የአገራችን መንግስት ግን፣ ተማሪዎች የትኛው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ መማር፣ በየትኛው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ መለማመድ እንደሚችሉ ምደባ ማካሄድና መወሰን ይችላል፡፡ የሸቀጦችን ግዢ እና ሽያጭን ከነዋጋ ተመናቸው በመግለጫ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፍም እናውቃለን፡፡ ስኳርና ዘይት በጅምላ የሚከፋፈለው ለሸማቾች ማህበር ብቻ ነው ተባለ፡፡ ደግሞም በስኳርና በዘይት ብቻ አይደለም የዋጋ ተመን የወጣብን፡፡ የበግ እና የፍየል ቆዳ ከ40 ብር በላይ ማንም መሸጥ የለበትም የሚል መግለጫም ሰምተናል፡፡

አሁን ደግሞ የእንስሳትና የቆዳ ገበያ ውስጥ እነማን ሻጭ እና ገዢ ለመሆን እንደሚፈቀድላቸው የሚደነግግ ህግ ተዘጋጅቷል፡፡ ታዲያ መንግስት ለምን ሲባል፣ የስለላ ጣጣ ውስጥ ይገባል፤ ሁሉም በእጁ ሁሉም በደጁ፡፡ ዜጎች የሕይወታቸው ብቸኛ ባለቤት ሆነው እንደየፍላጎታቸው ካሰኛቸው ሰው ጋር መገናኘትና መደራጀት፣ መስራትና መገበያየት ሲችሉ፣ ኑሯቸውን በየራሳቸው የግል ፈቃድ በነፃነት እየመሩ፣ እንደየሃሳባቸው ያመኑበትን ነገር መናገርና መፃፍ ሲችሉ… ያኔ፣ “ማን ከማን ጋር እየተገናኘ ይሆን? ማን ምን እያወራ ይሆን?” ብሎ መሰለል ወግ ነው። ዜጎችን መሰለል፣ ተገቢና ጥሩ ስራ ባይሆንም፣ “ትርጉም” ይኖረዋል። የእያንዳንዱን ሰው ገመና ለማወቅ የሚደረግ ስለላ ነዋ። የዜጎች ግንኙነት ከመንግስት በሚመጣ የ“1ለ5” አደረጃጀት የሚታዘዝ፣ የዜጎች ወሬ ከመንግስት በሚመጣ “አጀንዳ” የሚመራ፣ የዜጐች ስራ እና ግብይት በመንግስት የስምሪትና የተመን መግለጫ የሚቦካ የሚከካ ሲሆን ግን፣ ስለላ የሚባል ነገር ጨርሶ “ትርጉም” ያጣል። የዜጎች ሕይወትና ኑሮ በመንግስት እጅ ከሆነ፣ ለስለላ የሚያነሳሳ “ገመና” ከየት ይመጣል?

የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ አለምን ከዳር ዳር በሚያዳርስ የመረጃ መረብ፣ የውጭ ዜጎችን (የጠቅላይ ሚኒስትሮችና የፕሬዚዳንቶች ጭምር) የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን የቱን ያህል በስፋት እንደሚሰልል ሲታይ ጉድ ያሰኛል። በእርግጥ የስለላ ተቋሙ የአሜሪካ ዜጐችን በዘፈቀደ አልሰልልም ብሏል፡፡ የዜጐች የግል ሕይወትና የመልእክት ልውውጥ በመንግስት መነካት እንደሌለበት በአገሪቱ ሕገመንግስት ታውጇላ። የዜጐችን የስልክ እና የኢሜይል መልእክት የምበረብረው፣ በተጠርጣሪዎች ላይ በማተኮርና ፍርድ ቤትን በማስፈቀድ ብቻ ነው ይላል - የአሜሪካ የስለላ ተቋም። ታዲያ “ፍርድ ቤት” ሲባል፣ የወትሮው አይነት አይደለም። በሚስጥር የሚሰራ ልዩ ፍርድ ቤት ነው። ማዘዣ ወረቀቱም በሚስጥር የሚጠበቅ ስለሆነ፣ ከጊዜ በኋላ የፍርድ ቤቱን ውሳኔዎችና ትዕዛዞች መመርመር ያስቸግራል። ፍርድ ቤትን ማስፈቀድ በኢትዮጵያ አይሰራም በእውነቱ፣ እንዲህ አይነቱ ድብቅ የፍርድ ቤት አሰራር፣ ከታላቋ የነፃነት አገር (ከአሜሪካ) የሚጠበቅ አይደለም።

ለማንኛውም፣ የስለላ ተቋሙ “የፍርድ ቤት” ማዘዣ በማቅረብ ባለፉት አምስት አመታት የተለያዩ መረጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፡፡ ጉግል፣ ያሁ፣ ሆትሜይል፣ ፌስቡክ እንዲሁም ኤቲኤንድ ቲ የመሳሰሉ የኢንተርኔት እና የስልክ ኩባንያዎችም፣ የመቶ ሺ ገደማ ደንበኞች መረጃ ለስለላ ተቋሙ ለማስረከብ መገደዳቸውን ገልፀዋል። ኩባንያዎቹ የሕግ ግዴታ ሆኖባቸው እንጂ፣ የአንድም ሰው መረጃ አሳልፈው መስጠት አይፈልጉም - እንጀራቸው ነዋ። በደንታ ቢስነት የደንበኞችን መረጃ እያወጣ ለመንግስት የሚዘረግፍ ኩባንያ፣ የቱንም ያህል ግዙፍ ቢሆን መንኮታኮቱና በአጭር መቀጨቱ አይቀርም። ደንበኞቹ ይሸሹታል፤ ፊታቸውን ወደ ሌላ አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ በማዞር ጀርባቸውን ሲሰጡት፣ በኪሳራ ይፈራርሳል። ኩባንያዎቹ እንጀራቸውን ማጣት አይፈልጉም፤ እናም በተቻላቸው መጠን የደንበኞቻቸውን መረጃ ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለመንግስት ትልቅ ፈተና መሆናቸው አይገርምም።

በእኛ አገር ግን፣ መንግስት ይሄ ሁሉ ጣጣ አይኖርበትም። የኢንተርኔትና የስልክ አግልግሎት ሁሉ በመንግስት እጅ ነዋ። በፈለገ ጊዜ ባሰኘው መጠን፣ የስልክ ንግግሮችን ሲያዳምጥ ቢያድር፣ የፅሁፍ መልእክቶችን ሲበረብር ቢውል ማንም አያውቅም። ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ይሸሹኛል ብሎ አይሰጋም። ከቴሌ ሸሽተን የት ልንደርስ! ሌላ አማራጭ የለንም። እናም፣ ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞችን መረጃ አሳልፎ ላለመስጠትና ጠብቆ ለመያዝ የሚገፋፋ ጫና የለበትም። በአጭሩ፤ የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኙነታችን በሙሉ በመንግስት እጅ ነው። የሰዎችን የስልክ እና የኢሜይል ግንኙነትን ለመጥለፍ ፖሊስ ፍ/ቤትን ማስፈቀድ እንደማያስፈልገው፣ የፀረ ሽብር ህጉ ይደነግጋል “ሁሉም በእጄ ሁሉም በደጄ” ነው ነገሩ፡፡ በፍ/ቤት ያልተፈቀደ ድብቅ ስለላስ? የአሜሪካ የስለላ ተቋም በ“ፍርድ ቤት” ማዘዣ አማካኝነት የሚሰበስባቸው መረጃዎች አያረኩትም። ተጨማሪ ብዙ መረጃ ለመሰብሰብ፣ በተለያዩ የኢንተርኔትና የስልክ ኩባንያዎች ላይ በድብቅ ስለላ እንደሚያካሂድ ባለፈው ሳምንት የተሰራጩ ዘገባዎች ገልጸዋል።

እንዴት በሉ። የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ ያለ “ፍርድ ቤት” ማዘዣ የጐግል ወይም የማይክሮሶፍት የመረጃ ማዕከላትን መበርበር አይችልም። በድብቅ መሰለልም ቀላል አይሆንለትም። በቴክኖሎጂ የተራቀቁት ኩባንያዎች፣ የየራሳቸው የመረጃ ማዕከላት ላይ ከፍተኛ ጥበቃ ያካሂዳሉ። የመረጃ ማዕከላትን የሚያገናኙ የስልክና የኢንተርኔት ማስተላለፊያ (የፋይበር ኦፕቲክስ) መስመሮችስ? አገር አቋራጭ መስመሮች ላይ፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ ጥበቃ ማካሄድ ከባድ ነው። የስለላ ተቋሙም፣ የኢንተርኔት ኩባንያዎች ዋና ዋና የግንኙነት መስመሮችን በድብቅ በመጥለፍ ነው መረጃዎችን እንደሚሰበስብ የተዘገበው። በእርግጥ፣ በዘገባዎቹ ምክንያት ከፍተኛ ጫና እንደሚደርስበት የተገነዘበው የስለላ ተቋሙ፣ ሳይውል ሳያድር ዘገባዎቹን አስተባብሏል - “የኩባንያዎቹ የመረጃ ማዕከላት ላይ ስለላ አላካሄድኩም” በማለት። “የግንኙነት መስመሮች ላይስ ስለላ አካሂደሃል ወይ?” ተብሎ ሲጠየቅም የተቋሙ ምላሽ ተመሳሳይ ነው። “የመረጃ ማዕከላት ላይ ስለላ አላካሄድኩም” የሚል ሆኗል የተቋሙ ምላሽ፡፡ አጣብቂኝ ውስጥ የገባ ይመስላል፡፡

በአገራችን ግን፣ መንግስት በድብቅ መሰለል አያስፈልገውም፤ ውዝግብና ጭቅጭቅ ውስጥ የሚገባበት ምክንያትም የለም። የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኝነቶቻችንን የሚያከማቹ የመረጃ ማዕከሎች በሙሉ በመንግስት እጅ ናቸው። የስልክ ንግግሮችን ጨምሮ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የምናካሂዳቸው ግንኝነቶችን የሚያመላልሱ ዋና ዋና የመረጃ ማስተላለፊያ (የፋይበር ኦፕቲክስ) መስመሮችም የመንግስት ናቸው። ያሻውን ቢያደርግ ማን ይጠይቀዋል? “1ለ5” ማደራጀት ያልቻሉ፣ ለስለላ ይደክማሉ መቼም፣ የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን እየጠለፈ የሚሰበስበው፣ ማን መቼ ከማን ጋር እንደተገናኘና ምን እንዳወራ ለመሰለል ነው። የኛ አገር መንግስት ግን፣ መረጃ ለመሰብሰብ መባተል አያስፈልገውም። ማን መቼ ከማን ጋር እንደሚገናኝ ለማወቅ አይደክምም። ይልቁንስ፣ በ“1ለ5” አደረጃጀት ማን ከማን ጋር መገናኘት እንዳለበት ትዕዛዝ ያስተላልፋል። በትምህርት ቤትም ሆነ በስራ ቦታ፣ በገጠርም ሆነ በከተማ፣ “1ለ5” እንዲደራጁ የታዘዙ ዜጎች፣ በሳምንት ሁለት ቀን በየትኛው ሰዓት መገናኘት እንዳለባቸው መመሪያ የሚመጣባቸው ከመንግስት አካላት ነው። ተገናኝተው ምን ምን ማውራት እንዳለባቸውም ጭምር ትዕዛዝ ይደርሳቸዋል።

ታዲያ፣ የዜጎችን ህይወት በእጁ አስገብቶ ኑሯቸውን በትዕዛዝ የሚመራ መንግስት፣ ለምን ብሎ ይሰልላቸዋል? የአሜሪካ መንግስት የሰዎችን የመኪናና የአፓርትመንት ኪራይ በድብቅ ለመሰለል ይጣጣራል፡፡ ሰዎች የት እንዳደሩ ወዴት እንደተጓዙ ለማወቅም በስውር ይጣጣራል፡፡ የአገራችን መንግስት ግን ለድብብቆሽ ጊዜ አያጠፋም፡፡ እያንዳንዱ የቤት እና የመኪና አከራይ፣ የየእለቱን መረጃ መዝግቦ፣ በራሱ ወጪ መጥቶ ያስረከበኝ በማለት በኢቲቪ መመሪያ ያስተላልፋል፡፡ አዋጅ ማርቀቅና ማጽደቅ፣ ወይም ደንብ ማዘጋጀት እንኳ አያስፈልገውም፡፡ የዜጐች የመንቀሳቀስ ነፃነት በህገመንግስት በግልጽ እውቅና ቢሰጠውም፤ ሰዎች ከከተማ ከተማ በማታ እንዳይንቀሱ በመግለጫ ተከልክለው የለ! በትራንስፖርት ሚኒስቴር ተግባራዊ የተደረገ “የሰዓት እላፊ” ልንለው እንችላለን፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ ወደ አረብ አገራት መሄድ ተከልክሏል የሚል መግለጫ አውጥቷል፡፡ ህጋዊውን ስርዓት ተከትለው ምዝገባ በማካሄድ በየአመቱ በአማካይ 130ሺ ኢትዮጵያውያን ለስራ ወደ አረብ አገራት ሲሄዱ ቆይተዋል፡፡

በዚህ መሃል ነው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ድንገት ተነስቶ፣ “ጉዳት እንዳይደርስባችሁ ስለምጨነቅላችሁ እንዳትጓዙ አዝዣለሁ” የሚል መግለጫ ያወጣው፡፡ የመንቀሳቀስ ነፃነት የሚባለው የህገመንግስት አንቀጽ የት ደረሰ? የገንዘብ ሚኒስቴርስ፣ “ደሞዛችሁን እንዳታባክኑ ስለምጨነቅላችሁ፣ ግማሽ ደሞዛችሁን እንድትቆጥቡ አዝዣለሁ” ብሎ መግለጫ ማውጣት አይችልም? “በራሴ ደሞዝና ገቢ መንግስት ምን አገባው” ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ በእርግጥም የንብረት ባለቤትነትና ነፃነት የሚሉ የህገመንግስት አንቀፆች አሉ፡፡ ግን በርካታ አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት፣ ለቁጠባ ገንዘብ ለማስቀመጥ እንደሚገደዱ አታውቁም? የግል ባንኮችም፣ በየአመቱ ከሚሰጡት የብድር መጠን ከሩብ በላይ የሚሆነውን የመንግስት ቦንድ በመግዛት እንዲቆጥቡ ግዴታ ከተጣለባቸው ሁለት አመት አልፏቸዋል፡፡ በአጭሩ፣ መንግስት የዜጐችን እንቅስቃሴና የገንዘብ ልውውጥን ለመሰለል የሚደክምበት ምክንያት የለም፡፡

በየትኛው ሰዓት እና ወዴት አገር መጓዝ እንደምችል፣ ከደሞዛችን ምን ያህል መቆጠብና ለአስቤዛ እንደሚፈቀድልን ወይም እንደማይፈቀድልን በመግለጫ ማዘዝ እየቻለ፣ መንግስት የስለላ ጣጣ ውስጥ መግባት አይኖርበትም፡፡ የትምህርት ቤት ምዝገባና የስራ ስምሪትን፣ የሸቀጦች ግዢና ሽያጭን በተመለከተ መረጃ ለመሰብሰብ እነ አሜሪካ መከራቸውን ሊያዩ ይችላሉ፡፡ የአገራችን መንግስት ግን፣ ተማሪዎች የትኛው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ መማር፣ በየትኛው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ መለማመድ እንደሚችሉ ምደባ ማካሄድና መወሰን ይችላል፡፡ የሸቀጦችን ግዢ እና ሽያጭን ከነዋጋ ተመናቸው በመግለጫ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፍም እናውቃለን፡፡ ስኳርና ዘይት በጅምላ የሚከፋፈለው ለሸማቾች ማህበር ብቻ ነው ተባለ፡፡ ደግሞም በስኳርና በዘይት ብቻ አይደለም የዋጋ ተመን የወጣብን፡፡ የበግ እና የፍየል ቆዳ ከ40 ብር በላይ ማንም መሸጥ የለበትም የሚል መግለጫም ሰምተናል፡፡

አሁን ደግሞ የእንስሳትና የቆዳ ገበያ ውስጥ እነማን ሻጭ እና ገዢ ለመሆን እንደሚፈቀድላቸው የሚደነግግ ህግ ተዘጋጅቷል፡፡ ታዲያ መንግስት ለምን ሲባል፣ የስለላ ጣጣ ውስጥ ይገባል፤ ሁሉም በእጁ ሁሉም በደጁ፡፡ ዜጎች የሕይወታቸው ብቸኛ ባለቤት ሆነው እንደየፍላጎታቸው ካሰኛቸው ሰው ጋር መገናኘትና መደራጀት፣ መስራትና መገበያየት ሲችሉ፣ ኑሯቸውን በየራሳቸው የግል ፈቃድ በነፃነት እየመሩ፣ እንደየሃሳባቸው ያመኑበትን ነገር መናገርና መፃፍ ሲችሉ… ያኔ፣ “ማን ከማን ጋር እየተገናኘ ይሆን? ማን ምን እያወራ ይሆን?” ብሎ መሰለል ወግ ነው። ዜጎችን መሰለል፣ ተገቢና ጥሩ ስራ ባይሆንም፣ “ትርጉም” ይኖረዋል። የእያንዳንዱን ሰው ገመና ለማወቅ የሚደረግ ስለላ ነዋ። የዜጎች ግንኙነት ከመንግስት በሚመጣ የ“1ለ5” አደረጃጀት የሚታዘዝ፣ የዜጎች ወሬ ከመንግስት በሚመጣ “አጀንዳ” የሚመራ፣ የዜጐች ስራ እና ግብይት በመንግስት የስምሪትና የተመን መግለጫ የሚቦካ የሚከካ ሲሆን ግን፣ ስለላ የሚባል ነገር ጨርሶ “ትርጉም” ያጣል። የዜጎች ሕይወትና ኑሮ በመንግስት እጅ ከሆነ፣ ለስለላ የሚያነሳሳ “ገመና” ከየት ይመጣል?

            ኒውዮርክ ታይምስ ባለፈው መስከረም መግቢያ ላይ እንደዘገበው፣ የአሜሪካ ብሄራዊ የፀጥታ ኤጀንሲ (NSA) በየቀኑ 4 ቢሊዮን የስልክ እና የኢሜይል መረጃዎችን እየመዘገበ ያከማቻል። ዎልስትሪት ጆርናል በበኩሉ፣ NSA በአሜሪካ በየእለቱ በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የኢሜይል ልውውጦች መካከል 75 በመቶ ያህሉን የመከታተል አቅም እንዳለው ገልጿል። ስለላው የስልክ እና የኢሜይል ብቻ ሳይሆን፣ የጉዞና የሆቴል አዳርን፣ የመኪናና የአፓርትመንት ኪራይን ጨምሮ የማያካልለው የህይወት ገጽታ የለም፡፡ የሱፐርማርኬት ሸቀጦች ግዥና ሽያጭን፣ የባንክ ብድርና የገንዘብ ልውውጥን፣ የትምህርት ቤት ምዝገባና የስራ ቅጥርን የሚገልፁ መረጃዎች ሁሉ ስለላ ይካሄድባቸዋል፡፡ የሚያመልጥ ነገር የለም የሞባይል እና የኢንተርኔት ስለላ በእርግጥ፣ “የስልክና የኢንተርኔት ግንኙነቶችን እየተከታተለ መረጃዎችን ይሰበስባል” ማለት፣ “ጆሮውን ደቅኖ ይሰማል፤ አይኑን ተክሎ ይቃኛል፤ በየሴኮንዱም ድምፅና ፅሁፍ፣ ፎቶና ቪዲዮ እየቀረፀ ያከማቻል” ማለት ላይሆን ይችላል።

ስልክ ደውለን ስናነጋግር፣ ሞባይላችን መረጃዎችን ይመዘግብ የለ? የንግግራችንን ድምፅ ባንቀርፀውም እንኳ፣ ወደ የትኛው የስልክ ቁጥር መቼ እንደደወልን ወይም እንደተደወለልን፣ ለምን ያህል ደቂቃ እንዳነጋገርን ማወቅ እንችላለን። እንዲህ አይነቱ መረጃ “ሜታዳታ” ይሉታል። የተቀረፀ ንግግር ደግሞ “ዳታ” ብለው ይጠሩታል። ኮምፒዩተር ላይ ፋይሎችን ስንከፍት የምናገኘውን ድምፅ ወይም ቪዲዮ፣ ፎቶ ወይም ፅሁፍ፣ “ዳታ” ይሉታል። የፋይሎች ስምና አይነታቸውን፣ መጠንና ቦታቸውን፣ መቼ እንደተቀመጡና መቼ እንደተከፈቱ የሚገልፅ የመረጃ ዝርዝር ደግሞ ሜታዳታ ይባላል። የአሜሪካ ብሄራዊ የፀጥታ ኤጀንሲ፣ ዜጎች በስልክ የሚያወሩትን በድምፅ እየቀረፀ፣ በኢሜይል የሚለዋወጡትን ፅሁፍ እየገለበጠ እንደማያከማች ይገልፃል።

“ማን ለማን መቼ ደወለ?፣ ለምን ያህል ደቂቃ አነጋገረ? ማን ለማን መቼ ኢሜይል ላከ?” እንዲህ የመሳሰሉ “ሜታዳታዎችን” ነው የምሰልለው ይላል NSA። ይቅርታ፣ “ሜታዳታዎችንም አከማቻለሁ እንጂ አልሰልልም” ባይ ነው NSA። “መረጃዎችን አከማቻለሁ፤ መረጃዎች ላይ አንዳች ምርመራ ወይም ስለላ የማካሂደው፣ አጠራጣሪ ፍንጭ ሲኖር ብቻ ነው” ይላል - ኤንኤስኤ። ፖፕላር ሳይንስ መጽሔት ሰሞኑን ባወጣው ዘገባው፣ የNSA አሰራር ተራራ በሚያክል የሳር ክምር ውስጥ፣ መርፌ ፈልጎ እንደማግኘት መሆኑን ያስረዳል። በአንድ ሰው ተነስቶ ሺዎችን የሚያዳርስ የስለላ ድር NSA በየእለቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ መረጃዎችን የሚያከማች ቢሆንም፣ ከመረጃው ብዛት የተነሳ እያንዳንዱን እየመዘዘ መመርመር አይችልም። ነገር ግን አቋራጭ ዘዴዎች አሉ። ፍንጮችን በማነፍነፍ ላይ የተመሰረተ ምርመራና ስለላ! የተቋሙ ስለላ እንዴት እንደሚካሄድ ፒኤም መፅሄት ሲያስረዳ፣ አንድ በሽብር ተግባር የሚጠረጠር ተፈላጊ የመን ውስጥ ይኖራል በማለት ይጀምራል።

ተጠርጣሪው ሞኝ ካልሆነ በቀር፣ በቀጥታ አሜሪካ ውስጥ ወደሚገኝ ምልምል አባል ስልክ አይደውልም፣ ኢሜይል አይልክም። ነገር ግን፣ እዚያው የመን ውስጥ፣ የስልክ ወይም የኢሜይል ግንኙነት ማድረጉ አይቀርም። እዚህ ላይ ነው ስለላው የሚጀምረው፡፡ ተጠርጣሪው ለማንና መቼ ደወለ? ለምን ያህል ደቂቃ አነጋገረ? ለእነማን መቼ ኢሜይል ላከ? ከእነማን መቼ ተደወለለት? …. በእነዚህ ሜታዳታዎች አማካኝነት፣ የተጠርጣሪው የግንኙነት መረብ በኮምፒዩተር ይቀናበራል። በዚህ መረብ ውስጥ መቶ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ። ብዙዎቹ ከተጠርጣሪው የሽብር ተግባር ጋር ግንኙነት የሌላቸው የቤተሰብና የዘመድ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፤ በሰፈርና በቢዝነስ የሚተዋወቁም ይኖራሉ። ነገር ግን ከመካከላቸው ውስጥ አንዱ የተጠርጣሪው የሽብር ሴራ ተባባሪ፣ አለቃው ወይም ተላላኪው ሊሆን ይችላል። ግን የትኛው እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ ያስቸግራል። እናም በደፈናው፣ መቶዎቹ ሰዎች በስልክና በኢሜል የሚያደርጉት ግንኙነት እየተመዘገበ በኮምፒዩተር ይቀናበራል - በሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን የሚያካልል ሌላ ሰፊ መረብ ተፈጠረ ማለት ነው። እነዚህ በሺ የሚቆጠሩ ሰዎችስ ከማን ጋር ይደዋወላሉ? ሌላ የተንቦረቀቀ ሦስተኛ መረብ መሆኑ ነው፡፡

በሌላ አነጋገር፣ “የተጠርጣሪው የጓደኛ፣ ጓደኛ፣ ጓደኛ…” እየተባለ የስለላ መረብ ይዘረጋባቸዋል፡፡ እንዲህ በአንድ የመናዊ ተጠርጣሪ ዙሪያ ያጠነጠኑ በርካታ የግንኙነት መረቦች እየተለዩ ክትትል ይደረግባቸዋል። በግንኙነት መረብ ውስጥ ከተካተቱት በአስር ሺ የሚቆጠሩ የስልክ ቁጥሮች መካከል አንዱ ወይም ሁለቱ፣ በሆነ አጋጣሚ ለአንድ የአሜሪካ ነዋሪ ሲደውሉ ነው፣ በNSA ኮምፒዩተሮች ውስጥ “ቀይ መብራት” ብልጭ የሚለው። ግን ምን ዋጋ አለው? ከመካከለኛው ምስራቅ በየጊዜው የሚደወልላቸው የአሜሪካ ነዋሪዎች በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ናቸው። ሁሉንም በተጠርጣሪነት መመርመር አይቻልም። ምን ተሻለ? NSA በየእለቱ መረጃ የሚሰበስበው የስልክና የኢሜይል ግንኙነት ላይ ብቻ አይደለም። የገንዘብ ልውውጦችንም ይመዘግባል፤ “ማን ለማን መቼ ምን ያህል ገንዘብ፣ ጌጣጌጥና ስጦታ አበረከተ?” በየደቂቃውና በየሴኮንዱ መረጃዎች እየተሰበሰቡ ይከማቻሉ። ይህም ብቻ አይደለም። “ማን፣ መቼ፣ ምን፣ ከየት ገዛ?” … በክሬዲትካርድ ከየሱፐርማርኬቱና ከየመደብሩ የተፈፀሙ የግዢ መረጃዎች ይከማቻሉ። የሆቴል እና የአፓርትመንት ክፍያዎችን፣ የትምህርት እና የስልጠና ምዝገባዎችን፣ የአውሮፕላንና የባቡር ትኬቶችን፣ የመኪና ግዢና ኪራይን በተመለከተም መረጃዎች ይሰበሰባሉ።

እነዚህ ሁሉ ይጠናቀራሉ። ግዙፍ ኮምፒዩተሮችና ተዓምረኛ ሶፍትዌሮች በአንድ የመናዊ የሽብር ተጠርጣሪ ዙሪያ የስልክና የኢሜይል ግንኘነቶቹን በመቃኘት የተጀመረው ‘ፍንጭ ፍለጋ’፣ ብቻውን ያን ያህል ጥቅም አይኖረውም፡፡ ከሌሎች መረጃዎች ጋር ሲቀናበር ግን ውጤቱ ለማመን የሚያስቸግር ይሆናል። “አንድ የአሜሪካ ነዋሪ፣ ከመካከለኛው ምስራቅ ስልክ ይደወልለታል” ከሚለው ፍንጭ በተጨማሪ፤ “መኪና መከራየትን የሚያዘወትር ነው ወይ?” ተብሎ ይፈተሻል። ከውጭ አገርስ ገንዘብ ይላክለታል? ተቀጣጣይ ነገሮችን ለመስራት የሚያገለግሉ ሸቀጦችን ከሱፐር ማርኬት ገዝቶ ያውቃል? የአክራሪዎችን ፕሮፓጋንዳ በኢንተርኔት የሚከታተል ወይም የፈንጂ አሰራርን የሚያሳዩ ድረገፆችን መመልከት የሚያበዛ ከሆነም ተጨማሪ ፍንጭ ነው። የጥቃት ኢላማ ናቸው ተብለው ወደሚገመቱ ስፍራዎች በተደጋጋሚ የተጓዘ ወይም በአቅራቢያ አፓርታማ የተከራየ ከሆነም ያስጠረጥራል።

በየጊዜው የትምህርትና የስልጠና ቦታዎችን እየለዋወጠ ከተመዘገበም እንዲሁ! እነዚህ ሁሉ፣ “የአሸባሪዎች ልዩ ባህርይ ናቸው” ተብለው የሚጠቀሱ መለያዎች ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ ብዙዎቹን ነገሮች የሚያሟላ የአሜሪካ ነዋሪ አለ ወይ? እንዲህ አይነት ሰው፣ ያለጥርጥር ለሽብር ጥቃት የተዘጋጀ ሰው ነው። ግን አለ ወይ? ይሄ ነው የ NSA ጥያቄ። NSA አሰስ ገሰሱን ሁሉ እያሰሰ የመረጃ መአት የሚያሰባስበው፣ እንዲህ አይነት ጥያቄዎችን ለመመለስ ነው። በእርግጥ፣ እንደተራራ የገዘፈ የመረጃ ክምር ላይ መቀመጥ ብቻውን በቂ አይደለም። ያን ሁሉ መረጃ በአጭር ጊዜ መፈተሽና ለጥያቄው ምላሽ መስጠት የሚችል የኮምፒዩተር አቅምና ጥበብ ያስፈልጋል። NSA፣ ከመረጃ ክምችት በተጨማሪ፣ መረጃዎችን በፍጥነት ፈትሾና አመሳክሮ፣ አንጥሮና አቀናብሮ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግዙፍ የኮምፒዩተር አቅም አለው። ከሁሉም በላይ ደግሞ፣ የተራቀቁ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች (ሶፍትዌሮች) ባለቤት ነው። ከተራቀቁት ሶፍትዌሮቹ መካከል በአዲስነቱና በውስብስብነቱ የሚጠቀሰው ኤክስኪስኮር (Xkeyscore) የተሰኘው ሶፍትዌር እንደሆነ ዘጋርድያን ጋዜጣ ዘግቧል። ኤክስኪስኮር፣ መረጃዎችን አስሶና ፈልፍሎ፣ ለቅሞና አንጥሮ የማውጣት አቅሙ እጅግ ሃያል ከመሆኑ የተነሳ፣ “ብዙ ያዩና የሚያውቁ የNSA ባለሙያዎች” ሳይቀሩ አስደናቂ ትንግርት እንደሆነባቸው ዘጋርድያን ገልጿል።

ልብወለድ ይመስላል። ነገር ግን፣ በእንግሊዝ የስለላ ድርጅት ስራ ላይ የዋለው ዲሰንት (DScent) የተሰኘ ሶፍትዌር ምን ያህል ስኬታማ እንደሆነ በማየት ማነፃፀር ይቻላል። የእንግሊዙ ሶፍትዌር (ዲሰንት) “ማን፣ ምን አይነት ሸቀጦችን መቼ ሸመተ? ማን፣ መቼ፣ የት የት ቦታ ሄደ?” የሚሉ ጥያቄዎች ላይ በማተኮር ምርመራ የሚያከናውን መሆኑን ፒ ኤም መፅሔት ዘግቧል። ሶፍትዌሩ የሰዎችን የሸቀጥ ግዢና የጉዞ መዳረሻ በመፈተሽ፣ አሸባሪዎችን ለይቶ ማወቅ ይችላል ብሏል መጽሔቱ። ሶፍትዌሩ ሁሉንም አሸባሪዎች ለይቶ ያውቃል ማለት ነው? አይደለም። ነገር ግን፣ አንድ የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ዝግጅት ከሚያካሂዱ አስር አሸባሪዎች መካከል 6ቱን ለይቶ ለማወቅ እንደሚችል በሙከራ ተረጋግጧል ሲል ፒኤም መፅሄት ዘግቧል። የእንግሊዙ የስለላ ድርጅት የሚጠቀምበት ሶፍትዌር (ዲሰንት) ጉደኛ ነው ቢባል የሚበዛበት አይመስልም። የአሜሪካው ኤክስኪስኮር የተሰኘው ሴፍትዌር ደግሞ፤ ከዲሰንት በእጅጉ የላቀ እንደሆነ ተነግሮለታል። ለምሳሌ፣ “ተጠርጣሪው ሰውዬ የጀርመንኛ ቋንቋ የሚናገር የፓኪስታን ነዋሪ እንደሆነ መረጃ ደርሶናል። ሰውዬውን እንዴት ማግኘት እንችላለን?” የሚል ጥያቄ ይነሳል። ኤክስኪስኮር ለዚህ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ መስጠት ይችላል። “አንድ የማይታወቅ ሰው የሆነ አገር ውስጥ፣ ለሽብር ጥቃት የተመረጡ ቦታዎችን በኢንተርኔት ሲቃኝ ነበር። የኢሜይል አድራሻውን ማወቅ እችላለሁ?” … ኤክስኪስኮር አሁንም ፈጣን ምላሽ ያቀርባል። ተአምረኛ ሶፍትዌር ነው። አለምን የሚሸፍን የዘመናችን የስለላ መረብ በኢንተርኔትና በስልክ የሚተላለፉ ድምፆችን፣ ፅሁፎችን፣ ፎቶዎችንንና ቪዲዮዎችን በሙሉ በደፈናው መሰለልና ቀርፆ ማከማቸት አይቻልም።

በመላው አለም የሚመነጨውና የሚሰራጨው የኤሌክትሮኒክስ መረጃ እጅግ ብዙ ነው። በየቀኑ 7.8 ቢሊዮን ጊጋባይት መረጃ ይመነጫል። በየእለቱ የሚመነጨውን ዲጂታል መረጃ ለመቅረፅና ለማከማቸት፣ ምን ያህል ባለ አራት ጊጋባይት ፍላሾች ወይም ዲቪዲዎች እንደሚያስፈልጉ አስቡት። ሁለት ቢሊዮን ፍላሽ! ወይም ሁለት ቢሊዮን የዲቪዲ ዲስኮች! በየቀኑ! 35 ሚሊዮን መፃህፍት ከያዘው ግዙፉ የኮንግረስ ቤተመፃህፍት ጋር ማነፃፀርም ይቻላል። ዲጂታል መረጃዎችን በሙሉ ማከማቸት፣ በየእለቱ ስምንት መቶ ሺ ተጨማሪ ግዙፍ ቤተመፃህፍት እንደመገንባት ነው። ይሄን ሁሉ ጥሬ መረጃ (ዳታ) በየእለቱ መከታተልና ቀርፆ ማከማቸት አይቻልም። የመፃህፍቱን ርዕስ፣ ደራሲ፣ አሳታሚ፣ ወዘተ መዝግቦ ማስቀመጥ ይቀላል - ሜታዳታ መሰብሰብና ማከማቸት እንደሚባለው። NSA ይህንን ያደርጋል - ከአለም ዙሪያ “ሜታዳታ” ይሰበስባል። ወገኖቹ አውሮፓውያን፣ ቀልደኞቹ ራሺያና ቻይና በእርግጥ NSA ሁሉንም አገራት አይሰልልም። በተለይ አፍሪካን ዞር ብሎ የሚያያት አይመስልም። እንኳን የአፍሪካ አገራትን ሊሰልል ይቅርና፣ የምስራቅ አውሮፓ አገራት ላይም እንኳ ብዙ ትኩረት አያደርግም። ዋነኛ ትኩረቶቹ፣ ቻይና፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ኢራን፣ ሶሪያ፣ ፓኪስታንና አፍጋኒስታን የመሳሰሉ አገራት ናቸው - “ለአሜሪካ ደህንነት ስጋት ናቸው” በሚል።

በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ፣ የምዕራብ አውሮፓ አገራት ላይ ያተኩራል - “የአውሮፓ ደህንነት ያሳስበኛል” በሚል። NSA በአውሮፓ አገራት ላይ ስለላ የሚያካሂደው ለወዳጅ አገራት ደህንነት በማሰብ እንደሆነ ቢገልፅም፣ በርካታ የአውሮፓ መንግስታት ቁጣቸውንና ቅሬታቸውን ሲገልፁ ሰንብተዋል። በእርግጥም፣ የጀርመኗ መራሄ መንግስት አንጌላ ሜርከልን ጨምሮ፣ በርካታ የአውሮፓ መሪዎችና ሚኒስትሮች ስልካቸው በNSA መጠለፉ አስገራሚ ነው። የራሺያ እና የቻይና መንግሰታትም በፊናቸው፣ አሜሪካን ለማጥላላት ጥሩ አጋጣሚ አገኘን ብለው ሲተቹ ከርመዋል። እንዲያም ሆኖ፣ የአውሮፓ ባለስልጣናት ቁጣና ቅሬታ፣ ከአስመሳይነት ተለይቶ እንደማይታይ የዘገበው ዎልስትሪት ጆርናል፣ ከቻይናና ከራሺያ የሚሰነዘረው ትችትም አስቂኝ እንደሆነ ይገልፃል። እንዴት በሉ። በኒው ዮርኩ የተባበሩት መንግስታት ተቋም የአውሮፓ ህብረት ተወካይ መስሪያ ቤትን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። NSA በአውሮፓ ህብረት መስሪያ ቤት ውስጥ የስለላ መሳሪያዎችን እንደተከለ የዘገበው ዎልስትሪት ጆርናል፣ “ይሁን እንጂ ቀድሞም ቢሆን ቦታው ከስለላ ነፃ አልነበረም” ብሏል። የNSA የስለላ ባለሙያዎች የአውሮፓ ህብረት ቢሮዎችን በስለላ መረብ ውስጥ ለማስገባት ሲሰማሩ ነው፣ ከነሱ ቀድሞ የቻይና መንግስት የስለላ መረብ መዘርጋቱን በአካል ያዩት። የራሺያ መንግስትም እንዲሁ፣ ለጂ20 ስብሰባ የመጡ የተለያዩ ፕሬዚዳንቶችንና ባለስልጣናትን ለመሰለልና ስልኮቻቸውን ለመጥለፍ የሚያስችል መሳሪያ ተጠቅሟል።

ታዲያ፣ ራሺያና ቻይና፣ ከዳር ሆነው ትችት መሰንዘራቸው የምን አስመሳይነት ነው? የአውሮፓ መንግስታት ሁኔታም ተመሳሳይ ነው። የአሜሪካ መንግስት፣ በአንድ ወር ውስጥ ከአራት ቢሊዮን በላይ የስልክ መረጃዎችን ከጀርመን እንደወሰደ የገለፁ ዘገባዎች፣ ከፈረንሳይና ከስፔንም በአንድ ወር ውስጥ ከመቶ ሚሊዮን በላይ የስልክ መረጃዎችን እንደሰበሰበ ገልፀዋል። ነገሩ እውነት መሆኑ በተለያዩ ምንጮች ቢረጋገጥም፤ የጀርመን፣ የፈረንሳይና የስፔን ባለስልጣናት በቁጣ ቅሬታቸውን ሲገልፁ መታየታቸው አስቂኝ ድራማነት ያለፈ ትርጉም የለውም። ለምን ቢባል፣ መረጃዎቹን ሰብስበው ለNSA የሰጡት የየአገሮቹ የስለላ ተቋማት ናቸው - NSA በፈንታው የራሱን መረጃ ያካፍላቸዋላ። እንዲህም ሆኖ፣ NSA ከዳር እስከ ዳር መረጃዎችን አፋፍሶ መሰብሰቡ ትክክል ነው ማለት አይደለም። የሰዎችን የግል ሕይወት ይዳፈራል። መግቢያ መውጪያ የሚያሳጣ የመንግስት ስለላ እርግጥ ነው፤ የአሜሪካ ብሄራዊ የፀጥታ ኤጀንሲ (NSA)፣ የዜጎችን የግል ሕይወት ይጥሳል በሚል የሚቀርብበትን ተደጋጋሚ ወቀሳ ከማስተባበል ተቆጥቦ አያውቅም። “የዜጎችን የስልክ ንግግርና የኢሜይል መልእክት እየጠለፍኩ አይደለም” የሚለው NSA፣ ሰዎችን በስም የማይጠቅስ የስልክ፣ የኢሜይል፣ የግዢ፣ የባንክ፣ የሐዋላ፣ የክፍያ ጥቅል መረጃዎችን (ሜታዳታዎችን) ማከማቸት የዜጎችን የግል ሕይወት አይጥስም ይላል።

ከየትኛው ቁጥር ለየትኛው ቁጥር እንደተደወለ፣ መቼ ተደውሎ ለምን ያህል ደቂቃ የስልክ ግንኙነቱ እንደቀጠለ የሚያሳዩ ጥቅል መረጃዎችን እንሰበስባለን እንጂ፣ የዜጎችን የስልክ ንግግር አንቀርፅም ብለዋል የNSA ዳሬክተር። በዚያ ላይ፣ “የተሰበሰቡትን መረጃዎች አከማቻለሁ እንጂ በዘፈቀደ መረጃዎቹን አልመረምርም፣ አልሰልልም” የሚለው NSA፤ መረጃዎቹን የምመረምረውና የምሰልለው የጥርጣሬ ፍንጮች ላይ በመመስረት ብቻ ነው ይላል። ካለፈው ሰኔ ወር ወዲህ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ጋዜጦች የተሰራጩ ዘገባዎች ግን፣ ይህንን የNSA ማስተባበያ የሚቃረኑ ናቸው። NSA፣ “ፕሪዝም” እና “አፕስትሪም” በሚሉ የስለላ ፕሮጀክቶች፣ የስልክ ንግግሮችንና የኢንተርኔት ግንኙነቶችን በቀጥታ እየጠለፈ እንደሚሰልልና እየቀረፀ እንደሚያስቀምጥ ዘጋርድያን ዘግቧል። የየእለቱን መረጃ ሁሉ ሰብስቦ ለማስቀመጥ፣ በየእለቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዳዲስ ኮምፒዩተሮችን መግዛት እንደማይቻል ግልፅ ቢሆንም፣ ሌሎች ዘዴዎች አሉ።

ለምሳሌ፣ ከአሜሪካ ጋር በቅርበት ከሚሰሩ አራት አገራት መካከል አንዷ የሆነችው እንግሊዝ፣ የስለላ መረጃዎችን ለመጥለፍና ለማከማቸው ዘመናዊ ተቋም እየገነባች ነው። ተቋሙ ግዙፍ ከመሆኑ የተነሳ፣ በአውሮፓና በኤስያ አገራት ዙሪያ፣ በስልክና በኢንተርኔት የሚሰራጩ መልእክቶችን በሙሉ ለሶስት ቀናት ቀርፆ ማቆየት እንደሚችል የዘገበው ዘጋርዲያን፣ የ30 ቀናት ጥቅል መረጃዎችንም (ሜታዳታዎችንም) ሰብስቦ ማቆየት ይችላል ብሏል። እንግሊዝ እንዲህ ማድረግ ከቻለች፣ እጅግ ግዙፍ የሆነው የአሜሪካው NSA በብዙ እጥፍ የሚበልጥ የመረጃ ሰብስብ አከማችቶ ማቆየት እንደሚችል ለመገመት አይከብድም። (በነገራችን ላይ፣ ለአመታት ተደብቆ የቆየ ይሄ ሁሉ ሚስጥር፣ ድንገት በግላጭ የተዘረገፈው ለNSA በኮንትራት ይሰራ የነበረው ሮበርት ስኖደን ሰርቆ ባወጣቸው 50 ሺ ገደማ ሚስጥራዊ ደብዳቤዎች ሳቢያ ነው።) የስልክ፣ የኢሜይል፣ የግዢ እና የሽያጭ፣ የኪራይና የስጦታ፣ የጉዞ እና የጉብኝት መረጃዎች ላይ፣ የጐዳና ካሜራዎችና የጂፒኤስ፣ የሰው አልባ አውሮፕላንና የሳተላይት መረጃዎች ሲጨመሩበት፣ የዘመናችን ስለላ ምንኛ የሰዎችን የግል ሕይወት እንደሚያጠፉ ሲታሰብ ያስፈራል፡፡

            ከዕለታት አንድ ቀን፤ አንዲት አይጥ ወደ አያ ዝሆን ሄዳ ልጁን ለልጇ እንዲድርላት ጠየቀችው። አያ ዝሆንም፤ “እንዴት ባክሽ? እንዴት ብትደፍሪኝ ነው ልጄን ለልጅሽ የተመኘሻት?! እኔ ማን እንደሆንኩ አታውቂም ማለት ነው፡፡ ከእንስሳት ሁሉ ግዙፉና ጠንካራው እኔ ነኝ፡፡ ጥርሴ ልዩ ዋጋ ያለው አንጋፋ አባት ነኝ፡፡ የአንድ ሙሉ ጫካ ዛፍ ገለባብጬ ለመጣል እችላለሁ፡፡ እና ለአንድ አይጥ ለሚባል ጉድጓድ ውስጥ ለሚኖር ፍጡር፣ ለዚህ ደቃቃ ፍጡር ልጄን የምድር ይመስልሻል? ልጄንማ እንዲህ አድርጌ አላዋርዳትም!” አላት፡፡ አይጢትም፤ “ባለነጭ ጥርሱን ዝሆን ምንም ደቃቃ ብሆን የምጠቅመው ቀን ይመጣል” አለችው፡፡ አያ ዝሆንም በንቀት፤ “አንቺን ዓይነት ደቃቃ ለእኔ ዓይነት ግዙፍ እንስሳ ምን ሊያደርግ እንደሚችል አሁኑኑ ማወቅ እፈልጋለሁ፡፡

አለበለዚያ ስለ ድፍረትሽ እግሬ ሥር አስገብቼ እደፈጥጥሻለሁ!” እያለ ወደሷ መምጣት ሲጀምር፤ በድንገት አዳኝ - ፈረሰኞች እየጋለቡ አቧራውን እያስጨሱ መጡ፡፡ አያ ዝሆን እነዚህ የአደን ሰዎች፤ ያንን የሚኩራራበትን ነጭ ጥርሱን ፍለጋ ሊገድሉት እንደሚችሉ በመገመት መደበቂያ ቦታ ይፈልግ ጀመር፡፡ ይሄኔ አይጢቱ፤ “ጌታ ዝሆን! አይዞህ አትፍራ፡፡ አሁን እየመሸ በመሆኑ ጠላቶችህ አያዩህም፡፡ እኔ ግን ችሎታዬን አሳይሃለሁ” አለችው፡፡ “እሺ” ብሎ ጥግ ይዞ ቆመ፡፡ ዕውነቱም ፈረሰኞቹ ስለመሸባቸው በአካባቢው ፈረሶቻቸውን አስረው ተኙ፡፡ ጨለማው ዐይን ሲይዝ አይጢት ሥራዋን ጀመረች፡፡

የኮርቻውን ቀበቶ፣ የድሃራይና ቀዳማይ ማንገቻ፣ የመቀመጫውን ግላሥ፣ የእርካቡን ገመድ፤ በጥርሷ ቀረጣጠፈችው፡፡ ፈረሰኞቹ፤ ጠዋት ፈረሳቸው ላይ ወጥተው አደናቸውን ሊቀጥሉ ሲጋልቡ ኮርቻና እርካባቸው ተበጣጥሶ እየተንሸራተቱ ወደቁ፡፡ እግርና እጃቸው ተሰብሮ አደናቸውን አቋረጡ፡፡ አያ ዝሆን ዛፉን ተደግፎ፣ በአይጢቱ ሥራ ተደንቆ፣ “ዕውነትሽን ነው እመት አይጥ፡፡ ከእኔ ጥርስ ያንቺ ጥርስ እንደሚሻል ገባኝ፡፡ ለትልቁ እንስሳ ትንሿ እንስሳ ልትጠቅመው እንደምትችል አስተዋልኩ፡፡ “በቃ ልጄን ለልጅሽ እድርለታለሁ” አላት፡፡

                                                       * * *

ትልቅ ነን የምንል ሹሞች፤ ባለሥልጣናት ወይም የበላይ አካላት፤ ትናንሾች ናቸው ብላችሁ የምታስቧቸውን የበታች አካላት አትናቁ! ትንሹም አቅም አለውና፡፡ አበሻ ጋን በጠጠር ይደገፋል ይላል! ጋን በክብ መቀመጫው ለመቆም ምን ያህል እንደሚቸገር መረዕየት (Visualize የማድረግ) አቅም ብቻ ነው የሚጠይቀው፡፡ በፓርቲ ሰውነት፤ በመንግሥት ሹመኛነት፣ በትምህርት “ማዕረግ”፣ በውትድርና የበላይነት፣ በሊቀመንበርነት ነጭ ጥርስ ያለን ግዙፍ አካል ነን ለማለትና ለመገበዝ መሞከር፤ ክፉ ቀን ሲመጣ የት ልደበቅ ማለት ምን ያህል እንደሚያሸብር የትልቁ ዝሆን ታሪክ ሁነኛ ነገር ነው፡፡ ላፎንቴን ገጣሚው፤ “ድርጭትና ተራራው” በሚለው ግጥሙ - “ይህ ኩራትና ግብዝነት፣ መቼም የትም አያደርስህ እንዳንተ ትልቅ ባልሆንም፤ እንደኔ ትንሽ አደለህ!” የሚለው ይሄንኑ ዕውነታ ለማፀህየት ነው፡፡ ተፎካካሪዎችን መናቅ፣ ተቃዋሚዎችን መናቅ ከግዝፈት እሳቤ የመጣ ከሆነ ራስን ያለማየት ችግር እንዳለ ነው የሚያስገነዝበን፡፡ ወጣት ልጆቻችን የትምህርት ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አጠያያቂ አይደለም፡፡

ትምህርት ተማሩ የሚባለው የሚማሩበት ከባቢ አየር ጤናማ ሲሆን ነው፡፡ የትምህርቱ ጥራትና ክብደት፣ መምህሩ፣ የጽዳት ሠራተኞቹ፣ የትምህርት መሣሪያዎቹ፣ የመጫወቻ ሜዳዎቹ እና የመጫወቻ ክፍለ ጊዜያቱ፣ የማጠናከሪያ ትምህርቱ፣ የወላጅ መምህርና ተማሪ ስለስተ ጥምረቱ፡፡ ዛሬ ጥያቄ ውስጥ ነው፡፡ አንዱ ሲሳካ ሌላው እያነከሰ ወላጆችን እያስጨነቀ ነው፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ሸፍተው የሚውሉባቸው ቦታዎች እጅግ ዘግናኝ ገጽታ ነው ያላቸው፡፡ ያለዕድሜያቸው በሱስ ይጠመዳሉ፡፡ ያለ ዕድሜያቸው ያልተፈለገ እርግዝና ሰለባ ይሆናሉ።

ት/ቤቱም ወላጁም የዚህ ዕውቀት የለው አይመስሉም፡፡ ስለተረካቢ ትውልድ የምናስብ ከሆነ ይህን አሰቃቂ ዕውነታ ተቀብለን አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ አለብን! ዛሬ የማይናገር አፍ፣ ራስ - አቀብ (Self –censored) አፍ፣ የፈራ አፍ እንዳለ ሁሉ፤ ቀን አመቸኝ ብሎ የሚቀላምድ አፍ፤ የባለቤቱ ልጅ ነኝ ብሎ ዘራፍ የሚል አፍ፣ እኔ ብቻ ነኝ የተማርኩ የግድህን ስማኝ የሚል አፍ፤ የሚሰማውና የሚታዘበው አድማጭ ያለ የማይመስለው ዋልጌ አፍ ብዙ አፍ አለ፡፡ ህገመንግስት በዘፈቀደ የሚተረጐም ከሆነ፤ ቅጡን ያጣና አፍራሹና ፈራሹ የማይታወቅበት ሥርዓተ አልበኝነት እንዳይፈጠር ሥራዬ ብሎ ማጤን ተገቢ ነው፡፡ ህገ -መንግሥት አላዋቂ የሚጭበረበርበት፤ ጮሌ እንዳሻው እኔን ብቻ ስሙ የሚልበት መሆን የለበትም፡፡

የመመሪያዎች ግልጽነት ህብረተሰብን ከመወናበድ እንደሚያድን አንድ ሁለት የለውም። ወቅታዊ መግለጫዎች ራስ - አድን በመሆናቸው ይበረታታሉ፡፡ መንገድ እንደሚዘጋ ያወቀ አሽከርካሪ ካልሆነ ወጪና የጊዜ ኪሣራ ይድናል፡፡ ሚዲያዎቻችን ወቅታዊ መረጃ ማቅረብ ግዴታቸው ሆኖ ሳለ በሌሎች ዜናዎችና ዘገባዎች ከተጠመዱ “ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ” እንዳይሆኑ ሥጋት አለ፡፡ ሁኔታዎች ተባብሰው የማይቀለበሱበት ደረጃ እስኪደርሱ መጠበቅ ቢያንስ የዋህነት ነው አንተ ነህ አንተ ነህ በሚል ሰበብ መሸጋገር የአፍታ ጠቀሜታ ብቻ ነው ያለው፡፡ ጥቅም ያለው ነገር ሲሆን ራስን ማጨት፤ የከፋ ነገር ሲመጣ ሌላውን መመደብ፤ ቢያንስ ጊዜ ያለፈበት ታክቲክ እንደሆነ እንረዳ፡፡ “በሌላ ሰው እጅ እሳት መንካት አያስፈራም!” የሚለውን ተረት የአዘቦቱ ሰውም ይረዳዋል፡፡