Administrator

Administrator

 ለህጻናት ምቹ አገራት፡- ሲንጋፖር፣ ስሎቬኒያ፣ ኖርዌይ፣ ስዊድን

   በመላው አለም ከሚገኙት ህጻናት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ወይም 1.2 ቢሊዮን ያህሉ የድህነት፣ ግጭት ወይም ጾታዊ መድልኦ ሰለባዎች መሆናቸውን አለማቀፉ የረድኤት ተቋም ሴቭ ዘ ችልድረን፤ ባለፈው ረቡዕ ባወጣው አለማቀፍ ሪፖርት አስታውቋል፡፡
በአለማችን አንድ ቢሊዮን ህጻናት በድህነት በተጠቁና 240 ሚሊዮን ህጻናት ግጭት ባለባቸው አገራት ይኖራሉ ያለው ሪፖርቱ፤ 575 ሴት ህጻናት ደግሞ ጾታዊ መድልኦ በተንሰራፋባቸው አገራት ውስጥ እንደሚኖሩ አመልክቷል፡፡
ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የአለማችን ህጻናት ድሃ በመሆናቸው፣ በጦርነት አካባቢዎች በመኖራቸውና ሴት በመሆናቸው ሳቢያ የከፋ ህይወት እየመሩ ይገኛሉ ያለው የተቋሙ ሪፖርት፣ ያለ ዕድሜ ጋብቻ፣ የጉልበት ስራና የምግብ እጥረትም የአለማችንን ህጻናት ክፉኛ እየፈተኑ ከሚገኙ ተግዳሮቶች መካከል እንደሚገኙበት አመልክቷል፡፡
ሴቭ ዘ ችልድረን በ175 የአለማችን አገራት ላይ የሰራውን ጥናት መሰረት አድርጎ ባወጣው ሪፖርት፤ ምንም እንኳን ካለፈው የፈረንጆች አመት ጋር ሲነጻጸር ዘንድሮ በአብዛኞቹ የአለማችን አገራት፣ የህጻናት የችግር ተጋላጭነት ቢቀንስም፣ በ40 አገራት ግን ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉን አስታውቋል፡፡
ህጻናት በከፍተኛ ሁኔታ ለድህነት፣ ግጭትና ጾታዊ መድልኦ የተጋለጡባቸው ቀዳሚዎቹ የአለማችን አገራት ሁሉም ከአፍሪካ ናቸው ያለው ሪፖርቱ፤ ኒጀር፣ ማሊና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ደረጃን መያዛቸውን አመልክቷል፡፡ ለህጻናት ምቹ የተባሉት የአለማችን አገራት በአንጻሩ ሲንጋፖር፣ ስሎቬኒያ፣ ኖርዌይና ስዊድን ናቸው፡፡

ይድረስ ለሁለቱም አገራት  መሪዎች፡-
ግብፅና ኢትዮጵያ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት አላቸው፤ ከሰማኒያ በመቶ በላይ ከኢትዮጵያ የሚፈልቀው ጥቁር አባይ፣ ከነጭ አባይ ጋር ተጨምሮ፣ ለግብፃውያን የህልውናቸው መሰረት ነው፡፡ የጥንትም ይሁን ዘመናዊ የግብፅ መሪዎች፤ ይህንን የግብፃውያን የህልውና  መሰረት መጠቀምና ማስቀጠል የሚፈልጉት በኢትዮጵያውያን ኋላ ቀርነት፣ ደካማነትና ኪሳራ ላይ ብቻ ሆኖ መዝለቁ፣ የሁለቱን ሃገሮች ግንኙነት እስከ ዛሬ አሉታዊ አድርጎታል፡፡ ይህ በዲፕሎማሲ ቋንቋ፣ በተሸናፊነት መንፈስ፣ በኢትዮጵያ መሪዎችና ፖለቲከኞች የሚሸፋፈን ቢሆንም፣ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ልቦና ሁሉ እንደ ሰማዩ ፀሃይና ጨረቃ፣ በግልፅ ለዘመናት ለተያዘ ቅሬታና የቁጭት ስሜት ምክንያት ነው፡፡
ቀደም ብሎ ግብፃውያን መሪዎች ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ፣ ጥንታዊውን የሁለቱን ሃገሮች የሃይማኖት ግንኙነት ይጠቀሙ ነበር፤ ውጤታማም ነበሩ፡፡ ከዚህ በኋላ ግን የቀጠሉት የሃገራችንን የውስጥ ጉዳይና ቅራኔ፣ ኋላ ቀርነታችንን በመጠቀም፣ እሳቶቻችንን በመቆስቆስ፣ በማንደድና ቤንዚን በመጨመር ሲሆን ውጤታማ ሆነው ዘልቀዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ግብፃውያን ዘመን የፈጠረላቸውን፣ ለፍትሃዊ ተጠቃሚነት ግድ የሌለውን ዓለምና በተለይ የአረብ ሃገሮችን አጋርነት ተጠቅመው፣ የሃገራችንን የመልማት፣ የተፈጥሮ ሃብቷን የመጠቀም መብቷን ሙሉ ለሙሉ አፍነው ቆይተዋል፡፡
እስካሁን በዚህ አጠቃላይ አውድ የቀጠለው የአገራቱ ግንኙነት፣ ትላንትም ዛሬም፣ ለወደፊቱም ለሁለቱም አይጠቅምም፡፡ በተለይ ለግብፃውያን ደግሞ የበለጠ አይበጅም፡፡ ዛሬ ሁኔታዎች እያዘገሙም ቢሆን መቀየራቸውን መታዘብ ይቻላል፣ ወደፊትም መቀየራቸውም ግዴታ ነው፡፡ አዝጋሚው ሂደትና በተለይ የግብፅ መሪዎች ፍላጎት ግን ሁለቱንም እየጎዳ መቀጠሉን፣ ወደፊት ደግሞ የበለጠ ጉዳትና ኪሳራ እንደሚሆን መረዳት ተገቢ ነው፡፡
የሁለቱ ሃገሮች አጀንዳ ዛሬ ለሃይል ምንጭ ብቻ ነው ተብሎ እየተገነባ ካለው፣ ከህዳሴው ግድብ የውሃ አሞላልና ከውሃ ክፍፍል በላይ፣ በወቅቱ የውሃ ሃብቱን የመጠቀም፣ በተለይ በኢትዮጵያ በተፈጥሮ ላይ ያለው ጥገኝነት በወቅቱ የቀነሰ ህዝብና ኢኮኖሚ ዕውን የማድረግ፣ ተፈጥሮን የመጠበቅና ግብፃውያን መሪዎች በኢትዮጵያውያን ስሜት ላይ የፈጠሩትን ቁስል የሚያሽር ግንኙነት፣ እውነተኛ ትብብርና ዕርቅ መሆን ይኖርባቸው ነበር፡፡ በሁለቱም ሃገሮች መሪዎች እየተደረጉ ያሉ ድርድሮች፣ ውይይቶችና ስምምነቶች የጋራ ሆነው፣ በዚህ መሰረት ላይ ካልተፈፀሙ፣ ለሁለቱም ህዝቦች ችግርን የሚያራዝሙ፣ ከላይ የተጠቀሰውን የኢትዮጵያውያን ስሜት የሚያስቀጥሉ ብቻ ይሆናሉ፡፡ አለባብሰው ቢያርሱ ደግሞ ነገ በአረሙ መመለስ አይቀርም፡፡ እርሻውን በሁለቱ ሃገሮች በእየተራ እንመልከተው፡፡
አባይ፣ የህዳሴው
ግድብና የኢትዮጵያ መሪዎች
የኢትዮጵያ መሪዎች የወቅቱን ትኩሳትና ግርግር ብቻ ከማብረድ በላይ፣ ታሪካዊውንና ወቅታዊውን የግብፅ መሪዎችን ፍላጎቶችና ችግሮቻቸውን፣ ለሁለቱም ሃገር ህዝቦች ያተረፉትንና ወደፊት የሚያተርፉትን ችግር፣ የቀጠለውን የኢትዮጵያውያንን እውነተኛ ስሜት፤ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ ለእራሳቸው ለግብፃውያን ሁሉ ለማስገንዘብ  መስራት ይገባቸው ነበር፡፡ ለሁሉም ስለሚጠቅም፡፡
የዛሬውን የህዳሴ ግድብ ጨምሮ የአባይ ውሃን በኢትዮጵያ ለልማት ለመጠቀም ዕቅዱ የተዘጋጀው በንጉሱ ዘመን ቢያንስ ከዛሬ ሃምሳ ዓመታት በፊት በአሜሪካኖች ድጋፍ ነበር፡፡ የአሜሪካኖች የድጋፍ ጅምር ለግብፅ የርዕዮተ ዓለም አሰላለፍ የተመዘዘ ቢጫ ካርድ ብቻ ስለነበር፣ ግብፅ አሰላለፏን ስታስተካክል፣ ለዓመታት የተደረገው ጥናት፣ በሁለት ቀናት ተቋርጦ፣ ዕቅዱ ከግማሽ መቶ አመታት በላይ አቧራ ሲጠጣ ቆይቷል፡፡
ከምስራቁ ወደ ምዕራቡ ዞረው ለጊዜው የተሳካላቸው የግብፅ መሪዎች፣ ኢትዮጵያ በእራሷ አቅም ልትሰራ የምትችለውን ልማት ለመከላከል የመረጡት ስልት፣ በሃገሪቱ ችግሮች ስንጥር በማስገባት ማዳከምን ነበር፡፡ ጀብሃን፣ ሻዕቢያን፣ ወያኔንና ሌሎችንም መሳርያና ችግሮቻችንን ብቻ ከላይ (መሰረታዊ መንስኤዎቻቸውን ሳይሆን) ማስታጠቃቸውን፣ ዛሬም የአኩራፊዎቻችን አለኝታና መጠጊያ ሆነው መዝለቃቸው ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ለሶማሊያ አሸባሪዎች፣ለወራሪው ሻዕቢያ መሳርያ አቅራቢም ነበሩ፤ ዘርዝሮ መጨረስ አይቻልም። ከዚህ ጋር ግብፅ፣ ኢትዮጵያ ዓባይን ለሚመለከቱ ማንኛውም ዕቅዶች፣ ከየትኛውም ሃገር የገንዘብ ተቋም ብድር፣ እርዳታና የቴክኒክ ድጋፍ እንዳታገኝ ሳታመነታ በመስራቷና ስለተሳካላት ጭምር፣ ዛሬ የሃገራችን መሪዎች ግፉን አሜን ብለው ሊቀበሉት ችለዋል፡፡
በዚህ ሂደት ኢትዮጵያ በረጅም የእርስ በእርስ ጦርነት፣ በችጋርና በመከራ ውስጥ እየተንፏቀቀች፤ በድርቅና በርሃብ የሰው ህይወት እየጠፋ፣ ለስድሳ ዓመታት ስትዘልቅ፣ የተገነጠሉትን ትተን፣ የህዝብ ቁጥሯ ዛሬ ከመቶ ሚሊዮን በላይ ሆኗል፡፡ ከሃምሳ ዓመታት በፊት ሃያ አምስት ወይም ሰላሳ ሚሊዮን ስለነበር የህዝብ ቁጥሯ በአራት እጥፍ ሲያድግ፣ እንደ ጥንቱ ሙሉ ለሙሉ የተፈጥሮ ጥገኛ እንደሆነ ነው፡፡ ቀደም ብሎ የተሻለ ውጤታማ የሆነውን የአባይ ውሃ በተወሰነ መጠን የማልማት ዕድል ቢኖራት፣ሃገሪቱ የጦርነት አውድማ ባትሆን፣ትምህርት ቢስፋፋና እድገት ብታስመዘግብ ኖሮ፣ዛሬ ሃገሪቱ የተመጠነ የህዝብ ቁጥር፣በተወሰነ መልኩ ከተፈጥሮ ጥገኝነት የተላቀቀ ኢኮኖሚና ህዝብና ሌሎች የተፈጥሮና የውሃ ሃብቶቿን ለመጠቀም የሚያስችል አቅም ይኖራት እንደነበር ግልፅ ነው፡፡ ዛሬ ለግብፅም ለኢትዮጵያም የተሻለ ይሆን ነበር፡፡
ባለቤቶች ራሳችን ብንሆንም፣ በግብፅ መሪዎች የሚደገፈው ኋላ ቀር ጉዞ ግን ሌሎችን ጨምሮ የተፈጥሮ ሃብት የሆነውን አባይ ውሃ በመጠኑ ቀንሶታል፡፡ የተፈጥሮ ሃብቶች (ውሃን ጨምሮ) ለሃገራችን ያላቸውን አስፈላጊነት ደግሞ ከነበረው በአራት እጥፍ ጨምሮታል ማለት ይቻላል፡፡
የግብፅ መሪዎችን አፍራሽና አፋኝ ፍላጎት ለመቋቋምና መብታችንን መጠቀም ለመጀመር ደግሞ ዘገየን፤ ዋጋ አስከፈለን እንጅ እስከ መጨረሻው ሊገታን አልቻለም፡፡ የህዳሴውን ግድብ ጥርሳችንን ነክሰን ጀምረነዋል፤  ወደፊትም እንቀጥላለን፤ የቆመ መራመዱ ስለማይቀር፣ መቀጠሉ ግዴታ ይሆናል፤ በተለያየ ዓይነትና መጠን፡፡ የኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብታቸውና በአባይ ውሃ የመጠቀም መብት፤ ወቅቱንና ጊዜውን፣ መልኩን፣ ወርዱንና ስፋቱን የሚወስኑት፤ ዓለም አቀፍ ህጎችና ስምምነቶች፣ እንዲሁም  የእራሳችን ሃገር ውስጣዊ አቅም ናቸው፡፡
ከነዚህ ሁሉ በታች ግን በኢትዮጵያ ያለውና ወደፊት የሚኖረው የተፈጥሮ ሃብቶች፣ የውሃ ሃብቱ ተጨባጭና ወቅታዊ አስፈላጊነት፣ ከታችኛው ተፋሰስ ሃገሮች በተለይ ከግብፅና ከሱዳን ጋር ያሉን ታሪካዊና ወቅታዊ ግንኙነቶች፣ ታሪካዊ ቁርሾዎችና ጠባሳዎች ድርሻ አይኖራቸውም ማለት አይቻልም፡፡ ይህንን ለግብፅ መሪዎች በግልፅ ቋንቋ ማስረዳት ተገቢ ነበር፡፡ በተለያዩ ስልቶች ለሃገራችን ጉዞ ዕንቅፋት መሆናቸውን ማቆም፣ እርም ማለት እንደሚገባቸው ዛሬ ሳይሆን በፊትም ሊነገራቸው ይገባ ነበር፡፡ ከህዳሴው ግድብ ግንባታ በፊትም፣ በኋላም፣ ሁልጊዜ እስካልታረሙ ድረስ፣ የመሰረት ድንጋዩ ሲጣልም ቢሆን አብዩ መልዕከት መሆን ነበረበት፡፡
ይቻላል ተብሎ የተጀመረው የህዳሴው ግድብ መሰረት ሲጣል፣ ሃገራችን ሃብቷን ለምን ሳትጠቀም እንደዘገየች፣ ዛሬም እንዴት እንደምትገነባው ተገልፆ፣ ከታሪካችን የወደፊቱን ማመላከት ለሁሉም ጠቃሚ ነበር፡፡ ኢትዮጵያውያን የመልማትና የመጠቀም መብታቸውን በግብፅ ታፍነው ለዘመናት ከዘለቁ በኋላ ይህንን አፈና ለመቀልበስ የተጀመረውን የህዳሴ ግድብ ግንባታ፣ የአፈናውን አንዳንድ ስልቶች ከተቀበለ፣ የተሸናፊነት ስሜት ላይ የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥና ከዚያ በኋላ ማስቀጠል ስህተት ነው፡፡ ለወደፊቱም አቅም አይሆንም፡፡
የግብፅ መሪዎችን ግፍ አሜን ብላ የተቀበለችው ሃገር፣ የአባይን ውሃ መጠን በጣሳ የሚቀንስ ዕቅድን ይዛ የብድር፣የእርዳታና የቴክኒክ ድጋፎች ለማግኘት ሙከራ የምታደርግ አይመስልም፡፡ ባይገኝም ግን ችግሩን ለማስገንዘብ ሙከራው መደረግ፣ አጀንዳውን ሁልጊዜ ወቅታዊ ማድረግ ነበረብን፡፡ ይህን ትተን ለሃይል ማመንጫ ብቻ ብለን፣ የያዝነውን ዕቅድ የሚደግፍ ሃገርና ተቋም ዓለም ላይ ሲጠፋ እኛ የት እንዳለን፣ዓለም ምን እንደሆነች፣ የግብፅ መሪዎችንና ፍላጎቶቻቸውን ልናጠይቅበት፣ልንረዳበትና የጋራ አቋም ልንይዝበት ይገባ ነበር - ከታሪካዊ ጅምር ጋር፡፡
በውጭ ሃገር ስራ ተቋራጭ፣ በከፍተኛ ብድር ላይ የተደገፈና በእርዳታ በሚደጎም  አጠቃላይ ኢኮኖሚ የሚገነባን አንድ ፕሮጀከት የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር፤ “መሀንዲሶችም፣ ግንበኞችም፣ የፋይናንስ ምንጮችም እኛው  ነን” ብለው በኩራት መናገራቸው፣ ተገቢ ሳይሆን ከፍተኛ ስህተትም ነበር፤ ይህ የተጫነብንን ግፍ፣ በፈቃዳችን እንደመረጥነው ምርጫና ችሎታችን የሚያስገነዝብ ንግግር ዛሬም ድረስ ይደጋገማል፡፡ አስተሳሰቡ ሲቀጥል መንግስት ለስኳር ፋብሪካዎች ግንባታ ይውላል በማለት ለዓለም ገበያ ያቀረበውን የቦንድ ብድር የተበደረው ገንዘቡ ለምን እንደሚውል (ዛሬ ቢባክንም) ከመግለፅ በተጨማሪ ለህዳሴው ግድብ ግንባታ በጭራሽ እንደማይውል አበክሮ፣ ደጋግሞ፣ በመግለፅ ምሎ ተገዝቶ ነበር፡፡ በፍርሃት፣ በራስ ስሜት ብቻ መሸነፋችንን፤ ግፍን አሜን ብሎ መቀበላችንን ያረጋግጣል፡፡ ከዚህ ስሜት መውጣት እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡
በመንግስት ብቻ ተገድቦም አልቀረም፤ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ስለ ህዳሴው ግድብ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ቀርበው ሲናገሩ፣ ታሪክን አንስተው የገለፁትም ተመሳሳይ ነበር፤ ቆቅ ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ የሆነ፡፡ ዲያቆን ዳንኤል፤ “የአክሱም ህንፃን ስናቆም፣ ላሊበላን ስናንፅ የአለም ባንክ፣ አይ.ኤም.ኤፍ ነበሩ?” ሲሉ ራሳቸው ጠይቀው “አልነበሩም፤” ብለው ራሳቸው መልሰዋል፤- ዲያቆን ዳንኤል፡፡ በአወንታ እራሱን ለሚነቀንቀው ጋዜጠኛ “የህዳሴውን ግድብ ለመገንባትም ዛሬ እነዚህ ተቋማት ግዴታ አይደሉም፣ አያስፈልጉንም፣ በእራሳችን አቅም መገንባት እንችላለን፤” ሲሉ በስሜት ተናግረዋል፤ ከስሜት ጋር ደግሞ ስህተቶች አሉ፡፡
ዓለም ላይ ስመ ገናና የነበረውን አክሱም፣ የመን ድረስ ተሻግሮ አስተዳድሯል፣ ህንድ ድረስ የንግድ ግንኙነት ነበረው፣ ለግብፅ ክርስቲኖች ጭምር አለኝታ ነበር፤ የምንለውን ሃገርና ህዝብ ሃውልት ሲያቆም፣ ግብፃውያን ንቀውት፣ በአለም ሃገሮች አይን አይሞላም፣ ብቻውን ነበር ማለት ከፍተኛ ስህተት ነው፡፡ መነሻቸው ከመካከለኛው ምስራቅ የሆኑት፣ በእየጊዜው ከምንጫቸውና ከሌሎች ሃገራት ጋር ግንኙነቶች የነበራቸው ክርስትናችንና ንጉሱ ላሊበላ፣ ቤተ-መቅደስ ሲገነቡ፣ ብቻቸውን ነበሩ ማለት አለማገናዘብ ብቻ ነው፡፡
ዛሬ እኛ አሽቆልቁለን ዓለምና ተቋማት ተራምደው፣ እነዚህ ሁሉ አያስፈልጉንም ማለት ሞክራ ያልቻለችውን ጦጣ የሚያስታውስ ብቻ ነው፡፡ ዛሬ በግብፅ መሪዎች ፍላጎት ጫማ ስር ወድቀን በሌሎች ሃገሮች፣ በአለም ባንክ፣ በአይ.ኤም.ኤፍ አይን መሙላት አለመቻላችንን በተለይ ከአክሱም ስልጣኔ ጋር ማነፃፀር ነው ተገቢም፤ የሚጠቅመንም፡፡
በዘመናቸው ያላስፈለጋቸውን አባይ፤ አክሱማውያን ለግብፅ ወንድሞቻቸው ብቻ ቢተውት ትክክል ነበሩ፤ አባይን ተቀባይነታቸውን፣ ጥቅማቸውንና ፍላጎቶቻቸውን ለማረጋገጥ የተጠቀሙበት ግን ውሃውን መቀነስ ፣ማቀብ (መገደብ) ስለሚችሉ ነበር። ዛሬ የውሃ ሃብቱ እጅግ አስፈላጊ ቢሆንም ለዘመናት ሳንጠቀምበት የሰው ህይወት እየጠፋ፣ በችጋርና በመከራ ውስጥ ቆይተናል፡፡ ይህንን ታሪክ ለመቀየር እንደምንችል፣እንደጀመርነው ከዚህ በኋላ መቀጠል ይቻላል፡፡ ለህዝቡ ሞራል ተብሎ ከተገለፀም መቅደም የነበረበት ችግሩ ነው፡፡ ለህዝቡ ሞራል፣ መነሳሳትና እርብርብም ምክንያቱ እነዚህ የውሸትና የማስመሰል ንግግሮች አይደሉም - ከላይ የተገለፀው የዘመናት ቁጭቱ እንጅ፡፡  በሃገራችን መሪዎች የተሸናፊነት አቋም ምክንያት የግብፅ መሪዎች፣ አንድ ጊዜ ሰው፣ አንድ ጊዜ አፈር እየሆኑ እንዲቀጥሉ የልብ ልብ ሰጥቷቸዋል ማለት ይቻላል፤ እንመልከተው፡፡
ናይል፣ የህዳሴው ግድብና የግብፅ መሪዎች
ከግብፃውያኑ መሪዎች ዛሬ ደግሞ የሚጠበቀው፤ የትላንቱን ስህተት ሁሉ የሚያራግፍ፣ አፍራሽ ተልዕኮቻቸውን ሁሉ ማቆም ብቻ ሳይሆን በእውነተኛ ስሜትና ቁርጠኝነት፣ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ሃብታችንን የመጠቀም፣ የማልማት መብቶቻችንን በማክበርና በማረጋገጥ የታሪካዊውን ግንኙነት መስመር በወቅቱ ማስተካከል ነበር፡፡ ግብፃውያን መሪዎች የዛሬውን የኢትዮጵያ መሪዎች ፖለቲካና ዲፕሎማሲ ትተው፣ ዘላለማዊውን ከላይ የተገለጠውን፣ የፀሃፊውን ጨምሮ የዜጎችን ስሜት መረዳት አለባቸው፤ ፖለቲከኞችም ከዚህ የተለየ ስሜት ይኖራቸዋል ብሎ መጠበቅ ሞኝነት ነው፡፡
ግብፅና መሪዎቿ በቅርቡም በሃገራችን የተከሰተውን ችግር ለማራገብ ሞክረዋል፤ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ በቅኝ ግዛት ውል ለመሞገትና ንቀታቸውን ለመቀጠል ሞክረዋል፡፡ ቀደም ብለን እንደገለፅነው፤ ኢትዮጵያ በአዝጋሚ ሂደትም ቢሆን መቆም ጀምራለች፤ ተመስገን ነው፤ ግብፅና መሪዎቿ ያራገቡት ችግር ዛሬ አዲስ ተስፋን አምጥቷል፤ዶ/ር አብይ አህመድን የመሰለ መሪ። ምንም ቢሆን ግን ነገን በኢትዮጵያ በተሻለ ተስፋ መጠበቅ ግዴታ ስለሆነ፣ አቋምን በወቅቱ ማስተካከል የግብፅና መሪዎቿ ወቅታዊ ግዴታ ነበር፡፡  
ከኢትዮጵያ መሪዎች የተሸናፊነት ስሜትና ፈራ - ተባ ብለው በያዙት የዲፕሎማሲ አቋም ምክንያት የህዳሴው ግድብ የመሰረት ድንጋይ ከተጣለና በኢትዮጵያ ህዝብ እርብርብ ግንባታው ከቀጠለ በኋላም የግብፅ መሪዎች አቋም የተለያየ መልክ ነበረው፤ በመጨረሻ የነበረው ሊቀጥልበት ቢችልም፡፡
የመሰረት ድንጋዩ በተጣለ ማግስት የግብፅ መሪ የነበሩት ሁስኒ ሙባረክ ያቀኑት ወደ ምስኪኗ ኢትዮጵያ ሳይሆን ወደ ጣልያን ነበር፤ በንቀታቸው ምክንያት። ግድቡን የሚገነባው ሳሊኒ የጣልያን ስራ ተቋራጭ ስለሆነ፣ በጣልያን መንግስት በኩል እንደተለመደው እንቅፋት ለመሆን የተደረገ ሙከራ ነው፡፡ የጣልያን መንግስት፤ “ሳሊኒ ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ የሆነ ተቋም ስለሆነ ጣልቃ መግባት አንችልም፤” በማለት ሙከራውን አልተቀበለውም፡፡ ሙከራው ወደ ሳሊኒ አልቀጠለም ወይም ቀድሞ አልተሞከረም ብሎ የሚያስብ ገልቱ የለም፤ ስለዚህ ጣልያናዊው ሳሊኒ ግን ከሃገራችን ጎን ቆሞ መቀጠሉን ለማድነቅ እንገደዳለን፡፡
እኔ በግሌ የስራ ተቋራጩን አቋምና ወቅታዊ ስሜት ለመከታተል ሞክሬያለሁ፤ በአይናቸው ከማንሞላው የመገናኛ ብዙኋን፤ ሳሊኒ የህዳሴውን ግድብ የሚገነባበት ክፍያ (ከምስኪኗ ኢትዮጵያ) በወቅቱ እየደረሰው እንደሆነና ለወደፊትም ስጋትና ጥርጣሬ እንዳለው ተጠይቆ፣ በመገናኛ ብዙሃን አንብቤያለሁ፡፡ በሳሊኒ አመራሮች የተሰጠው መልስ አንጀቴን አርሶታል፡፡ ጣልያንንም ሳሊኒንም እጅ እንደነሳሁ አለሁ፡፡ ሁስኒ ሙባረክን የተኩት የሙስሊም ወንድማማቾች ሙርሲ፤ከዚህም በላይ የግብፃውያንን ህልውና ለማስጠበቅ እዘምታለሁ፣ የጦር መሪዎቻቸውን ሰብስበው፣ ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ ታዝበን ነበር፡፡ በተለያዩ የውስጥ ቀውሶች በቀጠለችው ግብፅ፤ ከሙርሲ በኋላ ወደ ስልጣን ከመጡት አልሲስ፣ መጀመርያ ላይ የለውጥ አዝማሚያ ታይቶ ነበር። አል.ሲ.ስ የኢትዮጵያውያንን የመልማት ፍላጎት እንረዳለን፣ እንደግፋለን ብለው፤ ከመሪዎች አልፎ የሁለቱ ሃገሮች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትም ተጀምሮ ነበር፡፡ በሊብያ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች፣ በግብፅ በኩል ወደ ሃገራቸው እንዲገቡ ከመተባበርም አልፈው መሪው፣ በአውሮፕላን ማረፍያ ተገኝተው፣ አቀባበል አድርገውላቸው ነበር፡፡ ለሁለቱ ሃገሮች የሚበጀው ተመሳሳይ ግንኙነት፣ መተባበርና መከባበር ስለሆነ፣ ተስፋን ያጫረ ጅምር ቢሆንም የቀጠለና የጎለበተ ግን አልነበረም፡፡
በሁለቱ ሃገሮች ከዚህ በኋላ የቀጠለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት፤ ውይይትና ድርድሩ ሁሉ በትክክለኛው መሰረት ላይ ያልቆመ፣ በጥርጣሬና ባለመተማመን ላይ የተመሰረተ ነበር፡፡ በአጠቃላይ ሱዳን የነበራትን አቋም ያስተካከለችበት፣ የግብፅ መሪዎች ግን ዛሬ የኤሌክትሪክ ሃይል ብቻ አመንጭተን የምንለቅበት ነው የምንለውን ግድብ እንኳ በሙሉ ልባቸው ለመቀበል ተቸግረዋል፡፡ እስከ ዛሬ የባከነው ጊዜ፣ ኢትዮጵያውያን ጥቂት መብቶቻችንን ለመጠቀም ሳንችል የቆየንበትን ታሪክ አልተረዱትም፡፡ አንድ ጊዜ ዝቅ ስላደረጉን የወደፊቱን ተገቢ ፍላጎቶቻችንን ከወዲሁ አልገመቱትም፡፡ ስለዚህ በዚህ የምንቀጥል ከሆነ መጨረሻው ለማንም የማይጠቅም፣ በተለይ ግብፃውያንን ዋጋ የሚያስከፍል ብቻ ይሆናል፡፡ ትላንትን ወደ ኋላ ማስታወስና ዛሬን መመልከት፣የወደፊቱን መዘዝ ለመተንበይ ያስችላል፡፡
አባይ ኢትዮጵያውያንና ግብፃውያን - እንደ መደምደሚያ
የግብፅ መሪዎች ኢትዮጵያን እንደ ጥንቱ አፍነው መቀጠል አይችሉም፤ ቢችሉም ግን አይጠቅማቸውም። ከዛሬ ሃምሳ ዓመት በፊት በነበርንበት ጉዞ ብንቀጥል፣ ከሃምሳ ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር አራት መቶ ሚሊዮን ይሆናል፤ እንደነበረው የተፈጥሮ ብቻ ጥገኛ ሆኖ ማለት ነው። በዚህ ወቅት ግድቡንና መስኖውን ትተን፣ ህዝቡ  ከብቶቹን ይዞ ወደ ተራሮቻችን ይወጣል፤ የውሃ ቅሉን ይዞ ወደ አባይና ገባሮቹ ይወርዳል፤ ግዴታው ነው፡፡ የሰው ዱካና የከብት ኮቴ ተፈጥሮን፣ዕፅዋትንና ውሃን ምን እንደሚያደርጉ መመልከት ይቻላል፤ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ብቻ፡፡ ያኔ ለሁላችንም አጀንዳ ላይኖር ይችላል፤ የበለጠ የምትጎዳው ሃገር ደግሞ ግብፅና ግብፃውያን ይሆናሉ፡፡
ከዚህ በመለስ የግብፅ መሪዎች በዚሁ ቀጥለው፣ ሃገራችን የጀመረችውን በተለያዩ መንገዶች የተፈጥሮ ሃብቷን  የመጠቀም መብቷን እያረጋገጠች ስትቀጥል አቅማችን ያድጋል፡፡ ያልነበረን ወንድማማችነትና ትብብር ድንገት ማምጣት ስለማይቻል፣ግብፃውያን እንደ አክሱም ዘመን፣ በወንድማማች ህዝቦች መካከል በሚኖር የትብብር መንፈስ፣ ከኢትዮጵያ ጋር የመስራት ዕድላቸው እየጠበበ ይሄዳል፡፡ በዚህ ወቅት በመካከላችን የሚኖረው ዓለም አቀፉ ህግና ስምምነት ብቻ ይሆናል፡፡ በዚህ ሁኔታም ግብፃውያን አያተርፉም፤ ስለዚህ ያዙኝ ልቀቁኝ አማራጭ ሆኖ ሊታያቸው ይችላል፡፡
በንጉሳችን የተመራውን ጉንዴትና ጉራን አናነሳውም፡፡ የሩቅ ታሪክም ቢሆን ሃገራችን ግን በዘመነ መሳፍንት ተከፋፍላ ነበር፡፡ አፄ ቴዎድሮስ ሃገሪቱን በቀላሉ አንድ አድርገው ቢነሱም፣ መጨረሻቸው እንደ ዘመነ መሳፍንት ወቅት ነበር፡፡ ንጉሱ በመቅደላ ተወስነው፤ በትግራይ በዝብዝ ካሳ፣ በሸዋ አፄ ምኒልክ፣ በላስታ ዋግሹም ጎበዜ ነግሰው ነበር፡፡ እንግሊዝ በአፄ ቴዎድሮስ የተያዙ ዜጎቿን ለማስፈታት ዕቅድ ስትነድፍ፣ የተያዘ አንድ ግንዛቤ ነበር፡፡ እንግሊዞች ለኢትዮጵያ ቅርብ ከሆኑት ቅኝ ግዛቶቻቸው፣  ግብፅና ሱዳን ጦር ለማዝመት ሃሳብ ነበራቸው፡፡ ኢትዮጵያውያንን ምን ቢከፋፍሉ፣ ከእነዚህ ሃገሮች የሚሰነዘር ጥቃት አንድ ላይ እንደሚያቆማቸው ስለተረዱ፣ ከህንድ ነበር ጦር ያዘመቱት፡፡ ሶማሊያና ዛይድ ባሬ እስካፍንጫቸው ታጥቀው፣ ኤርትራና ሻዕብያ በራሷ በግብፅ እስፖንሰርነትም በቅርቡ አይተውታል፡፡ ዛሬ ደግሞ ሁኔታዎች፣በኢትዮጵያ ተቀይረዋል፣ የተፈጠረ አቅም፣ የተያዘ ግንዛቤና ስምምነት አለ፤ ይቀጥላል፡፡


      አንዲት የቆቅ ልጅ የስንዴ እሸት ትርክክ ብሎ በስሎ በሚገኝበት እርሻ አጠገብ ወጥመድ ተጠምዶ አይታ እናቷን፤
“እናቴ ሆይ፤ እሸት አምሮኝ ነበር፣ ከዚህ ማሣ ገብቼ እንዳልበላ ወጥመድ እንዳይዘኝ ሰጋሁ፣ ምን ይሻለኛል?” ስትል ጠየቀቻት፡፡
እናቷም፤ “ተይ ልጄ ይቅርብሽ ትያዣለሽ አይሆንም” ብላ መከረቻት፡፡
 ልጅቷ ግን “ግድየለሽም አይዙኝም፣ ትንሽ ተክ ተክ አድርጌ ልውጣ” አለቻትና ገብታ ስትበላ ያ ወጥመድ እናቷ እንደፈራችው እግሯን ጥርቅም አድርጐ ያዛት፡፡
መቼም መከራ በመጣ ጊዜ በመጀመሪያ የሚታሰቡት ወላጆች ስለሆኑ፤ ያቺ የእናቷን ምክር አልሰማ ያለች ልጅ፤ “እናቴ ኧረ ተያዝኩልሽ” አለቻት፡፡
እናትየዋም፤ “ምነው ልጄ አስቀድሜ ነግሬሽ አልነበረም? አሁን ምን ላደርግልሽ እችላለሁ?” አለቻት፡፡
እማምዬ እባክሽ እርጂኝ? ፍቺልኝ ገመዱን?”
“በምን እጄ?”
“ታዲያ እንዴት ልሁን? ምን ይበጀኝ የኔ እናት?”
በዚህ ጊዜ እናት ለልጁዋ ምንጊዜም ምክር አዋቂ ናትና፤
“ዝም ብለሽ የሞትሽ መስለሽ ተኝ፤ ባለወጥመዱ ሲመጣ ሞታለች ብሎ ፈትቶ ይለቅሻል፡፡ ያኔ ታመልጫለሽ” አለቻት፡፡
ልጅ እንደተባለችው አደረገች፡፡
ባለወጥመዱ ሰው ሰብሉን ጐብኝቶ መጣና ቢመለከት ዝልፍልፍ ብላ ተኝታ ዐይኗን ጨፍና አገኛት፡፡ አጅሬ የሞተች መሰለውና፤ “አዬ ጉድ ወጥመዴ ቆቅ ይዞልኝ ነበረ፡፡ ነገር ግን ሞተች” አለና አዘነ፡፡
ጓደኛው ከበላዩ ሰብል ይጠብቅ ነበርና፤
“ወንድም” ብሎ ተጣራ “ወጥመዴ ቆቅ ይዞልኝ ነበረ፡፡ ነገር ግን በክታ አገኘኋት”
ባልንጀራውም፤ እስቲ ወደ ላይ አጉናት” አለው፡፡
ባለወጥመዱ ወደ ሰማይ ወርወር አደረጋት፡፡
ቆቋ ቱር ብላ ከጫካው ጥልቅ አለች፡፡
* * *
ምክር መቀበልና ማክበር ይገባል፡፡ አደጋ ላይ ሊጥል የሚችልን ነገር አስቀድሞ ማሰብ፣ ማውጠንጠንና መጠንቀቅ ተገቢ ነው፡፡ ብዙ አደጋዎችን፣ ብዙ ችግሮችን፣ ብዙ ውጣ - ውረዶችን ያየችው አገራችን መከራዋን ትወጣው እንጂ አብዛኛዎቹ የተከሰቱት ምክር በማይሰሙ መሪዎች፣ ኃላፊዎችና ሥራ አስኪያጆች ሳቢያ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ የታለፉ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ አጋጣሚዎች ደግመን ማጣት ከእንግዲህ ብርቱ ዋጋ ያስከፍለናልና ጥንቅቅ ብለን ማሰብ ይገባናል፡፡ የድህነት ነገር ሆኖብን ሁሌ ሥራችንን በዘመቻ እንድንሠራ እንገደዳለን፡፡
አንድን ሥራ በነጥብ መብራት አተኩረን መሥራት ትልቅ ጉልበት በማከማቸት ግብ እንድንመታ ይረዳናል፡፡ ሆኖም ዘላቂና የኔነት ስሜት ያለው ሥራ እንድንሠራ በሙያዊ ብቃት፣ በሥራ ክፍፍልና በሙሉ ስሜት እንድንራመድ ካልሆነ፣ ለብዙ ችግር እንጋለጣለን፡፡ ጦርነትም ቢሆን እንኳ በኃይል በኃይሉ፣ በክህሎት በክህሎቱ ሲሰደር ነው ለግብ ይበቃል የሚባለው፡፡
የጋራ ጥቅም ላይ ያነጣጠሩ መስሎ የግል ጥቅምን በጐን ማሳደድ ሊነቃበት የሚገባ ጨዋታ ነው፡፡ “ሌላ ጊዜ አንቺ ይላል፤ ጠላ ስትጠምቅ እሜቴ ይላል” የሚለውን የወላይታ ተረት ከልብ ማስተዋል ዋና ነገር፡፡
መቼም የሀገራችን ነገር አንዱ ሲወርድ አንዱ ሲወጣ ያለበት ነው፡፡ ከሥራውም ይልቅ ሰውዬውን ለሚያይ ዘላቂነት ያለውና ያለፈውን ስህተት ለማረም የቻለ ጉዞ ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡ የሠራተኛው፤ የፓርቲ አባሉ፣ የበታች ኃላፊው ሁሉ፣ ሁልጊዜ “እናቴን ያገባ ሁሉም አባቴ ነው” የሚልበት ዘመን ያከተመ ይመስላል፡፡ “ተሰናባች አይርገምህ፤ ተተኪው አይጥላህ” የሚለውን በጥንቃቄ ካዩት፣ ትርጉም ያለው ቁምነገር ያስጨብጠናል።
ተሰናባች በግፍ፣ በምቀኝነት ወይም በአድልዎ ተባሮ ከሆነ፣ እርግማኑ ይደርስብኛል ብሎ ማሰብ የአባት ነው፡፡ ተተኪው በተንጋደደ ዐይን የሚያይ ከሆነና፤ “ለዚያኛው ያልተኛ እኔን አይምረኝም”
ብሎ ያሰበ ከሆነም ሲሰጉ መኖር ነው፡፡ ከዚህም ይሰውረን፡፡ የሚመጣውን ሁሉ ተዘጋጅቶ መጠበቅ ያለ ነው፡፡ ጦር መጣ፣ ጦር መጣ እያሉ በጣም ያስፈራሩት ጀግና፤ በዝግታ እየተዘጋጀ፤ “ይምጣ ከመጣ ሞቼ ልጠብቀው እንዴ ልዘጋጅ እንጂ!!” አለ የሚባለውንም አንዘንጋ፡፡
ጉዳዩን የሚያቅ፤ የበሰለ፣ ባለገድልና ባለታሪክ ሰዋችንን አንናቅ፡፡ ከየቦታው ሰብስበን ሥራ ላይ እንዲቀመጥ እናድርግ፡፡ ልታይ ልታይ የሚለውንና የአደባባይ ጌጥ የሆነውን ትተን፤ ከልቡ ለሀገር የሚያስበውን እናስተውል፡፡ “ይቺ እንዴ ትጨፍራለች?” ቢባል፤ “ልብስ አጥታ እቤት የቀረችውን ባየህ!” አለ፤ የሚባለው የወላይታ ተረት የሚነግረን ይሄንኑ ነው፡፡

አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር፤ በቶፊቅ ኑሪ ተደርሶ፣ በዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ የተዘጋጀውን “ከመጋረጃው በስተጀርባ” የተሰኘ ቴአትር የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ እንደሚያስመርቅ ገለጸ፡፡
ጭብጡን በአገር ጉዳይ ላይ ባደረገው በዚህ የሙሉ ሰዓት ቴአትር ላይ አንጋፋና ወጣት ተዋንያን የሚሳተፉበት ሲሆን በምርቃቱ ላይ የባህልና ቱሪዝም ኃላፊዎች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚታደሙ ሀገር ፍቅር ቴአትር አስታውቋል፡፡   


Saturday, 26 May 2018 13:04

እንደ መግቢያ

  እንደ መግቢያ
                   ነቢይ መኮንን

ምነው ዛሬ እንባዬ፣ ለሰው ሳይታይ ይወርዳል
ምነው ዛሬስ ልቅሶዬ ሰው - አይሰማው - ሙሾ ሆኗል
ምን ታላቅ ሰው ሙቶብኝ ነው
እንዲህ ድምፄ ድምፁን ያጣው?
ዋ! ጋሽ አብይ!
ጋሽ አብይኮ ሰው ነበር፣ ከሰውም ሰው የቅን ማማ
የረቂቅ ተምሳሌት በላይ፣ ዕፁብ ምስል የነብስ አርማ፡፡
እሱስ አዕምሮውን አዞ፣ ማወቅ ያለበትን አውቋል፡፡
ሳያውቅ ዱታው - ዘራፍ የሚል፣ ባገሬ ስንት ዐብይ ሞልቷል!
ከዚህ በላይ እርግማን አለ? በአገር ላይ አለመታደል?
ይህ ነው መሰል ያስለቀሰኝ
ድምፅ - አልባ እዬዬ ያስቃኘኝ?!
ነበር አይባልም እሱ!
ጋሽ ዐቢይ!
ሰፊ ነው የዕውቀት አትሮንሱ
ነበር አይባልም እሱ!
“አለ”ም ቢባል፣ ተራ “አለ” አደል
ፈልጉለት ሌላ ዕፁብ ቃል
ጥበብ ነው ጥሩሩ ልብሱ
ነበር አይባልም እሱ
ሌላ የነፃነት እኩል፣ ገድል - አከል ቃል አስሉ
ነበር አይባልም እሱ!
“አለ”ም ቢባል ተራ “አለ” አደል
ፈልጉ ሌላ ህያው ቃል!!
ከህይወት ከራሱ እሚሻል!!
እናም “ቢሞት ሞተ አትበሉ”
ለእሱ ሞተ አይደለም ቃሉ
ልዩ ኑሮ ኖሮ ኖሮ
ልዩ ጥበብ ፈጥሮ አፋጥሮ
አልፎ ሄደ በሉ እንግዲህ፣ እራሱን በዕውቀት አኑሮ
እንደአየር ኃይል ባየር በሮ
እንደጠቢብ ፊልም ፈጥሮ
እንደኮሙኒኬሽን ሰው፣ የየክህሎቱን ቸሮ
የልባም አዋቂን ገድል፣ ፈፅሞና አስከብሮ
እራሱን አውርሶን ሄዷል፣ የልካችንን ቀምሮ!
ዕውነት እንበል ካልን …
እንደማንም መሞትማ ለማንስ ምኑ ያቅታል
እንደምንም መኖርማ ለማንስ ምኑ ይሳናል፡፡
ሰው ሆነን ሰው ሆነን መሞት፣ የባጀን ለታ ነው ጭንቁ
እንደጋሽ ዐቢይ ሰው ፈጥሮ፣ ማለፍ ነው የልባም ሳቁ!!
ሞተ ካፋችን አይውጣ
ሞትማ ዕውቀት አይገልም
ምሥጥ ጥበብ አያኝክም
የዘለዓለም ነው ሥሪቱ
አትሮንስ አይቆረጠምም!
“From ashes to ashes”
Such a mind never allows!
ከትቢያ ወደ ትቢያማ፣ ብሎ ሐረግ ለሱ የለም
    እንደ ዐቢይ ላለው አይሰራም!
ሰፊ ነው የሊቅ አድማሱ
አየር ኃይል ህዋ ፈረሱ
ኪነ - ፊልም ጥበብ ግላሱ
የሐዋርድ አዋጅ መለከት፣ የጥቁር ድምፅ ምስል ቅርሱ
ነበር አይባልም እሱ፣ ነውም ያንሳል ቃለ - ግሡ
አይለካም ወርደ - አትሮንሱ!
ዩኒቨርስ በሰው ቢመሰል፣ ዐቢይ ነበር የምድር ዋሱ
ነቢብ - ገቢር ውቂያኖሱ!
ፒያኖ ማዕጠንት መቅደሱ
ኮንጋና ጀምቤ ከበሮ፣ የካሪቢያን ዳሱ
የፎርት ዋሺንግተን ጀማ፣ የሙዚቃ ደቦ ምሱ
የሰው ፍቅሩ፣ የሰው ሱሱ
ምን ቃል ይበቃዋል ለሱ?!
እልፍ ነውና መለኪያው
ስውር ነውና ሚዛኑ
ሳይለይ አበባ እሳቱ
አይሞላምና ቋቱ
ለዚህ ነው ታላቅ ሰው ሲሞት
ፀሐይ ዕንባዋ እሚያጥራት
ከምድር ምህዋሯን እምትስት
ፍጥረታት ጉዞ እሚገቱት
ላም መታለብ የምታቆም
ወፍም መዘመር እምትሰንፍ
ሲሰሙ ነው የሊቅ ማለፍ
ሲዘጋ ነው የዕውቀት ደጃፍ!!
ጋሽ አብዬ … የዘር ግንዱ የአገር ፍቅር
    የእናት ኢትዮጵያ አፈር መከር
የእሱም ጥሪ ሆኖ ይሄው
በእናቱ መሬት አየነው!
ያም ሆኖ ነበር አይባል፣ ኗሪም - ቢባል ነገ አይበቃው
የፓን - አፍሪካው ነጋሪት፣ ገና የመጪ ድምፅ ነው!!
ዋ! ጋሽ አቢይ! …
(ለፕሮፌሰር አቢይ ፎርድ፤
ግንቦት 8፣2010) 

Saturday, 26 May 2018 13:04

እንደ መግቢያ

  እንደ መግቢያ
                   ነቢይ መኮንን

ምነው ዛሬ እንባዬ፣ ለሰው ሳይታይ ይወርዳል
ምነው ዛሬስ ልቅሶዬ ሰው - አይሰማው - ሙሾ ሆኗል
ምን ታላቅ ሰው ሙቶብኝ ነው
እንዲህ ድምፄ ድምፁን ያጣው?
ዋ! ጋሽ አብይ!
ጋሽ አብይኮ ሰው ነበር፣ ከሰውም ሰው የቅን ማማ
የረቂቅ ተምሳሌት በላይ፣ ዕፁብ ምስል የነብስ አርማ፡፡
እሱስ አዕምሮውን አዞ፣ ማወቅ ያለበትን አውቋል፡፡
ሳያውቅ ዱታው - ዘራፍ የሚል፣ ባገሬ ስንት ዐብይ ሞልቷል!
ከዚህ በላይ እርግማን አለ? በአገር ላይ አለመታደል?
ይህ ነው መሰል ያስለቀሰኝ
ድምፅ - አልባ እዬዬ ያስቃኘኝ?!
ነበር አይባልም እሱ!
ጋሽ ዐቢይ!
ሰፊ ነው የዕውቀት አትሮንሱ
ነበር አይባልም እሱ!
“አለ”ም ቢባል፣ ተራ “አለ” አደል
ፈልጉለት ሌላ ዕፁብ ቃል
ጥበብ ነው ጥሩሩ ልብሱ
ነበር አይባልም እሱ
ሌላ የነፃነት እኩል፣ ገድል - አከል ቃል አስሉ
ነበር አይባልም እሱ!
“አለ”ም ቢባል ተራ “አለ” አደል
ፈልጉ ሌላ ህያው ቃል!!
ከህይወት ከራሱ እሚሻል!!
እናም “ቢሞት ሞተ አትበሉ”
ለእሱ ሞተ አይደለም ቃሉ
ልዩ ኑሮ ኖሮ ኖሮ
ልዩ ጥበብ ፈጥሮ አፋጥሮ
አልፎ ሄደ በሉ እንግዲህ፣ እራሱን በዕውቀት አኑሮ
እንደአየር ኃይል ባየር በሮ
እንደጠቢብ ፊልም ፈጥሮ
እንደኮሙኒኬሽን ሰው፣ የየክህሎቱን ቸሮ
የልባም አዋቂን ገድል፣ ፈፅሞና አስከብሮ
እራሱን አውርሶን ሄዷል፣ የልካችንን ቀምሮ!
ዕውነት እንበል ካልን …
እንደማንም መሞትማ ለማንስ ምኑ ያቅታል
እንደምንም መኖርማ ለማንስ ምኑ ይሳናል፡፡
ሰው ሆነን ሰው ሆነን መሞት፣ የባጀን ለታ ነው ጭንቁ
እንደጋሽ ዐቢይ ሰው ፈጥሮ፣ ማለፍ ነው የልባም ሳቁ!!
ሞተ ካፋችን አይውጣ
ሞትማ ዕውቀት አይገልም
ምሥጥ ጥበብ አያኝክም
የዘለዓለም ነው ሥሪቱ
አትሮንስ አይቆረጠምም!
“From ashes to ashes”
Such a mind never allows!
ከትቢያ ወደ ትቢያማ፣ ብሎ ሐረግ ለሱ የለም
    እንደ ዐቢይ ላለው አይሰራም!
ሰፊ ነው የሊቅ አድማሱ
አየር ኃይል ህዋ ፈረሱ
ኪነ - ፊልም ጥበብ ግላሱ
የሐዋርድ አዋጅ መለከት፣ የጥቁር ድምፅ ምስል ቅርሱ
ነበር አይባልም እሱ፣ ነውም ያንሳል ቃለ - ግሡ
አይለካም ወርደ - አትሮንሱ!
ዩኒቨርስ በሰው ቢመሰል፣ ዐቢይ ነበር የምድር ዋሱ
ነቢብ - ገቢር ውቂያኖሱ!
ፒያኖ ማዕጠንት መቅደሱ
ኮንጋና ጀምቤ ከበሮ፣ የካሪቢያን ዳሱ
የፎርት ዋሺንግተን ጀማ፣ የሙዚቃ ደቦ ምሱ
የሰው ፍቅሩ፣ የሰው ሱሱ
ምን ቃል ይበቃዋል ለሱ?!
እልፍ ነውና መለኪያው
ስውር ነውና ሚዛኑ
ሳይለይ አበባ እሳቱ
አይሞላምና ቋቱ
ለዚህ ነው ታላቅ ሰው ሲሞት
ፀሐይ ዕንባዋ እሚያጥራት
ከምድር ምህዋሯን እምትስት
ፍጥረታት ጉዞ እሚገቱት
ላም መታለብ የምታቆም
ወፍም መዘመር እምትሰንፍ
ሲሰሙ ነው የሊቅ ማለፍ
ሲዘጋ ነው የዕውቀት ደጃፍ!!
ጋሽ አብዬ … የዘር ግንዱ የአገር ፍቅር
    የእናት ኢትዮጵያ አፈር መከር
የእሱም ጥሪ ሆኖ ይሄው
በእናቱ መሬት አየነው!
ያም ሆኖ ነበር አይባል፣ ኗሪም - ቢባል ነገ አይበቃው
የፓን - አፍሪካው ነጋሪት፣ ገና የመጪ ድምፅ ነው!!
ዋ! ጋሽ አቢይ! …
(ለፕሮፌሰር አቢይ ፎርድ፤
ግንቦት 8፣2010) 

  ፕሮፌሰር አብርሃም (አብይ) ፎርድ የሚለው ስም፣ በሕይወት በነበሩበት ጊዜም ሆነ ከሞቱ በኋላ ሲነሳ፣ አንዳች የአድናቆትና የአክብሮት ስሜት በብዙዎች ልብና አእምሮ ውስጥ ይፈነጥቃል። ዳሩ ግን ኢትዮጵያዊው ተወላጅ አብይ ፎርድ፣ በምርምር ሥራዎች ግርጌ  የሚጠቀሱ ብቻ ሳይሆኑ በአገራቸውም ሆነ በዳያስፖራነታቸው በእውነተኛ መንፈስ የሚሠሩ ነበሩ። ፕሮፌሰር አብይ  የተውልን ምርጥ ሥራዎቻቸውንና በአርአያነት የተሞላ አገልግሎታቸውን ብቻ አይደለም፡፡ የሰው ልጅ ምርጫውን ተከትሎ፣ በነጻነት እንዲያስብና ያሰበውንም በንግግር እንዲገልጽ አጥብቀው በማስረዳት ረገድ መልካም ውርስ ትተውልን ያለፉ በመሆናቸው ሲዘከሩ ይኖራሉ፡፡   
በትውልዳቸው ኢትዮጵያዊ የሆኑት ፕሮፌሰር አብርሃም (አብይ) ፎርድ የተወለዱት የካቲት 27 ቀን 1927 ዓ.ም  በአዲስ አበባ ውስጥ ሲሆን ወላጆቻቸው የተከበሩ የአፍሪካ ባርባዶስና የአፍሪካ አሜሪካ ተወላጆች ነበሩ፡፡ አባትና እናታቸው፣ ማርከስ ጋርቬይ (1887-1940) የፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄን በመፍጠር፣ በልዩ ልዩ ምክንያቶች አያት ቅድመ አያቶቻቸው፣ ወደ ሰሜንና ደቡብ አሜሪካ እንዲሁም  ካሪቢያን ደሴቶች የሄዱ ሁሉ ወደ ጥንታዊት አህጉራቸው አፍሪካ ተመልሰው፣ የልማቷ አካል እንዲሆኑ ያቀረቡትን ጥሪ በመቀበል፣ ወደ ጥንታዊት ሀገራቸው ኢትዮጵያ የመጡ ናቸው፡፡ በመሠረቱ፣ ማርከስ ጋርቬይ በመላው ዓለም የሚገኙ አፍሪካውያን ወደ አህጉራቸው እንዲሄዱ ከፍ ያለ ቅስቀሳ ከማድረጋቸውም በላይ ‹‹ጥቁር ኮከብ የሰውና የዕቃ ማጓጓዣ የንግድ መርከብ›› የተሰኘ ኩባንያ አቋቁመው እንደነበር ይታወሳል፡፡ ያኔም ኢትዮጵያ ከወራሪ ጠላት እራሷን ጠብቃ የኖረች፣ የሌሎችን መብት የምትጠብቅና የምታከብር፣ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች በማንነታቸው ኮርተው የሚኖሩባት ሀገር መሆኗ በብዙዎች ዘንድ ይታወቅ ስለነበር፣ አፍሮ አሜሪካውያን ወደ አፍሪካ አህጉር ለመምጣት ሲንቀሳቀሱ፣ ተቀዳሚ ምርጫቸው ያደርጓት እንደነበር ይታወቃል፡፡ ከ14 ክፍለ ዘመናት በፊት በተለይም እስልምና በምድረ አረቢያ መስፋፋት በጀመረበት ጊዜ የእምነቱ ተከታዮች ጭቆና ሲደርስባቸው የተሰደዱት፣ያኔ አቢሲኒያ ዛሬ ደግሞ ኢትዮጵያ ወደተባለችው አገር እንደነበር ይታወሳል፡፡ በእርግጥም አገራቸውን መልቀቅ ሲገደዱ በሞትና በሕይወት መካከል ሆነው የተሰደዱት፣ ፍትህ ወደማይጎድልበት የኢትዮጵያ ንጉሥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ፣ አሁን ልናስታውሰው ከምንችለው ጊዜ በፊት ጀምሮ የህሊና ነጻነትና ሰብአዊ ክብር የሚከበርባት፣ በማንነታቸው ኮርተው የሚኖሩ ህዝቦች የሚገኙባት አገር እንደሆነች የተመሰከረላት ናት፡፡  
የፕሮፌሰር አብይ ህይወት፣ ነጻነት ያለው ህዝብ፣የተለያየ ዘርና ባህል ቢኖረውም እንዴት አብሮ መኖር እንደሚችል ያስታውሰናል፡፡ ለመሆኑ አብይ ፎርድ ማን ናቸው?
ማንነታቸውን በአጭሩ ለማስቀመጥ ይቻል እንደሆነ በአባታቸው የታላቁ ሙዚቀኛ፣ የሃይማኖት ፍልስፍና ሊቅ፣ ራባይ (ይሁዳዊ ጳጳስ)፣ የአስተማሪውና የስነ ልሳኑ ሊቅ የአርኖልድ ጆሲያህ ፎርድ እና በእናታቸው የታላቋ መምህር፣ የሙዚቀኛዋ፣ የመጋቢ ዕውቀቷ፣ የቴኒስ ጨዋታ አሰልጣኟ፣ በኢትዮጵያ ቀዳሚ የስካውት መሪዋ ሚኒዮን ሎራይን ኢኒስ ልጅ ናቸው፡፡ አብይ ፎርድና ወንድማቸው ዮሴፍ ፎርድ፣ በኢትዮጵያ በተቋቋመው ቦይስካውት ከግምባር ቀደምቱ ወጣቶች የሚሰለፉ ሲሆን በኋላም ‹‹ፈጣሪንና አገሬን፣ ሕጓን አክብሬ፣ በታማኝነት (ያለ ወገንተኝነት) ለማገልገል ቃል እገባለሁ›› ብለው በመሃላ ያረጋገጡ የስካውት መሪዎች ናቸው፡፡ ዛሬ እኔም እኒህን ታላቅ ሰው በመንፈስ የምሰናበተው፤ ለእናት አገሬ፣ ሕጓን አክብሬ፣ በመሃላ ባረጋገጥኩላትና ለብሸው በነበረው የስካውት አርማ ላይ ሦስት ጣቶቻቸውን በማውጣትና እስከ ትከሻዬ ከፍ በማድረግ ነው፡፡
እንደሚታወቀው ሁሉ የፕሮፌሰር  አብይ እናት ወይዘሮ ሚኒዮን ሎራይን ኢኒስ፣ ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረራ ይዞ በነበረበት ጊዜ፣ ያኔ ልዕልት ዘነበ ወርቅ ተብሎ በሚጠራው ትምህርት ቤት፣ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ከትምህርት እንዳይርቁ ያልተቆጠበ ጥረት ያደርጉ  ነበር፡፡ የቋንቋና የሙዚቃ አስተማሪ የነበሩት አባታቸው የሞቱት በ1935 ዓ.ም ሲሆን የተቀበሩትም አዲስ አበባ ውስጥ ነበር፡፡ እኒህ የጥንታዊ ዝርያዎቼ አገር ኢትዮጵያ ናት ብለው የመጡ ታላቅ ሰው (የፕሮፌሰር አብይ አባት) ዕድሜያቸው በአጭሩ ቢቀጭም፣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ መዝሙር የደረሱ፣ እርሳቸው የደረሱት ብሔራዊ መዝሙርም ያኔ ‹‹Universal Negro Improvement Association [UNIA] in 1920›› ለተባለው ንቅናቄ፣ መዝሙር እንዲሆን ያበቁ ታላቅ ሰው ነበሩ፡፡  
ፕሮፌሰር አብይ፣ የአባትና የእናታቸውን ፈለግ በመከተል የመጀመሪያውን ዲግሪያቸውን ያገኙት ኒውዮርክ በሚገኘው በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን በአሜሪካ ውስጥም የአየር ኃይል አባል በመሆን በጦር አይሮፕላን አብራሪነት አገልግለዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ባለ አንድ ኢንጅን የሆነች አይሮፕላን በመግዛት፣በሙያው መሠማራት ለሚፈልጉ አሰልጣኝ ሆነው ነበር፡፡ ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው ሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ፣ አንጋፋ ፕሮፌሰር ሆነው እየሠሩም፣ የተወለዱባት አገር ኢትዮጵያ፣ የጀመረችውን የህዳሴ ጉዞ እዳር ታደርሰው ዘንድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ ዕውቀትና ልምዳቸውን ከ2007 ወዲህ በማካፈል፣ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማድረግ ጥረት ያደረጉ ሰው ናቸው፡፡
ከራስ ወዳድነት ስሜት የራቁት ፕሮፌሰር አቢይ፤ ሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ የፊልም ጥበብ፣ የሬዲዮና ቴሌቪዥን ጋዜጠኝነት እንዲሁም የስነጥበብ ዕውቀት ጮራ የሚፈነጥቅበት ትምህርት ቤት እንዲሆን ለአርባ ዓመታት ያልተቋረጠ ጥረት እንዳደረጉትና በርካታ አፍሪካውያንንና ትውልደ አሜሪካ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን ለጋዜጠኝነት ሙያ እንዳበቁት ሁሉ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ነጻ የጋዜጠኝነት ሥራ ይስፋፋ ዘንድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡  
ፕሮፌሰር አብይ፣ በፈጠራ ጥበብ ላይ የተመሠረተ ሥርዓተ ትምህርት ያላቸው፣ ለሀገር እድገት ከፍተኛ ተስፋ የሚጣልባቸው የስነጥበብ ከፍተኛ ትምህርት ቤቶች በኢትዮጵያ እውን እንዲሆኑ የነበራቸውን የራዕይ ጥልቀት መለካት አስቸጋሪ ቢሆንም፣ በተራ አገላለጽ ‹‹ከጥልቅ ስሜት፣ ከጥልቅ ማስተዋል፣ ከጥልቅ አመለካከት፣ መንፈስን ጨምድዶ ከሚያዝ ጥልቅ አስተሳሰብ የመነጨ ነው›› ለማለት ይቻል ይሆናል።  በ2006 ዓ.ም  በጡረታ ከመገለላቸው በፊትም በሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ ከሚገኙ ጥቂት የትምህርት ፋኩልቲዎች ጋር በመተባበር፣ በኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የስነጥበብ ዕውቀት እንዲሰጥ የሚያስችል ሥርዓተ ትምህርት ለመዘርጋት የተሳካ ሙከራ ማድረጋቸው አይዘነጋም፡፡   
ፕሮፌሰር  አብይ ወጣት የፊልም ባለሙያ ኢትዮጵያውያን ስኮላርሺፕ አግኝተው ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ፣ በሌሎች ለአፍሪካውያን ተብለው በተከፈቱ አካዳሚያዊ ዕድሎች እንዲጠቀሙም ያበረታቱ ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከእህት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ግንኙነት መስርቶ ለማየት ከፍተኛ ጉጉት ነበራቸው፡፡  
የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር አንድርያስ እንደገለጹት፤ ‹‹አቢ ለፊልም ሙያ ትምህርት ቤት መቋቋም ከበስተጀርባ ሆኖ የሚገፋ ኃይል ነበር፡፡›› በእርግጥም ወዳጆቻቸውና የሙያ ባልደረቦቻቸው ስለ ወደፊቷ ኢትዮጵያ ፊልም እንዲያስቡ ይገፋፉና ዘወትር ሐሙስ በጁፒተር ሆቴል ፒያኖ እየተጫወቱ ያዝናኑ ነበር፡፡  እኔም ወደ አዲስ አበባ ስመጣና በግል ቤታቸው ብቻ ሳይሆን በዋሺንግተን ዲሲና በአዲስ አበባ በሚዘጋጁ የሙዚቃ ኮንሠርቶች ተጋባዥ ሆኜ የመመልከት ዕድል አጋጥሞኛል፡፡
ፕሮፌሰር  አብይ  ፎርድ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ  ታላቁ ሕልማቸው፣ ከእናታቸው ትምህርት ቤት አጠገብ፣ የአፍሪካ አሜሪካውያን ሙዚየም ተቋቁሞ ማየት ነበር፡፡ ከራስ ወዳድነት ስሜት የራቁና ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ለሚያፈቅሯት ትውልድ ሀገራቸው የሚሠሩ መሆናቸውን የተገነዘቡ ወዳጆቻቸውም፣ ለኢትዮጵያውያን ቤተሰቦቻቸው፣ ለኢትዮጵያን አርበኞች አስፈላጊ ለነበሩት ለኩሩ አፍሮ ካሪቢያውያንና ለአፍሪካ አሜሪካውያን መታሰቢያ የሚሆን ሙዚየም እየገነቡላቸው ነው፡፡  
የሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት አመራር ቦርድም፤ እኒህ ታላቅ ታውልደ ኢትዮጵያዊ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ በክፍል ውስጥና ከዚያም ውጭ፣ በትርፍ ጊዜያቸው ሳይቀር ይሰጡት የነበረው በቅንነት ላይ የተመሠረተ አገልግሎት፣ ለትምህርት እድገት አስፈላጊ እንዲሁም ለተከታዮቻቸው፣ ለወዳጆቻቸውና ለአቻ የሥራ ባልደረቦቻቸው አርአያነት ያለው ተግባር መሆኑን በማመኑ፣ “ዝክረ አብይ ፎርድ” እንዲከበር ወስኗል፡፡ በዚህም አርአያነት የተሞላ ተግባራቸው በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል መልካም ግንኙነት እንዲፈጠር አድርገዋል፡፡ እንደ አንድ አንጋፋ የሬዲዮ፣ የቴሌቪዥንና የፊልም ዲፓርትመንት ፋኩልቲ አባል፣ በዚህ የትምህርት መስክ ለተገኘው እድገት ባበረከቱት አስተዋጽኦ እንዲሁም በታወቁ ጆርናሎች ላይ ባወጡት የምርምር ሥራቸው የፕሮፌሰርነት ማዕረግ አግኝተዋል።
አንጋፋው ፕሮፌሰር  አብይ ፎርድ በሕይወት ዘመናቸው ያካበቱት ዕውቀት ወደ ኢትዮጵያ፣ ቡርኪና ፋሶና ወደ ሌሎችም አፍሪካ ሀገሮች ለሁለት ተከታታይ ዓመታት መጥተው እንዲሠሩ ያስቻላቸው ሲሆን በ2006 ዓ.ም  በጡረታ ከተገለሉ በኋላ እንኳን ሲመኙት የነበረውን ራዕይ ብቃት ያለው ምሁር ሆነው ለማሳካት የቻሉ ታላቅ ሰው ነበሩ፡፡
የሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ ባለአደራ ቦርድም፣ የብዙዎቻችንን ስሜት የሚጋራ ሲሆን  ለልጃቸው ለሚኒባ ፎርድና ለቤተሰቧም በአባቷ ሞት የተሰማውን ልባዊ ሐዘን ገልጧል፡፡   
ፕሮፌሰር አንድሪያስ እሸቴ፤ ‹‹አብይ አፍሮ-ካሪቢያን፣ አፍሪካ አሜሪካውያንና ኢትዮጵያውያውያንን ያስተሳሰረ ሕያው ምስክር ነው›› በማለት ይገልጧቸዋል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር አንድሪያስና ሌሎች ፕሮፌሰር አብይን ለሚያውቁ እንዲሁም ለተማሪዎቻቸው፣ ባልደረቦቻቸው፣ ጓደኞቻቸውና ሙዚቃቸውን ላዳመጡ ሁሉ፣ የእርሳቸው ማሸለብ ለሀገራቸውና ለፓን አፍሪካኒዝም ትልቅ ጉድለት ሆኖ እንደሚሰማቸው አያጠያይቅም፡፡   
ወዳጆቻቸውና ሌሎችም ምሁራን እርሳቸው ወደሚያገለግሉበት ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ መልካም አቀባበል እንደሚደረግላቸው ይሰማቸው ነበር። አስተማሪያቸውና አማካሪያቸው ይሆኑ ዘንድም ይመርጧቸው ነበር፡፡ ከጥንታዊ የጥቁሮች ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ በሆነው ሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያንና የአፍሪካን ታሪክ ሲያስተምሩ ለሚያውቋቸው፣ ሰዎችን የመረዳት፣ በጥንቃቄ የመቀበልና ጥልቀት ያለው ምሁራዊ አስተያየታቸውን፣ ፈገግታቸውንና የሚሰነዝሯቸውን ቃላት መርሳት ከቶ አስቸጋሪ ነው፡፡ እኔም ዓለም አቀፍ ጤናና ልማትን የሚመለከት ትምህርት በዩኒቨርሲቲው ሳስተምር፣ እንደ አንድ የዩኒቨርሰቲው አባል፣ ከእርሳቸው ብዙ የተጋራኋቸው ቁምነገሮች እንዳሉ እርግጥ ነው፡፡፡   
ፕሮፈሰር  አብይ ፎርድ፤ ስካውት ኮትኩቶ ያሳደጋቸው መሆኑን በሚያረጋግጥ መልኩ በመላ ህይወታቸው አዲስ መጭዎች፣ የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም  የሁለተኛና  ሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች፤ ስለ ኢትዮጵያና ፓን አፍሪካኒዝም አስተሳሰብ እንዲማሩ፣ እንዲያውቁና በመላ ሕይወታቸውም ለዚህ የተቀደሰ ተግባር ጥብቅና እንዲቆሙ በትጋት የሰሩ ሲሆን ዳያስፖራዎችም አርአያ ሆነው እንዲገኙ አበክረው ይመክሩ ነበር፡፡ ግልጽነት እንደ ባህል፣ በምንሰጠው ህዝባዊ አገልግሎትና በምናካሂደው ውይይት ልዩነትን በማስወገድ፣ በሰላም አብሮ መኖርን የሚያስገኝ ጤናማ ዴሞክራሲያዊ ባህል በመሆኑ ከፍተኛ ግምት ይሰጡት ነበር፡፡  ምንም እንኳን ፓን አፍሪካኒዝምን በሚመለከት ያለው ክርክር በእርሳቸውና በወላጆቻቸው፣ በዳያስፖራ ወዳጆቻቸውና በጓደኞቻቸው ዘመን ሥር የሰደደ ቢሆንም፣ የሐሳብና ስሜትን የመግለጽ ነጻነት ጉዳይ በተነሳ ቁጥር ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጣልቃ እየገባ፣ እስከ ህይወታቸው ፍጻሜ ድረስ ሲያስቸግራቸው ተስተውሏል፡፡  
ፕሮፌሰር  አብይ ፎርድ በብዙዎቹ ጓደኞቻቸው ዘንድ ሐሳባቸውን ከስሜታዊነት በራቀ መንገድ የሚያቀርቡ፣ ነገሮችን መዝነውና አስተንትነው በጥልቀት የሚያስቡ፣ ለማያምኑበት ነገር ቅን አስተያየታቸውን የሚሰጡ፣ የሚያደርጉትን ነገር ሁሉ መዝነው የሚሠሩ እንደነበሩ ይታወቃሉ፡፡ ሰባኪና አፈ ጉባኤ በመሆን ብዙ ሺህ ማይሎችን ተጉዘዋል፡፡ ከዚህ ሁሉ የበለጠ ግን አፍቃሪ፣ ለሰው ልጅ እንክብካቤ የሚያደርጉ፣ ለቤተሰባቸው የተለየ መውደድ ያደላቸው፣ እንደ ጓደኛም የሚሰማቸውን ለማካፈል ዝግጁ የሆኑ ቅን ሰው ነበሩ፡፡ የሚያውቋቸው ሁሉ የሰለጠነ ባህላቸውን፣ የከተሜ ሰብእናቸውን በአድናቆት ከመግለጥ ተቆጥበው አያውቁም፡፡ ከዚህ ዓለም በሞት በተለዩ ጊዜም ብዙዎች እንባቸውን ያፈሰሱት የሚፈጠረውን ትልቅ ክፍተት በመፍራት ነበር፡፡ እኔም ቤተሰባቸው፣ ጓደኞቻቸው፣ አድናቂዎቻቸው፣ ተማሪዎቻቸው፣ የዩኒቨርሲቲው ታላላቅ ምሁራንና የቦርድ አባላት በተገኙበት ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው በሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው “ዝክረ ፕሮፌሰር አቢይ ፎርድ” ላይ ተገኝቼ፣ ይህን እውነታ ለመመስከር ችያለሁ፡፡
የፕሮፌሰር አቢይ ፎርድ ሌጋሲ፣ የዘራቸው ሐረግ፣ ከቤተሰባቸው የወረሱት የአርበኝነት ስሜት በተቀበሩባት ኢትዮጵያ ምድር ሲታወስ ይኖራል። የተሰማንን ልባዊ ሐዘን ለልጃቸው ለሚኒያቢና ለልጅ ልጃቸው ፋሲል እየገለጽን፤ የፕሮፌሰሩን ችቦ ተቀብለው እንዲያበሩ፣ በትምህርቱ መስክ የጀመሩትን መልካም ሥራም ተክተው እንዲያከናውኑ ከልብ እንመኛለን፡፡
(ተጻፈ በፕሮፌሰር አሕመድ ዓብዱላሂ ሞኢን (DrPH, MPH, MHA) ሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ፣ ዋሺንግቶን ዲሲ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ)


    ሩሲያውያን አንድ ተረት አላቸው፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ንጉሥ በዋናው ከተማ ውስጥ እየተዘዋወረ ሳለ የጣት ቀለበቱ ይጠፋበታል፡፡ ወዲያው በጋዜጣ ላይ ማስታወቂያ ያወጣል፡፡ “የጣት ቀለበቴን አግኝቶ ላመጣልኝ ሰው ወሮታውን እከፍላለሁ” የሚል ነው ማስታወቂያው፡፡ አንድ ተራ ወታደር ዕድለኛ ሆነና ቀለበቱን አገኘ፡፡ “ምን ባደርግ ይሻላል” ሲል አሰበ፡፡ “ወደ ዋናው ጦር ክፍሌ ሄጄ ሪፖርት ባደርግ ጉዳዩ ወደ በላይ ይመራል፡፡ እያንዳንዱ የበላይ የራሱ የበላይ አለው። ስለዚህ ወደ በላይ ይመራዋል፡፡
ሃምሣ አለቃው ለመቶ አለቃው፤ መቶ አለቃው ለሻምበሉ፤ ሻምበሉ ለሻለቃው፣ ሻለቃው ለኮሎኔሉ፣ ኮሎኔሉ ለብርጋዲየር ጄኔራሉ እያለ ማለቂያ በሌለው የዕዝ ሰንሰለት ውስጥ ሲቀባበሉት መኖሩ ነው፡፡ ስለዚህ በቀጥታ ወደ ንጉሱ ሄጄ ቀለበቱን ባስረክባቸው ይሻላል” ብሎ ይወስናል፡፡
ወደ ቤተ መንግሥቱ ይመጣል፡፡
የጥበቃ መኰንኑ፤ “እዚህ ምን ልታደርግ መጣህ?” ይለዋል፡፡
“የንጉሱን የጣት ቀለበት አግኝቼ ለማስረከብ ነው የመጣሁት” ይለዋል ተራ ወታደሩ፡፡
“በጣም ጥሩ ነው ወዳጄ፡፡ ለንጉሱ እነግርልሃለሁ፡፡ ነገር ግን በአንድ ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡ ይኸውም ንጉሱ ቀለበቱን ስላገኘህላቸው ከሚሸልሙህ ነገር ግማሹን ለእኔ የምትሰጠኝ ከሆነ ነው፡፡ ተራ ወታደሩም በሆዱ፤
“ወቸ ጉድ! በዕድሜዬ ዛሬ አንድ መልካም ዕድል ቢገጥመኝ፤ እሷኑ የሚቀራመተኝ አዘዘብኝ፡፡ ግን ይሁን ግዴለም፡፡ ይካፈለኝ” ይልና ወደ ጥበቃ መኮንኑ ዞሮ፤ “ይሁን ከሽልማቱ ግማሹን ላካፍልህ እስማማለሁ፡፡ ነገር ግን በአንድ ቅድመ - ሁኔታ ነው” ይለዋል፡፡
“ምንድነው ቅድመ ሁኔታው?” ሲል ይጠይቃል፤ የጥበቃ መኮንኑ፡፡
“ከማገኘው ሽልማት ግማሹን አንተ፤ ግማሹን እኔ እንደምወስድ የሚገልጽ ማስታወሻ ፃፍልኝ” ሲል ይጠይቃል።
የጥበቃ መኮንኑ ማስታሻውን ጽፎ ይሰጠዋል፡፡ ከዚያም ሄዶ ለንጉሱ ቀለበቱን ያገኘ ሰው መምጣቱን ይናገራል። ንጉሱም ቀለበታቸውን ስለማግኘቱ ያን ተራ ወታደር እጅግ አድርገው ያመሰግኑትና፤
“በጣም አመሰግናለሁ ጀግና ወታደር! ሁለት ሺህ ብር በሽልማት መልክ ሰጥቼሃለሁ” ይሉታል፡፡
“የለም ንጉሥ ሆይ፤ ለወታደር የሚገባው ሽልማት ሁለት ሺ ብር ሳይሆን ሁለት ሺ ጅራፍ ነው፡፡” ይላል፡፡
ንጉሡም እየሳቁ፤
“ምን ያለው ጅል ነው?” ብለው “እሺ ጅራፉ ይምጣ” አሉና አዘዙ፡፡
ተራ ወታደሩ ልብሱን ማወላለቅ ሲጀምር፣ በድንገት አንዲት ወረቀት ዱብ ትላለች፡፡
“የምን ወረቀት ነው እሱ?” ሲሉ ይጠይቃሉ ንጉሱ፡፡
“ንጉሥ ሆይ፤ ይህ ማስታወሻ የሽልማቴን ግማሹን፣ የጥበቃ መኮንንዎ እንዲወስድ የተስማማንበትን ውል የሚጠቁም ነው”
ንጉሱ ሳቁና የጥበቃ መኮንኑን አስጠሩት፡፡ ከዚያም “እንግዲህ መቶው ጅራፍ ያንተ ነው ማለት ነው” አሉት፡፡
ቀጥሎም የጥበቃ መኮንኑን በጅራፍ፣ ገራፊው ይገርፈው ጀመር፡፡ የመጨረሻው አሥር ጅራፍ እንደቀረ ያ ተራ ወታደር ወደ ንጉሱ ጆሮ ጠጋ ብሎ፤ “ንጉሥ ሆይ፤ እኔ እንደሱ ስስታም ሰው አይደለሁም፤ የቀረውን ግማሹን ሽልማቴንም ሰጥቼዋለሁ!” ይላቸዋል፡፡
“እንዴት ያለህ ደግ ሰው ነህ ጃል” አሉና ንጉሡ፤ የጥበቃ መኮንኑ ሌላውን የጅራፍ ሽልማት እንዲወስድ አዘዙ። ያ የጥበቃ መኮንን በእምብርክኩ እስኪሄድ ድረስ ተለጠለጠ፡፡
ከዚያም ንጉሱ ተራ ወታደሩን ጠሩና፤ “በል ከዛሬ ጀምሮ ከሥራ መደብህ በክብር ተባረሃል፡፡ ለመቋቋሚያ ይሆንህ ዘንድ ሶስት ሺ ብር ተሸልመሃል?” አሉና አሰናበቱት፡፡
*   *   *
ከበላይ ወደ በላይ ሲመራ ከሚውል ጉዳይ ይሰውረን፡፡ በየደረጃው ሽልማትህን አካፍለኝ ከሚሉም ያውጣን! ለበቀል ብለን የመዘዝነው ጅራፍ በራሳችን ላይ እንደሚዞር ማስተዋያ ልቦና አያሳጣን፡፡ ባሳበቅንበት ሊሳበቅብን፣ ባስቀጣነው ልንቀጣ፣ ባጨበጨብንበት ሊጨበጨብብን እንደሚችል፤ በጭራሽ አንዘንጋ፡፡
“አፈር ወስዶ ብለን፣ ያማረርነው አባይ
የሚያጨበጭብ ሰው፣ ይዞ ነጐደ ወይ?”
አለ አሉ ገጣሚ፤ ሆይ ሆይ ሲል ውሃ የወሰደውን ሰው አይቶ፡፡ እንሸለም ብለን ሌላውን መጉዳት ውሎ አድሮ የከፋ ጉዳት ወደ ማስተናገድ ሊያመራ እንደሚችል ዐይናችንን ገልጠን እንይ፡፡ ተማርን የምንል፣ ሥልጣን ላይ ያለን፣ በሞቅ ሞቅ ሙስናችንን ለመሸፈን የምንፍጨረጨር፣ የባለቤቱ ልጅ ነን የምንል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ፊታችን ያለው እየወደቀ እያየን፣ እኔን አይመለከትም እያልን የምንስቅ “አቤቱ ወደ ፈተናም አታግባን” ብንል ይሻላል፡፡
አንድ አዛውንት “በዚህ ዘመን ዘርዛራ ወንፊት፣ ቀጥሎ ጠቅጣቃ ወንፊት መኖሩን አዳሜ አያውቅም፤ ከዘርዛራው ወንፊት ያመለጠው፣ በጠቅጣቃው ወንፊት የተያዘውን እየሰደበና እያዋረደ ብዙ የሚቆይ ይመስለዋል” ሲሉ ስለ ስብሰባዎች ተናግረዋል፡
አንዱ ባንዱ ሲስቅ ጀምበር ጥልቅ አለ ነው ነገሩ፡፡
በሰው ገንዘብ፣ በሰው ንብረት ላይ መፍረድ ቀላል ነው፡፡ እርዳታ ላያደርጉ ይሄ ይሁን፣ ይሄ አይሁን ማለትም እጅግ ቀላል ነው፡፡ የማያግዝ “ቤቱን አስፍታችሁ ሥሩ” ይላል፤ እንደተባለው ነው፡፡
ሳናወያይና ሳናጠና መመሪያ አናውጣ፡፡ ሳናስብ አንናገር፡፡ ከተናገርን አንፈር፡፡ ካፈርኩ አይመልሰን ብለንም በግትርነት አንደንፋ፡፡ ላወቅነውና ላለምነው ጉዞ በልባምነት እንገስግስ፡፡
አለቃ ተክለየሱስ ዋቅጅራ የተባሉ ደራሲ፤ “የጐጃም ትውልድ በሙሉ፤ ከአባይ እስከ አባይ” በተባለ መጽሐፋቸው፤ “የማኖ የላስታ ሰው ነው፡፡ ጀግና ፈረሰኛ ነበር፡፡ ሥነፀሐይን ሲያጭ “ምን ገንዘብ አለህ” ቢሉት፤ “ልብና ፈረስ አለኝ” አለ፤ አሉ፡፡ ዓላማ ያለው፣ ለሀገርና ለህዝብ አሳቢ የሆነ ሰው ልብና ፈረስ ያስፈልገዋል፡፡ በቀላሉ ተስፋ መቁረጥ የለበትም፡፡ አርቆ አስተዋይ ሊሆን ይገባል፡፡ የዛሬን ብቻ ሳይሆን የነግ ተነግወዲያውን ሊያሰላ፣ ሊያሰላስል ያሻል፡፡ ዕድገትና ብልጽግና የዚህ መርህ የልጅ ልጆች ናቸው፡፡ መልካም አስተዳደር ይኑር፡፡
ፍትሕ አይጓደል፤ የግለሰብም ሆነ የቡድን ወገናዊነት ይውደም፤ ሙስና ይወገድ፣ የዲሞክራሲ መብቶች ይከበሩ እየተባለ ነጋ ጠባ የሚወተወተው ለአንድ ሀገራችን ዕድገት እንጂ ጥቂቶች የሚያወለውሉባትና ብዙሃን በአጥንታቸው የሚሄዱባት አገር ትሆን ዘንድ አደለም፡፡ ያውም ለሀብታሞቹ እንኳ ባልተመቸው በአሁኑ ዓለም!!
ፕሮፌሰር ሳች የተባሉ ምሁር “በዛሬ ጊዜ፤ ሀብታሞቹ የአናሳ ፍትሕና የተትረፈረፈ አለመረጋጋት ሰለባ ይሆናሉ (A Less Just and more unstable world) የሚሉትን አባባል በጥሞና ማውጣት ማውረድም ይኖርብናል፡፡ ፍርሃትንና የደህንነት ምቾት ማጣትን የምንቋቋምበት ሥርዓት መፍጠር ይኖርብናል፡፡ “የተገደበውን የፖለቲካ መንቀሳቀሻ ሥፍራ የሚተካ/የሚያካክስ መላወሻ ሜዳ መፈጠር አለበት” እንደሚለን ማለት ነው፤ ፒተር ጊልስ፡፡ ዛሬ እንደ ዋዛ የዘጋነው በር ነገ ከናካቴው ተከርችሞ፤ ቆላፊውም ተቆላፊውም መንገድ እንዳያጡ ስጋቱን መግለፁ ነው፡፡
በጥቃቅን እርምጃዎቻችን ከባባድ ለውጥ ያመጣን አስመስለን ከማጋነን መቆጠብ ይኖርብናል፡፡ ችግሮቻችን ዝሆን አከል ናቸው፡፡ የዝሆንን ግዙፍ አካል እለካለሁ ብላ እንደተነሳችው ጉንዳን እንዳንሆን መጠንቀቅ ተገቢ ነው። ሥር - ነቀልና ሥር የያዘ ለውጥ እያመጣን መሆኑን እያስረገጥን መጓዝ አለብን፡፡ በዚያው በትላንቱ ልባችንና አካሄዳችን እያለምን፤ ዛሬን አዲስ ነው ብለን ለማሳየት መሞከር፤ “ኖሮ በይው ልብሱን፣ ሰውዬውስ የቅድሙ ነው” እንደሚባለው የጉራጊኛ ተረት ይሆናል፡፡ Old wine in a new bottle እንደሚሉት መሆኑ ነው ፈረንጆቹ፡፡

ሰዓሊ ታምራት ስልጣን ተወልዶ ያደገው እዚህ አዲስ አበባ ልደታ አካባቢ ነው፡፡ በልጅነቱ የእናቱን የስፌት ጥበብ እያየ ይመሰጥ እንደነበር የሚያስታውሰው ሰዓሊ ታምራት፤ ወደ ስዕል ሙያ እንዲገባ ያነሳሳውም የእናቱ የስፌት አሰራር እንደሆነ ይገልፃል፡፡  በ1988 ዓ.ም  በአዲስ አበባ ጥበብና ዲዛይን ት/ቤት ገብቶ፣ የ4 ዓመት ትምህርቱን ቢያጠናቅቅም የስዕል ሙያን የሙሉ ጊዜ ሥራው ያደረገው ግን ዘግይቶ ነው- ከዓመታት በኋላ፡፡ ሰዓሊው እስከ ዛሬ በቡድን 20፣ በግሉ ደግሞ 5 የስዕል አውደርዕዮችን በአገር ውስጥና በውጭ አገራት ለእይታ አብቅቷል፡፡ በተለይ “አፈርሳታ የተሰኘው” አውደርዕዩ ከፍተኛ አድናቆትን እንዳስገኘለት ይናገራል፡፡
በዛሬው ዕለት ደግሞ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የኢትዮጵያ እናቶችና የመክተፊያ መስተጋብርን የሚያሳይ የስዕል አውደ ርዕይ ይከፍታል፡፡
 የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ፤ በሙያ ህይወቱ፣ በአውደርዕዮቹ፣ በስዕል ገበያና…  ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከሰዓሊ ታምራት ጋር ተከታዩን ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡

   የእናትህ ስፌት እንዴት ለስዕል ሙያ እንዳነሳሳህ አጫውተኝ ….
ሁሌም እናቴ ስፌት ስትሰፋ አያታለሁ፡፡፡ ከእናቴ ጋር ያለኝ ቅርበት በጣም የጠበቀ ነው፡፡  ስፌቶቹን ገና ስትጀምር የምትሰራውን ውጥን አይና፣ እያደገ ሄዶ የሚይዘው ቅርፅ ይገርመኝ ነበር፡፡ ከዚያ ቀለም የሚያቀልሙት ስንደዶና አክርማ (አለላ) በስፌቱ ላይ ቅርፅ እየያዘ ይመጣል፡፡ እርግጥ እናቶች ስፌት ሲሰፉ በቀላሉ ቆጥረው ነው ዲዛይኑን የሚሰሩት፡፡ ያ ነገር ቀልቤን ይስበዋል፡፡ አንዳንዴም እናቴ ውጥኑን ወጥና ስትሰጠኝ እሰፋ ነበር፡፡ ለቤቱ የመጀመሪያ ልጅ እንደመሆኔ የተሻለ ነፃነት ነበረኝ፡፡  ክረምት ላይ በተገዛልኝ ጥቁር ሰሌዳ ላይ ስዕል መሳል… በጠመኔ መሞነጫጨር ጀመርኩኝ፡፡ ለአዲስ ዓመት አበባ እያልን በየቤቱ የምናዞረውን ስዕልም እስል ነበር፡፡ መሳል ብቻ ሳይሆን ከመርካቶ ቀለም ገዝቼና ንድፍ ሰርቼ፣ በካርቦን ኮፒ እያደረግሁ ለሰፈር ልጆች እሸጥ ነበር፡፡ ለዚሁ ሁሉ ግን መነሻዬ እናቴ የምትሰፋው ስፌት ነው፡፡
ከስዕል ት/ቤት ተመርቀህ እንደወጣህ ወደ ስዕል ሙያ ገባህ?
ሙሉ ለሙሉ ወደ ስዕል ሙያ አልገባሁም ነበር። ግማሽ ጊዜዬን ለኑሮ ገቢ የሚያመጣ ስራ እየሰራሁ፣ በግማሹ ጊዜዬ ነበር የምስለው፡፡ ምክንያቱም የኑሮ ጥያቄዎችን ለመመለስ ሌላ ስራ መስራት ነበረብኝ። የመጀመሪዎቹን ሁለት ዓመታት ተቀጥሬ ሰራሁ። ከዚያም የራሴን የህትመት ቤት ከፍቼ መስራት ጀመርኩኝ፡፡ ቀስ በቀስ ነው፣ የሙሉ ጊዜ ሰዓሊ የሆንኩት፡፡
“አፈርሳታ” የተሰኘው አውደ ርዕይህ አድናቆት አትርፎልሃል፡፡ እስቲ ስለ እሱ ንገረኝ?
“አፈርሳታ”ን ያሳሰበኝ ለተፈጥሮ ቅርብ መሆኔ ይመስለኛል፡፡ በነገራችን ላይ ተፈጥሮን የምንረዳበት መንገድ ቢለያይም ሁላችንም ለተፈጥሮ ቅርቦች ነን፡፡ አንድ ሰው መኖር ይፈልጋል፡፡ ለመኖር ደግሞ አካባቢውንና ተፈጥሮን መረዳት አለበት። ከተረዳን በኋላ የእኔ አበርክቶ ምንድነው የሚለው ሀሳብ ይመጣል፡፡ ለምሳሌ እኛ ቡድን አለን፤ ተራራ እንወጣለን፣ ጫካ ውስጥ እናድራለን፡፡ ይሄ ከተፈጥሮ ጋር ያለንን ግንኙነት ያጠናክረዋል፡፡ የሆነ ጫካ ቦታ ስትሄጂ፣ ዛፍ ስር ነው አረፍ የምትይው፤ ስለዚህ ዛፍ ማረፊያም ነው፡፡ አፈርሳታ በገጠር አካባቢ እቃ ሲጠፋ አውጫጭኝ የሚደረግበት ሥርዓት ነው፤ ዛፍ ስር ነው የሚደረገው፤ እንደ ፍርድ ቤትም ልታይው ትችያለሽ። ተፈጥሮና የሰው ልጅ ያላቸውን ቅርበት ተመልከቺ። በአፈርሳታ ሌባ ይለያል፤ ያጠፋ ይቀጣል፡፡ አካባቢያዊ ሥርዓትን ማክበርና ለዚያ መገዛት፣ የመኖር መሰረት ነው። በዚህ እሳቤ ተነስቼ ነው “አፈርሳታ”ን ያዘጋጅሁት፡፡ ጥሩ ተቀባይነት አስገኝቶልኛል፡፡
አንተ የመሃል ልደታ ልጅ ነህ፡፡ እንዴት ስለ አፈርሳታ በጥልቀት አወቅክ?
ትክክል ነው፤ የከተማ ልጅ ነኝ፤ ልደታ ነው የተወለድኩት፤ ነገር ግን በአገሪቱ ላይ የሚደረጉና የሚካሄዱ ባህላዊና ትውፊታዊ ነገሮችን ለማወቅ የግድ ገጠር መወለድ ላያስፈልግ ይችላል፡፡ አሁን ላይ ወቅቱና ሁኔታው አጠፋቸው እንጂ አሮጌው ኤርፖርት ወንዙ አካባቢ ትልቅ ጫካ ነበር፡፡ ጅብ ሁሉ ይጮህ ነበር፡፡ ልጅ ሆነን ዳክዬ ዋና የሚባል ቦታም እንዋኝ ነበር፡፡ በወቅቱ የገጠር ስሜትን የሚፈጥር ድባብ ነበረው፡፡ ማህበረሰቡም መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ያለው፣ ግን ተቀራርቦና ተጋግዞ የሚኖርበት በመሆኑ፣ ሁሉን ነገር አውቀሽ የምታድሪበት ነው፡፡ እነዛ ስሜቶች የሚፈጥሩብሽ ነገር በውስጥሽ ይቀራል፡፡ ከዚያ ደግሞ የተለያዩ ታሪኮች ታነቢያለሽ፡፡ ድራማ ታያለሽ፡፡ ድራማውን ወይም ታሪኩን ከአካባቢሽ… ከአደግሽበት ዛፍ ጋር ታገናኚዋለሽ፡፡ አፈርሳታም የእነዚህ እሳቤዎች ውጤት ነው፡፡ አፈርሳታን ሳዘጋጅ ብሄረፅጌ መናፈሻ እየሄድኩ፣ ንድፍ እሰራ ነበር፤ የዛፎቹን ባህሪ አጠና ነበር፡፡ ከአንድ ዛፍ ብቻ ብዙ አይነት ባህሪን ታገኛለች፡፡ ዛፉ በክረምት፣ በበጋና በሌላ ወቅት ያለው ባህሪ ምንድን ነው? ቀለሙ ምን ይመስላል? ቅርንጫፎቹና ቅጠሎቹ እንዴት ይሆናሉ? በክረምት ውሃ አዝሎ ሲያብጥ፣ ከዚያ አልጌ ሲይዝ… የተለያየ አርት አለው፡፡ በሌላ አቅጣጫ ዞረሽ ያንኑ ዛፍ ብትመለከቺ፣ ሌላ አይነት ነው፡፡ ስለ መስመሮች ለምሳሌ፡- ስለ ቨርቲካል ሆሪዞንታል እናስብ ብንል፣ በዛፍ ላይ እነዛ መስመሮች በቅርንጫፍም በቅጠልም ምክንያት ይሰበራሉ ወይም ይቋረጣሉ እንጂ ቀጥ ብለው አይሄዱም። በዚህ ምክንያት “ተፈጥሮ ልክ ነው” የሚለውን ግንዛቤ ትወስጃለሽ፡፡ ቨርቲካልና ሆሪዞንታል መስመሮች የሌሉበት ተፈጥሮ ደግሞ ብዙ ጊዜ እረፍት አለው፡፡
“ጥላ” ስለተሰኘው አውደ ርዕይም ብዙ ሲነገር ሰምቻለሁ… እስቲ ስለሱ ንገረኝ?
ጃንጥላ በእኛ ማህበረሰብ ውስጥም ሆነ በሌላው ዓለም ያለው ሚና በወቅት እንኳን የተገደበ አይደለም፡፡ በተለይ ከገጠር እስከ ከተማ ያለው አገልግሎት ከፍተኛ ነው፡፡ ይህ እንደ መከላከያ የምንጠቀምበት እቃ ስም እስከመሆን ደርሶ፣ አንድ ለእኛ ጠቃሚ ደጋፊ የሆነን ሰው ጥላዬ ጥላሁን ብለን እንሰይማለን፡፡ ይህንን ለማንፀባረቅ ሞክሬያለሁ፡፡ ሌላው “ዩኒቲ” በተሰኘው ስራዬ በኢትዮጰያ ንግድ ባንክ ልደታ ቅርንጫፍ፣ አዲስ በተሰራው ህንፃ፣ ስራዬ አለ በዚህ  ህንፃ ላይ የሚታየው፣ ጥላው ዋና መጠለያ ሆኖ፣  የተለያየ ቁመትና ውፍረት ያላቸው ዛፎች በስሩ አሉ፡፡ ይሄ እንግዲህ የተለያየ አቅም እውቀትና ሃብት ቢኖረንም ከተባበርን መቆም እንችላለን የሚለውን ለማሳየት ነው፡፡
ቅዳሜ (ዛሬ ማለት ነው) በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የሚከፈት “መክተፏያ” የተሰኘ የስዕል አውደ ርዕይ አዘጋጅተሃል?
ቀደም ብዬ እንደነገርኩሽ ከእናቴ ጋር ያለኝ ቁርኝትና ስሜት የጠበቀ ነው፡፡ እናቴ ደግሞ እቃ አረጀ አበቃለት ብላ አትጥልም፤ ያው ከድሮ ሰዎች አንዷ ናትና፡፡ እዚህ ፊት ለፊትሽ የምትመለከቻት መሃሏ ሳስቶ የተበሳችና የተሰነጠቀች መክተፊያ (ቃለ ምልልሱ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ውስጥ ነው የተደረገው) እኔ ሳድግ ከበላሁባቸው ወይም ከበላኋቸው አንዷ ናት፡፡
ከበላኋቸው ስትል ምን ማለትህ ነው?
ያው መክተፊያው የሚጎደጉደው፣ የሚሳሳውና የሚበሳው በቢላዋው አማካኝነት አብሮ እየተፋቀና ከምግብ ጋር እየተቀላቀለ ወደ ሆዳችን ስለሚገባ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ መክተፊያ በልቼበታለሁም፤ በልቼዋለሁም ማለት ነው፡፡ አንድ ቀን መክተፊያዋን ሳያት የሃሳብ መነሻዬ ሆነች፡፡ ከዚያ ማሰላሰል ጀመርኩኝ። እያሰብኩ ማስታወሻ እየያዝኩ ቆየሁና ሙሉ በሙሉ ማተኮር እንዳለብኝ ወሰንኩ፡፡ ከመክተፊያው ጋር አብራ ያለችው ሴት ህይወትም ታሰበኝ፡፡ ከዛ በኋላ ከእናቴም ከሌሎችም መክተፊያዎችን ሰብስቤ፣ ስቱዲዮ አስቀምጬ ማየት፣ ማሰብና ከጓደኞቼ ጋር መወያየት ስጀምር፣ ሃሳቡ እያደገና እየዳበረ መጥቶ እዚህ ደረሰ፡፡
አሮጌና የጎደጎደ መክተፊያ እየዞርክ ስትሰበስብ… ችግር አልገጠመህም?
ገጥሞኛል፡፡ እንደውም ከመጥፎ አምልኮ ጋር ያገናኙትም ነበሩ፡፡ መክተፊያዎቹን በስጦታም በግዢም ነው የሰበሰብኳቸው፡፡ አንድ የታክሲ ሹፌርም ፍላጎቴን አይቶና ገርሞት መክተፊያ አምጥቶልኛል፡፡ በዚህ ኤግዚቢሽን ለማሳየት የምሞክረው ሁሌም ሰዎች ተሰናድቶና አልቆ የቀረበ ምግብ ላይ ደስተኞች ነን፡፡ ነገር ግን ከጀርባ ያለውን ለመስራት የሚያስፈልገውን ነገር ማሰብ አንፈልግም፡፡ ምግብ ከእናት ማህፀን እስከ ዕለተ ሞት ከኛ ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ የምንኖረው በምግብ ነው። መክተፊያና ምግብ በምሳሌነት አነሳሁ እንጂ በሁሉም የስራ መስክ አሰሪዎችም የላቀና የተጠናቀቀ ስራ ሲያዩ ደስ ይላቸዋል፡፡ ያ ሰው እንዴት አድርጎ  እንደሰራው፤ እንዴት እንደወጣና እንደወረደ ግን ማሰብ አይፈልጉም። መክተፊያና የኢትዮጵያ እናቶች… ምግብ ተሰርቶ  እስኪቀርብ የሚያዩትን ፈተና ማሰብ፣ ትኩረት መስጠት የተለመደ አይደለም፡፡
በሌላው አለም የስዕል ሙያ ከኑሮ መተዳደርያም አልፎ ያበለፅጋል፡፡ እኛ አገር አሁንም ድረስ “እንጀራ” መሆን አልቻለም፡፡ ለምንድ ነው ትላለህ?
ያነሳሽው ሃሳብ በጣም ሰፊ ነው፤ በአጭር ሰዓት ለመተንተንም ከባድ ነው፡፡ ነገር ግን እኔ በገባኝ መጠን ለመመለስ ልሞክር፡፡ ስዕል በሌላው ዓለም ከታሪክም አኳያ ወደ ኋላ ርቀን ስንመለስ ብዙ ነገር አለው፡፡ ለምሳሌ በ14ኛ ክ/ዘመን (ዘመነ ትንሳኤ የሚባለውን) ብዙዎቹ ለአውሮፓ ስልጣኔ ፈር የቀደዱበት ዘመን ነበር፡፡ ከዛ ቀጥሎ ነው የኢንዱስትሪ አብዮት ሲመጣ፣ ከአርቲስቶቹ የመጡ ሃሳቦች ከስነ ህንፃ ጋርም የተያያዙ እሳቤዎች ናቸው ይሄንን ዘመን የገነቡልን፡፡ እንደውም አንድ ሃሳቤን የምትገልፅልኝን ጥቅስ ልንገርሽ፡፡ መድኃኒዓለም አጠቃላይ ሁለተኛ ት/ቤት ውስጥ በሚገኘው የስዕል ት/ቤት እማር ነበር፡፡  የስዕል ክፍል በር ላይ፡- “የፊዚክስና ኬምስትሪ ሳይንስ ባልነበሩበት ዘመን፣ ስነ -ጥበብና ዕደ ጥበብ ነበሩ” ትላለች፡፡ ስነ ጥበብና ዕደ ጥበብ ናቸው፣ ፊዚክስና ኬሚስትሪን ያመጡት፡፡ እኔ ሳይንስ አካዳሚ መጥቼ ይህንን አውደ ርዕይ ሳሳይ፣ በዚህ ማዕከል ብዙ ፕሮፌሰሮችና ዶክተሮች አሉ፡፡ ይህንን ሀሳብ ይዘሽ ስትመጪ፣ እነዚህ ሰዎች “ስዕል ውስጥም ለካ ሃሳብ አለ” የሚለውን ይገነዘባሉ፡፡ እኔ ወደነሱ ሄጄ ሀሳቤን እነሱ ላይ አጋባለሁ፤ ይሄን ኃላፊነቴን ተወጣሁ ማለት ነው፡፡ ሌሎችም በዚህ መልኩ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት፣ ወደ እነሱ የሚመጣን ነገር ከመጠበቅ እነሱ መሄድ አለባቸው ማለት ነው፡፡ በዚህ መልኩ ግንዛቤውን መፍጠር ካልቻልን፣ ስዕልን የሙሉ ሰዓት ስራ አድርገን ለመኖር መቸገራችን ይቀጥላል፡፡ እኔም የሙሉ ሰዓት ሰዓሊ ለመሆን የፈጀብኝን ጊዜ ቀደም ብዬ ነግሬሻለሁ። አመርቂ አይደለም፡፡ ገና ብዙ መሰራት አለበት። አሁንም ስዕልን ከግድግዳ ጌጥነትና ማድመቂያነት ባለፈ ውስጡ ሃሳብ እንዳለ የሚረዱ ጥቂቶች ናቸው፡፡
እኔ “አፈርሳታ”ን ከዛፍና ከማህበረሰብ ዕሴት ጋር አያይዤ ስሰራ፣ ቅጥ ያጣው የከተማው ግንባታ እያመጣ ያለውን ችግርም በማሰብ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ለአገር ይጠቅማል ብለሽ ሀሳብ ይዘሽ የሆነ የሚመለከተው መስሪያ ቤት ስትሄጂ፣ “ሀሳቡ ምንድን ነው? ጠቀሜታው ምን ያህል ነው?” ብለው ማየት ቀርቶ፣ ሊያናግሩሽ አይፈልጉም፡፡ እንዲህ አይነት ሰዎች ለዚያ ቦታ አይመጥኑም፡፡ ለቦታው የሚመጥን ሰው ለማስቀመጥ ዞሮ ዞሮ ግንዛቤ ላይ መስራት ያስፈልጋል።
እስኪ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና ሌሎች ተቋማት ስለስራሃቸው የጥበብ ውጤቶች ንገረኝ?
በተቋም ደረጃ እንግዲህ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተጠቃሽ ነው፡፡ ስራዎቼን በ“አፈርሳታ” ምክንያት አይተውት ነበር፡፡ አፈላልገው አገኙኝና አወሩኝ። ከሳይንስና ቴክኖሎጂ አንፃርም ሆነ በሌላ ጥሩ ሀሳብ ይዘዋል የሚሏቸውን ሥራዎቼን ወሰዱና ቦታ መርጠው ሰቀሉ። የሰው ልጆች አዕምሮ እንዴት ወደ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ተሸጋገረ የሚል ሀሳብ ያላቸው ሲምቦሊክ ስራዎችንም ሰርቼላቸዋለሁ። ለምሳሌ ጃካራንዳ የተባለውን ዛፍ ልብ ብለሽ ብትመለከቺ፣ ብዙ የተጠላለፉ እርስ በእርስ የተቆራኙና የተወሳሰቡ መስመሮችና ቅርንጫፎች አሉት፡፡ በተለይ ቅጠሉ ሲረግፍ ደግሞ አንዷን መስመር ብትይዢ ተጠላልፎ ውሉ ይጠፋል ይሄ ደግሞ የቴክኖሎጂውን የተጠላለፈውን ኬብል ይወክላል፡፡  በወቅቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ነበሩ መጀመሪያ ስራዬን ያዩትና ያናገሩኝ። ከዚያም የተቋቋመው ኮሚቴ አማካኝነት ሰርቼ፣ ሥራዬ በብዛት እዚያ ይገኛል፡፡ እንደ ተቋም የማመሰግነው ሳይንስና ቴክኖሎጂን እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ነው፡፡ ስዕል ያለውን ሀሳብ አምነውበት፣ ብዙ በጀት መደበው፣ በፕሮጀክት መልክ ነው የተሰራው።
ከአገራችን ሰዓሊያን ማንን ታደንቅሃል? ከአንጋፎቹም ከወጣት ሰዓሊያንም ሊሆን ይችላል…
እኔ ትልቅም ይሁን ትንሽ ስራውንና ሙያውን አክብሮ የሚሰራ ሰው አደንቃለሁ፡ እስከ ሰራ ድረስ አበርክቶው አይናቅም፡፡ አሁንም ድረስ ስቱዲዮአቸው እየሄድኩ፣ ሀሳብ የምካፈላቸው አስተማሪዎቼ የነበሩ አሉ፡፡ በህይወት ከሌሉት መካከል አርቲስት ታደሰ ግዛው በጣም የማከብረው ትልቅ ባለሙያ ነው። ማስተማሩንም ስራውንም ወድዶ የኖረ ትልቅ ሰው ነው፡፡ አሁን ካሉት ሰዓሊ ዘሪሁን የትምጌታ እና ረዳት ፕሮፌሰር ጌታቸው ዮሴፍ ለእኔ ልዩ ናቸው፡፡ እነዚህ ትልልቅ ሰዎች ከትንንሾቹ ጋር ሁሉ ሲመክሩ፣ ወጣቶችን ሲኮተኩቱ ነው የሚውሉት፡፡ እነሱ እውቀት ብቻ ሳይሆን ከኪሳቸው ሁሉ የማይሰስቱ አባቶች ናቸው፡፡ አርአያዎቻችንም ናቸው፡፡

 የወጣቱ ድምፃዊ ኢሳያስ ጂ (ኢሳ-ጂ) “አንኳኳ” አዲስ የሙዚቃ አልበም ለአድማጭ ቀረበ፡፡ በአገር፣ በፍቅርና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ 12 ዘፈኖችን የያዘው አልበሙ፤ ዜማና ግጥሙ በራሱ በድምፃዊው መሰራቱም ተገልጿል፡፡
ቅንብሩና ማስተሪንጉ ሙሉ በሙሉ በናትናኤል ተሾመ የተሰራ ሲሆን ራስ ጃኒ እና ናሽ የተሰኙ ድምፃዊያን በፊውቸሪንግ ተሳትፈውበታል ተብሏል። ጎጃም ሙዚቃ ቤት እያከፋፈለው እንደሚገኝም ታውቋል፡፡