Administrator

Administrator

በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ የተጀመረውን የቤቶች ልማት ፕሮግራም ምዝገባ አስመልክቶ አስተያየታቸውን የተጠየቁ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ፕሮግራሙ የሚሳካ አይመስለንም ይላሉ፡፡ በርካታ የቤት ተመዝጋቢዎችም መንግስት ቃል የገባው የቤቶች ግንባታ ይሣካ ይሆን የሚል ጥርጣሬ አላቸው፡፡ ይሄንን መነሻ በማድረግ የቤት ፕሮግራሙን በተመለከተ የተቃዋሚ አመራሮቹ አይሳካም የሚሉበትን ምክንያት በዝርዝር እንዲያስረዱን ጠይቀናቸው የሰጡንን ምላሽ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡


“እንደ ብሄራዊ ሎተሪ በእጣ ቤት ማደል የኢኮኖሚ ስራ ነው ብዬ አላምንም”
አቶ ሙሼ ሠሙ
የባንክ ባለሙያና የኢዴፓ ሊቀመንበር
መጀመሪያ ማንም ዜጋ ቤት ማግኘት ያለበት በጥረቱ ነው ብዬ ነው የማስበው እንጂ ልክ እንደብሄራዊ ሎተሪ በእጣ ቤት ማደል የኢኮኖሚ ስራ ነው ብዬ አላምንም፡፡ መጨረሻ ላይ ማጣፊያው ያጥራል፡፡ መጀመሪያውኑ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ሲታደሉ መንግስት እያንዳንዱ ቤት ፈላጊ የተወሠነ ገንዘብ አጠራቅሞ ባጠራቀመው ገንዘብ ላይ ድጋፍ ተደርጐለት በረጅም ጊዜ ብድር ቤት የሚያገኝበት እድል ቢያመቻች ኖሮ ዛሬ የሚሠሩት ቤቶች አጣብቂኝ ውስጥ አይገቡም ነበር፡፡ መንግስት ከዚህ አኳያ ሊገጥመው የሚችለው ችግር የገንዘብ አቅም ጉዳይ ነው፡፡ ገንዘቡ ከአሁን በኋላ ተጠራቅሞ ነው እንግዲህ ሠዎች የቤት ባለቤት የሚሆኑት። በዚህ መሀል መገንባት አለበት፡፡ ቤቱን ለመገንባት ደግሞ ወደ ብድር መግባት አለበት፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትን አቅም እናውቀዋለን - 1.2 ሚሊዮን ቤት ለመገንባት የሚያስችል አቅም ሊፈጥር የሚችል ገንዘብ የተለየ ፈንድ ካላገኘ በቀር ከየትም ሊያመጣ አይችልም፡፡ ገንዘብ ማተም ውስጥ ካልገባ በቀር ወይም ደግሞ በጣም ከፍተኛ ገንዘብ ከቻይናና ከህንድ የሚያገኝበትን ሁኔታ ካላመቻቸ በቀር እነዚህን ቤቶች በሰባት አመት ውስጥ ሊገነባ የሚያስችለውን አቅም ሊያገኝ አይችልም፡፡ ሁለተኛው ይሄንን ቤት ለመገንባት የሠው ሃይል ጥያቄ አለ፡፡ 1.2 ሚሊዮን ቤቶች ለመገንባት በቤት ግንባታ እውቀት ያላቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሠዎች ያስፈልጋሉ፡፡ እነዚህ ሠዎች ከየት ነው የሚመጡት? ሶስተኛው ደግሞ የተፈጥሮ ሃብት ነው - መሬት፣ ድንጋይ፣ ብረት፣ ሲሚንቶ፣ ጠጠር የመሣሠሉት በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ከየት ነው ሊመጡ የሚችሉት? እነዚህ መሠረታዊ ጉዳዮች በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ይሟላሉ ብዬ አላምንም፡፡ የተባለው ፕሮግራምም ይሣካል ብዬ አልገምትም፡፡
“መንግስት የዜጐች ቤት ሠሪ ሊሆን አይችልም”
የተከበሩ አቶ ግርማ ሠይፉ
የፓርላማ አባል- የአንድነት ፓርቲ አመራር
እኔ በግሌ ትርጉም የሚሠጥ ነው ብዬ አስቤውም አላውቅም፡፡ የህዝቡን ስሜት ለመግዛት ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሲያስቡ የመጣላቸው እና የታያቸው አንዱ መንገድ ነው፡፡ አሁን እየተደረገ ያለው ነገር በዋናነት የሃገር ውስጥ ቁጠባ አነስተኛ ነው ከሚለው በመነሣት የመጣ ነው፡፡ እርግጥ ነው የሃገር ውስጥ ቁጠባ አነስተኛ ነው ነገር ግን ህዝቡ ዝም ብሎ አይቆጥብም። ስለዚህ መንግስት ህዝቡ እንዲቆጥብ አንድ ነገር ራቅ አድርጐ ሠቅሎ ማሣየት ነበረበት፡፡ የቤቶች ፕሮግራሙ ዋና አላማው በሃገር ውስጥ ያለውን የቁጠባ ባህል ከፍ ማድረግ ነው፡፡
ስለዚህ ቤት በማግኘትና ባለማግኘት ቁም ነገር ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ሣይሆን የሃገር ውስጥ ቁጠባን ለማሣደግ ተብሎ ነው፡፡ ከዚያ ውጪ ግን በመርህ ደረጃ መንግስት የዜጐች ቤት ሠሪ ሊሆን አይችልም፡፡ ለምሣሌ ባለፈው ክቡር ጠ/ሚኒስትሩ መቶ ሺህ ቤቶች ሠርተናል ብለው በኩራት ተናግረዋል፡፡ እነሱ ጉልበትና ስልጣን ስላላቸው የሠው ስራ ቀምተው በመስራታቸው ሊኩራሩ አይገባም፡፡ በ1998 ለተመዘገቡ 450 ሺህ ቤት ፈላጊዎች በስምንት አመት ጊዜ ውስጥ ቤቶች ሰርተን እናጠናቅቃለን ብለው ይኸው ስምንት አመት አልፎ እንኳ 100ሺህ ቤቶች መስራት አልቻሉም፡፡ ጅምሮቹን ጭምር ነው 100 ሺህ ቤቶች ሠርተናል ያሉት። ለእነዚህ ቤቶች አንድ ጊዜ መሠረት በመጣል፣ አንድ ጊዜ በማስመረቅ ሌላ ጊዜ ቁልፍ በመስጠት አምስት ጊዜ ይወራና 500ሺህ ያስመስሉታል። አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተሠሩት ቤቶች 100ሺህ ናቸው - እስክስታው ዘፈኑ ግን ሚሊዮን ነው። በተቃራኒው ግን በማህበር በመሣሠሉት ከዚህ ከላይ ቤቶች ተሠርተዋል፡፡ ከዚህ አንፃር መታየት ያለበት ፕሮግራሙ አንደኛ አላማው ለዜጐች ቤት መስጠት ሣይሆን የቁጠባ ባህሉን ማበረታታት ነው፡፡ ግን በየአመቱ ትንሽ ትንሽ ነገር እየሠጡ በማሣየት ሠዎች በተስፋ እንዲቆጥቡ ይደረጋል፡፡ በዚህ ማሣያው ቁጠባውን ያቋረጠ ይሠረዛል ይላል፡፡ ቤቱን ይሠሩታል አይሠሩትም ለሚለው በእርግጠኝነት አይሠሩትም፡፡ የሆነ አስማት እንኳ ተፈጥሮ ቢሠሩት ትክክል ነው ብዬ አላምንም። ሌሎች በሪል ስቴት ውስጥ ተሣትፈው ይሄን ሊያደርጉ የሚችሉ ሠዎችን ስራ እየቀሙ ነው እንሰራለን የሚሉት፡፡ መንግስት ዜጐች በተመጣጣኝ ዋጋ ቤት ማግኘት አለባቸው የሚል አቋም ሊይዝ ይችላል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ቤትን ውድ የሚያደርገው አንደኛው መሬት ነው - ራሱ ሲሠራ በነፃ መሬት ይወስዳል፡፡ የግንባታ ግብአትም ከቀረጥ ነፃ እንዲገባ ያደርጋል፡፡ ስለዚህ በርካሽ ዋጋ የመስራት አቅምን ለራሱ ያመቻቻል፡፡ ይህን አቅም ወደ ግል ሴክተሩ አዘዋውሮ እነዚህን ማበረታቻዎች ሠጥቶ ሜዳውን ለነሡ ቢለቅ ነበር የሚሻለው፡፡ አሁን ግን ፕሮግራሙን ወደ ገጠር አካባቢዎችም ለማስፋት እቅድ ያለው ይመስላል። በየቦታው የተከፈቱ የንግድ ባንክ ቅርንጫፎችም ለዚህ የተመቻቹ ናቸው፡፡ ሠው አሁን ቆጥቦ በኋላ ባይደርሠው ገንዘቡን መውሠድ እንደሚችልም አማራጭ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን ቆጣቢው ኋላ ላይ የሚያገኘው ገንዘብ በዋጋ ንረት የተጐዳና የመግዛት አቅም የሌለው ነው የሚሆነው፡፡

“መንግስት የሚመረጠው ነጋዴ እንዲሆን አይደለም”
አቶ ቡልቻ ደመቅሣ
የፋይናንስ ባለሙያና የመድረክ አመራር አባል
የቤቶች ፕሮግራሙ የተዘረጋው የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት ነው፡፡ የእነዚህ ፕሮግራም ተሣታፊዎች የኢህአዴግ አባል እንዲሆኑ ነው የሚደረጉት፡፡ ለምሣሌ አንድ ሠው ቤት ልስራ ብሎ 40/60 የሚባለው ውስጥ ቢገባ መጀመሪያ ማረጋገጥ የሚፈልጉት የኢህአዴግ አባል መሆኑን ነው፣ ስለዚህ ይሄ ጠቃሚ ሳይሆን ጐጂ ነው። መንግስት የሚመረጠው ነጋዴ እንዲሆን አይደለም። ፍርድ እንዲሠጥ፣ የፖሊስ ስራ እንዲሠራ፣ ጉምሩክ እቃ ሲገባ ቀረጥ እንዲያስከፍል፣ መሬት በደንብ እንዲለማ፣ የኢኮኖሚ ልማት እንዲመጣ ነው እንጂ ንግድ ውስጥ ገብቶ እንደ ተራ ነጋዴ ለመቸብቸብ አይደለም፡፡ ዞሮ ዞሮ ደግሞ ይሄ ሃገራችንን ይጐዳል፡፡ የአለም ንግድ ድርጅት አባል መሆን ያልቻልነው እኮ መንግስት ከንግድ ውስጥ መውጣት ባለመቻሉ ነው፡፡ በዚህ ድርጅት ውስጥ አለመግባት ደግሞ ለዘለቄታው ጉዳት አለው፡፡ ለኢህአዴግ ንግድ ፖለቲካ ነው። በንግዱ የፖለቲካ ትርፍ ማግኘት ይችላሉ፡፡ አሁን ለህዝቡ ቃል እንደገባው ተሣክቶለት ቤቱን ቢሠራም ትክክል አይደለም፡፡ ገንዘብ ከዚህ ሁሉ ሠው መሠብሠቡ በራሱ ቀላል አይደለም። የመንግስት ዋነኛ ስራው መሆን የለበትም፡፡ የመንግስት ሠራተኛ የሚቀጠረው የመንግስት ስራ ተብለው የተለዩትን ለመስራት ብቻ ነው፡፡ ግብር መሠብሠብ እንጂ ከህዝቡ ጋር እየተጋፉ ገንዘብ ለማስገባት አይደለም፡፡ አሁንም አጥብቄ የምናገረው ይህ የመንግስት ተግባር አለመሆኑን ነው፡፡ የመንግስት ሥራ ዳር ድንበር መጠበቅ፣ ፍትህ ማስፈን፣ መንገድ መገንባት እንጂ ብር እያበደሩ ቤት መስራት አይደለም፡፡

“የቤት ፕሮግራሙ ለቀጣዩ ምርጫ የታለመ ይመስላል”
ዶ/ር መረራ ጉዲና
የፖለቲካ ሣይንስ ምሁር እና የመድረክ አመራር አባል
መንግስት ብዙ ድስቶችን ጥዶ ነው የሚንቀሣቀሰው፡፡ አንደኛው ድስት ይሄ መሆኑ ነው፡፡ ዋናው ግን ይሄ የቤት ፕሮግራም ለ2007 ምርጫ የታለመ ይመስላል፡፡ የዚያን ጊዜ እኛን ካልመረጣችሁ ቤት አታገኙም ሊሉ ይመስላል ዳር ዳር የሚሉት፡፡ አሁን እንግዲህ ወደ 2 ሚሊዮን ቤት ነው እንሰራለን ያሉት፡፡ ይሄ ደግሞ በኛ አቅም አጠያያቂ ነው፡፡ ደግሞ ሁሉን አይነት ሠው ነው የሚመዘግቡት፡፡ ውጤቱን እንግዲህ ውሎ አድሮ ማየቱ ይሻላል፡፡ የኔ ጥርጣሬ ግን የ2007 ምርጫን ታሣቢ አድርገው ነው የሚል ነው፡፡ ጨዋታው ቀላል አይደለም፡፡
ቤት መስራት ብቻ ሣይሆን ከዚያ ጋር ብዙ የተያያዙ ነገሮች አሉ፡፡ መሠረተ ልማቱ መጨመር አለበት- ውሃ፣ መብራት፣ መንገድ፣ ስልክ አለ። እኒህን ሁሉ ማሳካት ከቻሉ ጥሩ ነው፣ ግን አይመስለኝም፡፡

ከክርስቶስ ልደት በፊት በሶስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረ ኩንግ ሲ የተባለ አንድ ንጉስ በቻይና ይኖር ነበር፡፡ ንጉስ አሳ በጣም ይወድ የነበረ መሪ ነበር ይባላል፡፡ የአገሩ ህዝብ በሞላ አሳ ይገዛና እጅ መንሻ ያቀርብለታል፡፡ ንጉሱ ኩንግ ሲዩ ግን ስጦታውን አልቀበልም፤ይላል፡፡ ይህንን ያየው ታናሽ ወንድሙ ወደ ንጉሱ ይመጣና “ያለጥርጥር አሳ በጣም እንደምትወድ አውቃለሁ፡፡

ስለምን ነው የአሳ ስጦታቸውን አልቀበልም ያልከው?” ሲል ጠየቀው፡፡ ንጉሱም፤ “ወንድሜ ሆይ ! የአሳ ስጦታ የማልቀበልበት ምክንያት፤ እያንዳንዱ ስጦታ በውለታ እንድትታሰር ያደርግሃልና ነው፡፡ በውለታ ከታሰርኩኝ የሃገራችንን ህግ እስከመጠምዘዝ ድረስ እሄዳለሁ፡፡” “ለምን ትጠመዝዛለህ?” “ውለታ የዋልክለት ህዝብ በፋንታው ይሄን አድርግ ብሎ ስለሚጠቨቅህ ነዋ!” “ለምን እምቢ አትልም ታዲያ?” “አሳ የምወድደወው ጭንቅላቴን ረቂቅ ስለሚያደርግልኝ ነው፡፡

ይሄንን እንዳረግ ያደረገኝም አሳ ነው!” “አልገባኝም” “አሳ አትበላማ! አሳ ሳትበላ እንዴት ይግባህ?” “ህጉ ቢጣመም ምን ቸገረህ? ስልጣኑ ያንተ?” “ህጉን ካጣመምኩ ራሴ ተጣምሜ ከስልጣኔ እወርዳለሁ” “ከስልጣንህ ብትወርድ ምን ቸገረህ?” “ከስልጣኔ ከወረድኩ በኋላ ራሴን አሳ ለመመገብ አልችል ይሆናል! በተቃራኒው ካየኸው ግን፤ከህዝብ የአሳ ስጦታ ባልቀበል፣ ከመንበሬ ባልወርድ፣ መቼም ቢሆን አሳ ገዝቼ መብላት አያቅተኝም!!”

                                                    * * *

ስጦታና እጅ መንሻ ስርዓትን እስከመናድ እንደሚደርስ በሀገራችን አይተናል፡፡ ከፈረንሳይ ድረስ የ70,000(ሰባ ሺ) ብር ሽቶ (ብራችን በዶላር 2.05 ብር ይመነዘር በነበረ ጊዜ) ለልደታቸው ስጦታ ይመጣላቸው የነበሩ ልዕልቶች እንደነበሩ ታዝበናል፡፡ የሀገር መሪዎች በስዊስ ባንክ አያሌ ሚሊዎን ብርና ወርቅ አስቀምጠው የነበረበት ወቅት እንደነበር አንረሳም፡፡ ይህን ዓይነቱ ነገር የዛሬ ስሙ ሙስና ነው፡፡ መታያ፣እጅ -መንሻ፣ስጦታ ፣የደስ ደስ ፣ቤት ማሞቂያ፣ህንፃ ማድመቂያ፣እጅ ማበሻ… ሁሉም የሙስና ተለዋጭ ስሞች ናቸው፡፡ “ሙሳዊ ጫና የክፉ ስራዎች ሁሉ የዓመት ከዓመት ፀደይ ነው፡፡

የስርዓቱ ብልሽት መጠንሰሻ ነው፡፡ የአገር ዕዳ ክምር - ክንብንብ ነው፡፡ ክንዳችንን ያልማል፡፡ ከሸንጎ ውስጥ የጥበብን ብልት ቆርጦ ስልጣንን ለግል ጥቅም ለማዋልና ስምና ዝናን ማትረፊያ ለማድረግ እንድናውለው ያመቻችልናል!” ይለናል በርክ የተባለው ፀሐፊ፡፡ ይህሁነት በዲሞክራሲ ማነቆነት፣ በልማት እንቅፋትነት፣ በሃይማኖት ግጭት መንስዔነት፣ በጦርነት ሰበብነት ትልቅ ተፅዕኖ ቢፈጠር ዞሮ ዞሮ ጦሱ ለሀገር ነው የሚተርፈው፡፡ ጀርመኖች ደግሞ ስለታላላቅ ጦርነቶች የሚከተለውን ይላሉ፡- ታላቅ ጦርነት ሃገሪቱን የሶሰት ዓይነት ሰራዊት ባለቤት ያደርጋታል፡- የጦር- ጉዳተኞች ሰራዊት፣ የሐዘንተኞች ሰራዊት እና የሌቦች ሰራዊት! ሃይማኖቶች የቅዱሳት፣የቀና መንፈስ፣የመልካም ስራ መመሪያ የሚሰጡ፣የበጎ ምግባር አቅጣጫ መሪ እንጂ የግጭት መንስኤና ሰበብ መሆን የለባቸውም፡፡ ለዚህ ነው:- “ሃይማኖት ታረደ ደሙን ኩቲ ላሰው እንግዲህ ሆድ ለሆድ አልተገናኘም ሰው” እያለ የሀገራችን ሰው የሚገጥመው፡፡

ሁሌ የምንሰራው ስራና የእንቅስቃሴያችን ሂደት “በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለፀ”፣ “የስራ ግምገማው እንደሚያሳየው የዕድገት አቅጣጫ ጠቋሚ ነው”፤ “በይሄን ያህል ፐርሰንት ያደግን መሆኑ ተገለፀ” ወዘተ እየተባባልን ችግሮቻችንን እንዳናይ ዐይናችንን መጨፈን ትልቅ አባዜ ነው፡፡ “ሞኝ፤የሚያደንቀው ሞኝ አያጣም”፤ እንዲሉ እርስ በርስ በመደናነቅና “አበጀህ”፣ “አበጀህ!” በመባባል ብዙ የተራመድን በመሰለን ጊዜ መስጋትና መጠንቀቅ ብልህነት ነው፡፡ ፍትህ፤ ዕውነታችን በየትኛው አቅጣጫ እንዲበራ እንደምናደርግ ራሳችንን የምንፈትሽበት ድንቅ መሳሪያ ነው፡፡ “ስለ አገርህ፣ስለ አምላክህ፣ስለ ዕውነትህ፤ ይሁን እንጂ ቅን ዓላማህ፣ ፍትሐዊነት ቅን ፀጋ ነው፣ ፈፅሞ ፍርሃት አይግባህ” (ይላል ሼክስፒር) ዲሞክራሲያችንን እንፈትሽ፡፡ “ዲሞክራሲን ማፍቀር እኩልነትን ማፍቀር ነው፡፡”

ይለናል ሞንቴስኩ፡፡ ይህ የእኩልነት ፍቅር አለን ወይ? “ዲሞክራሲ ምርጥና ለመተግበር እጅግ አዳጋች የፖለቲካ አደረጃጀት ነው” ይለናል ራልፍ ባርተን፡፡ ይህንንስ ተገንዝበናል?(dynamic democracy) ተንቀሳቃሽ እና አንቀሳቃሽ ዲሞክራሲ ካልሆነ ዲሞክራሲ የለም ብንል ይሻላል፡፡ ህዝባችን መሳተፍ ሲያቆም፣ፀሀይ ውስጥ ቦታ ሲያጣ -ያኔ ሁላችንም በመበስበስ (በንትበት) ጨለማ (darkness of decadence)ውስጥ በነን እናልቃለን፡፡ ሁላችንም ዲዳ ፣ሞራለ - ቢስ እና የቀለጡ ነብሶች እንሆናለን” (ሳውል ደ-አሊንስኪ) ዲሞክራሲ ስንል እንደፕሉታርክ “ሂድ፡፡ በራስህ ቤት የራስህ ዓይነት ዲሞክራሲ ሞክር” ማለታችን ቢሆንም ይመረጣል፡፡ የሙስናን፣ የጎረቤትን የጦርነትን፣ የሃይማኖትን ነገር፣ የዲሞክራሲንና የዕድገትን ነገር፣ በወጉ ለማየት ችግራችንና መፈርትሄዎቻችንን በተያያዘ ጥምረት ማገናዘብ አለብን፡፡

የሃገራችንን ችግር ስንቃኝ አንዱን ካንዱ አስተሳስረን መሆን አለበት፡፡ አለበለዚያ የአንድ ሰሞን ግርግር ዘመቻ ብቻ ይሆናል፡፡ ተከታታይ ጥረትና ቀጣይነት አይኖረውም፡፡ አንዱን ዘመቻ ሌላው እያስረሳውና እየሻረው ስለሚሄድ ዕድገታችን ደብዛዛ ይሆናል፡፡ የተሳሰረ ጥረት የማይረሳሳ ትግል ነው ሊኖረን የሚገባው፡፡ በተበታተነ ሁኔታ ውስጥ እንዳንበታተን፤ አረሙን፣ እንቅፋቱን፣ ዳተኝነቱንና ግብዝነቱን ትተን፣ ለመጓዝ፤ ”የመጣ ሳይመጣ የውሃ ቦይ ጥረግ” የሚለውን ተረት ማሰብ አለብን!!


አድማስ አድቨርታይዚንግ እ.ኤ.አ በ1990 የተቋቋመ የግል ድርጅት ነው፡፡ አድማስ አድቨርታይዚንግ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሁለት ዋና ክፍሎች አሉት፡፡

የህትመቱ ክንፍ አንዱ ሲሆን ሳምንታዊው ጋዜጣ አዲስ አድማስ ያሳትማል የማስታወቂያ ክንፉ ደግሞ የፊልም መስሪያስቱዲዮ እና ግራፊክ ዲዛይን ያለው ነው፡፡ ድርጅታችን በኤሌክትሮኒክስ ሆነ በህትመት ሚዲያ ላይ የሚሰራ የማስታወቂያ ኤጀንሲ ነው፡፡ የቴሌቪዢንና ሬዲዮ ማስታወቂያዎችን በመስራት በአየር ላይ ከማዋላችንም በተጨማሪ የሚዲያ ምክርና ዕቅድ አገልግሎቶች እንሰጣለን፡፡ በሚሰጠን ቅድመ መረጃ አማካይነት ማናቸውንም የቲቪ፣ሬዲዮ እና ፕሬስ ማስታወቂያዎች እንዲሁም ግራፊክ አርትስ እንሰራለን፡፡

አገልግሎታችን በሚዲያ ምርጫ ላይ ማማከር፣ማቀድ፣መከታተል፣የማስታወቂያዎቹ ያስገኙትን የመጨረሻ ውጤት መገምገምን ያካትታል፡፡ በርፉ ያልን በቂ ልምድና በቡድን የመስራት ባህል ሚዲያውን እንዴት ደንበኞቻችን በሚያረካና ውጤታማ በሚያደርግ መልኩ መጠቀም እንዳለብን እንድናውቅ አስችሎናል፡፡ አድማስ አድቨርታይዚንግ የአዲስ አበባ ንግድ ም/ቤት አባል ሲሆን በተለያዩ ባህላዊና ማሕበራዊ እንቅስቃሴዎች ንቁ ተሳታፊ ነው፡፡

Audio visual studio

የማስታወቂያ አገልግሎት እና ኦዲዮ/ቪዥዋል ስቱዲዮበላቀ የፕሮዳክሽን ደረጃው ዪታወቀው የማስታወቂያ ክፍላችን ለንግዱ ዘርፍና ለማህበራዊ ግብይት ዋነኛ አጋርነቱን አረጋግጧል፡፡ ፕሮፌሽናል የኦዲዮ/ቪዲዮ ስቲዲዮችን፡፡ በፕሮፌሽናል ዲቪ ካሜራዎች ከአማራጭ ሌልሶች ጋር የመብራትና የድምጽ መሳሪያዎች የካሜራ ክሬን በተሟላ የኤዲቲንግ ስቱዲዮ እና በሌሎች ተፈላጊ መሳሪያዎች የተደራጀ ነው፡፡ ቴክኖሎጂ ያፈራቸውን የተደራጀ ዘመናዊ መሳሪያዎች የያዘው ስቱዲዮአችን በአገራችን ካ ጥቂት ምርጥ የፊልም ስቱዲዮዎች አንዱ ያደርገዋል፡፡

አድማስ አድቨርታይዚንግ ብቁና ተፎካካሪ በሆኑ የአስተዳደር የፋይናንስ እና በጥበብ ባለሙያዎች የተሞላ ነው በድርጅቱ የሚሰሩት ተርጓሚዎች ገጣሚዎች የአርት ዳይሬክተሮች እና ጋዜጠኞች በሙያቸው የተሞከሩ የተፈተኑና በበርካታ ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤት ያስመዘገቡ ናቸው፡፡ በተጨማሪው ድርጅቱ በህዝቡ ዘንድ በተቀዳጀው አክብሮት እና አስተማማኝ የሥራ ሁኔታ የተነሳ በአገሪቱ የሚገኙ ምርጥ የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ባለሙያዎች ለመቅጠርና አብረውን እንዲሰሩ ለማድረግ አስችሎታል፡፡ ለዚህም በየጊዜው ያስመዘግባቸው የስኬት ክብረወሰኖች ከቃላት በላይ ይናገራሉ፡፡

የአድማስ አድቨርታይዚንግ ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ አሰፋ በኢትዮጵያ የማስታወቂያ ኢንዱስትሪ ጉልህ ለውጥ ማምጣታቸውም ይታወቃል፡፡

በኢትዮጵያ በተፈጠረው የዲሞክራሲ ስርዓት ሚዛናዊ ሂሳዊ ጋዜጣ በመመስረት ለህብረተሰቡ የንባብና የዕውቀት ዕድል የፈጠረ ሰው ነበር፣ያሉት በቀብር ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምኦን ሲሆኑ የሪፖርተር ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ አቶ አማረ አረጋዊ በበኩላቸው ‹‹ በኢትዮጵያ ፕሬስ የተግባር ሚና ከተጫወቱ ሰዎች ግንባር ቀደም ነው ›› ብለዋል፡፡የአቶ ድንገተኛ ሞት አስመልክተው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አስተያየታቸውን ሲሰጡዕ ‹‹ እንደ ህብረተሰብ ትልቅ ሰው ነው ያጣነው ›› ብለዋል፡፡

በብዙዎች ዘንድ አድንቶትን ያተረፈውንና በስምንት ድምፃውያን የተዜመውን ‹‹ ማውቀር ነው መሰልጠን ›› የተሰኘ የዘፈን ክሊፕ ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት አድማስ አድቨርታይዚነግ ማሰራቱ የማታወቅ ሲሆን በቅርቡ በኮራ አሸናፊ የሆነው የድምፃዊት ፀደንያ ገ/ማርቆስ የዘፈን ክሊፕ አቶ አሰፋ እራሳአው በቅርቡ ባቋቋሙት የፊልም ስቱዲዮ መሰራቱ ታውቋል፡፡

በአድማስ አድቨርታይዚንግ ስር የሚታተመውና በአገራችን በስርጭት ብዛት ከሁለት ዓመት ወዲህ በቀዳሚነት ሥፍራ የሚገኘው የአዲስ አድማስ ጋዜጣ መስራች ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ አሰፋ ከምዕራብ አገራት የፊልም ደረጃ ጋር የሚስተካከል ፊልም ለመስራት ባላቸው ራዕይ ለየት ያለ ስቲዲዮ በመገንባት ላይ ነበሩ፡፡


Saturday, 22 June 2013 12:18

የፌዴሬሽኑ ቅሌት

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫው ማጣሪያ የሁለተኛ ዙር ግጥሚያ ጋቦሮኒ ላይ ከቦትስዋና አቻው ጋር ባደረገው ጨዋታ ሁለት ቢጫ ያየውን ምንያህል ተሾመ በማሰለፉ በፊፋ የቀረበው ክስ ለመላው የእግር ኳስ ቤተሰብ ያልተጠበቀ መርዶ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ለቀረበበት ክስ በቂ መከላከያ ማቅረብ ካልቻለ ከቦትስዋና ጋር ተጫውቶ ያስመዘገበው የ2-1 ውጤት ተሰርዞ ለቦትስዋና ቡድን በፎርፌ 3 ነጥብ እንደሚመዘገብላት ተገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ 130ሺ ብር ቅጣት መክፈል ይጠበቅባታል፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ወደ ዓለም ዋንጫ ለማለፍ መስከረም 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ የግድ ማሸነፍ ይኖርበታል፡፡ ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ዝርክርክ አሰራር ነው፡፡

ከዋልያዎቹ የ2ለ1 ድል በፊት የደረሰው መርዶ መርዶው በይፋ የተሰማበት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ጋዜጣዊ መግለጫ ማክሰኞ እለት በጊዮን ሆቴል ሳባ አዳራሽ ሲሰጥ በደስታ መግለጫና በምስጋና ነበር የተጀመረው፡፡ ከዚያም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በደቡብ አፍሪካ ላይ 2ለ1 በሆነ ውጤት ካስመዘገበው ድል ጋር በተያያዘ በመላው ኢትዮጵያ በነበረው የደስታ አገላለጽ ለሞቱ ሁለት ወጣቶችም የ1 ደቂቃ የህሊና ፀሎት ተደርጓል፡፡ ሁለቱ የባህርዳር ወጣቶች የ16 ዓመት ተማሪ እና የ13 ዓመት ሊስትሮ ናቸው፡፡ ፌዴሬሽኑ በደስታ አገላለፁ የሞቱት ሁለት ወጣቶች መሆናቸውንም ቢገልጽም በመግለጫው ላይ የተገኙ አንዳንድ ጋዜጠኞች የሟቾች ቁጥር 4 ይሆናል የሞት አደጋ ያጋጠመው በባህርዳር ብቻ አልነበረም በሱልልታና በአዳማም ጭምር እንጅ ብለው እርማት አድርገዋል፡፡

ጋዜጣዊ መግለጫውን የመሩት የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ ገ/ወልድ፣ በደቡብ አፍሪካ ላይ በተመዘገበው የ2ለ1 ድል ዘግተናል ያልነውን ምዕራፍ እንደገና ለመክፈት ተገደናል በሚል የመግቢያ ንግግራቸው መግለጫውን የጀመሩት ፤ አስደንጋጩ መርዶ ፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት የደረሰው ረቡዕ ዕለት መሆኑን በመግለፅ ነበር፡፡ ኢትዮጵያና ደቡብ አፍሪካ በአዲስ አበባ ስታድዬም ከመገናኘታቸው ሶስት ቀናት ቀደም ብሎ ማለት ነው፡፡ ከፊፋ የመጣው የክስ “ኮምኒኬ” ረቡዕ 5 ሰዓት ላይ ለፌዴሬሽኑ በፋክስ ሲደርስ በጽ/ቤቱ ስለ እሁድ ጨዋታ አጠቃላይ ዝግጅት ለመነጋገር ተሰብስበው የነበሩት የፌዴሬሽኑ ኃላፊዎች፣ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ ገ/ወልድ ፤ተቀዳሚ ም/ፕሬዚዳንቱ አቶ ብርሃኑ ከበደ ፤ ዋና ፀሐፊው አሸናፊ እጅጉ ናቸው፡፡ ለፌዴሬሽኑ ኃላፊዎች አስደንጋጭ፣ የሚረብሽና ከፍተኛ የሃዘን ስሜት ውስጥ የከተተ መርዶ ሆኖባቸው እንደነበርም ገልፀዋል፡፡ ዋና ተቀዳሚ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ተካ አስፋው፣ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ስብሰባ ካይሮ ሄደው ነበርና ሐሙስ ሲመለሱ የፌዴሬሽኑ ኃላፊዎች አስቸኳይ ስብሰባ ተቀመጡ፡፡ እንዲህ በሚልም ተነጋገሩ፡፡ “እሁድ ጨዋታ አለን፡፡ ህዝቡ ጉጉት ላይ ነው፡፡ ተጨዋቾቹ ስሜታቸው የተነሳሳበት ወቅት ነው፡፡ ያለውን ድባብ ማፍረስ ስለሌለብን ጉዳዩን በከፍተኛ ምስጢር መያዝ አለብን” በማለት ተማማሉ፡፡ መማማሉ በየትኛውም መንገድ መረጃው እንዳይወጣ፣ የብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች እንዳይረበሹ፣ ህዝቡ ስሜቱ እንዳይጎዳ በሚል ነበር፡፡

እንደ አቶ ሳህሉ ገለፃ፣ ዋልያዎቹ የእግዚአብሔር ፈቃድ ሆኖ ከደቡብ አፍሪካ ጋር የተደረገውን ጨዋታ በድል በመወጣታቸው ለፌደሬሽኑ ሃላፊዎች ከእነጭራሹ ደብዝዞና ከስሞ የነበረው ተስፋቸውን አለመለመላቸው፡፡ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫው የመጨረሻ ማጣሪያ ምዕራፍ መግባቱን ባረጋገጠ ደስታ ተውጦ ነበር፡፡ ስለመርዶው ምንም የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ የፌዴሬሽኑ ሥ/አስፈፃሚ አባላት ሰኞ ዕለት 10 ሰዓት ላይ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀመጡ፡፡ ስብሰባው የተፈጠረውን ሁኔታ በመገምገም እና ችግሩን ለይቶ አጠቃላይ የጋራ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነበር፡፡ በዚህ የስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ ከ11 አባላቱ ባሻገር ዋና አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻውና የጽ/ቤት ኃላፊዎች በሙሉ ተገኝተውበታል፡፡ እንደ ፌደሬሽኑ አመራሮች ማብራርያ፣ በስብሰባው የፊፋን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ህገ ደንብ በማጣቀስ በቀረበው ክስ ዙርያ መከራከርያ ነጥቦች ተነስተው ተመክሯል፡፡

ከቀኑ 10 ሰዓት ተጀምሮ እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት ተኩል በዘለቀው ስብሰባ፣ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚዎች እንደየሃላፊነታቸው እና የስራ ድርሻቸው በቡድንና በተናጠል ተገማግመዋል፡፡ ስብሰባው የመደናገጥ እና የመላቀስ ድባብ እንደነበረውና ስፖርታዊ ጨዋነትን በተላበሰ መንገድ እንደተከናወነ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተናገሩት የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ፣ በመገማገም መድረኩ ስህተት መፈፀሙ እንደተረጋገጠ ፤ በቀረበው ክስ ለፊፋ ይግባኝ ለመጠየቅ እና ለመከራከር እንደማይቻል ታወቀ ብለዋል፡፡ ለደረሰው ጥፋት ተጠያቂ መኖር እንዳለበት በመተማመን በየደረጃው ተጠያቂ አካላትን በመለየት በጋራ መግባባት ውሳኔ ላይ መደረሱን ሲያብራሩም ምንም አይነት ሆን ተብሎ የተደረገ (Deliberate) የተሸረበ ሴራ (sabotage) ፣ የታቀደ ተንኮል (Intentional) እንዳልሆነ ተረድተናል ብለዋል፡፡ ዋልያዎቹን ነጥብ ያስጣለው ዝርክርክ አሰራር፤ ተጠያቂዎቹ እና ቃላቸው በፌደሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ግምገማ ላይ ለተፈፀመው ጥፋት የመጀመርያው ተጠያቂ የሆኑት ተቀዳሚ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ከበደ ናቸው፡፡ አቶ ብርሃኑ ከበደ የቡድን መሪ ሆነው የተሾሙት የዓለም ዋንጫው የምድብ ማጣርያ በደቡብ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ ጨዋታ ሩስተንበርግ ላይ ሲጀመር እና ከዚያም በኋላ በሁለተኛ ዙር የምድብ ማጣርያ አዲስ አበባ ላይ ኢትዮጵያ እና ሴንትራል አፍሪካ ባደረጉት ግጥሚያ የቡድን መሪ ከነበሩት አቶ አፈወርቅ አየለ ሃላፊነቱን በመረከብ ነበር፡፡ ከሁሉም በላይ በእኔ ኃላፊነት ይህ ጥፋት በመድረሱ የተሰማኝን ሃዘን መግለጽ እፈልጋለሁ በማለት ቃላቸውን መስጠት የጀመሩት አቶ ብርሃኑ ከበደ፤ በዋልያዎቹ የቡድን መሪነት ስራቸውን የጀመሩት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በጋብሮኒ ከቦትስዋና አቻው ጋር በተጋጠመበት ወቅት ነበር፡፡

የፌደሬሽኑ ፅህፈት ቤት የዚሁን ጨዋታ ኮሚኒኬ አስፈርሞ እንደሰጣቸው ቢገልፅም፤ አቶ ብርሃኑ ግን በሰጡት ቃል ፈረሙበት የተባለው ደብዳቤ ኮፒ እጃቸው ላይ እንደማይገኝ፤ እንደተሰጣቸው እንደማያስታውሱ፣ ተሰጥቷቸውም ከሆነ ደብዳቤው እንዴት ከእጃቸው እንዳመለጠ እንደማይገባቸው ነው የገለፁት፡፡ በጋብሮኒ ለተካሄደው ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልዑካን የቪዛ ጉዳዮች እና ሌሎች ጉዳዮች የማስፈፀም ድርብ ሃላፊነት እንደነበረባቸው ያስታወሱት አቶ ብርሃኑ ከበደ፣ በወቅቱ ዋና ተቀዳሚው ም/ፕሬዚዳንት አቶ ተካ አስፋውና ዋና ፀሐፊው አቶ አሸናፊ እጅጉ ሞሪሽዬስ ውስጥ በሚደረግ የካፍ ስብሰባ ላይ ለመካፈል ሄደው ስለነበር በሎጀስቲክ ስራዎች ላይ አተኩረው እንደነበር ፣ ተቀጥረው የሚሰሩበት ከፌደሬሽኑ ውጭ ያለ ስራቸውም ለተጨማሪ ውጥረት እንደዳረጋቸው፣ በዚህ ውዥንብር ውስጥ “ደብዳቤው እንዳመለጠኝ ነው የሚገባኝ” ብለዋል፡፡ ልጆቹ ወደ ሜዳ ሲመጡ እኮ እንደ ቡድን መሪነት ብቻ ሳይሆን እንደ አሰልጣኞቹ ረዳት ሆኜ ኳሶችና የመለማመጃ ቁሳቁሶችን ይዤ ነው የምጠብቃቸው፣ ዋናው ነገር ከእጅ ላይ መጥፋቱን እንዴት ላስተውል በማለት በተሰበረ ስሜት ማብራርያቸውን የቀጠሉት አቶ ብርሃኑ፤ ከጽ/ቤት በኩልም ብርሃኑ እንደዚህ አይነት ወረቀት ሰጥተንሃል ብሎ ያስታወሳቸው እንዳልነበር በመጥቀስ፣ የልጆቹን መነሳሳት በጣም እፈልገው ስለነበር ስለሚገጥሙን ውጣ ውረዶች ለማንም ሳልናገር የጉዞ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በማስፈፀም አተኮርኩ እንጂ የቀይና ቢጫ ጉዳይ ትዝ አላለኝም ነበር በማለት አስረድተዋል፡፡ በተፈጠረው ስህተት ጥፋተኛው ራሴ እንጅ ማንም ላይ ለማላከክ አልፈልግም ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኑ ከበደ፤ ደብዳቤው አምልጦኛል፡፡ ለምን አመለጠህ ቢባል እንኳን አላውቀውም፡፡ ከማናችንም በላይ ያዘንኩት እኔ ነኝ፡፡

ወደዚህ የመጣሁት ላገለግል ልሠራ ነው፡፡ በህይወቴ እንደዚህ አይነት ነገር እንዲያጋጥመኝ አልጠብቅም ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብን በጣም ይቅርታ እጠይቃለሁ በማለት ንግግራቸውን ቋጭተዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ተጠያቂ የሆኑት ደግሞ የብሄራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝን ሰውነት ቢሻውና ሌሎች አካላት ናቸው፡፡ ያጋጠመው ጥፋት ሁላችንንም ከልብ አሳዝኖናል ያሉት አሰልጣኝ ሰውነት፤ለደረሰንበት ደረጃ ሚዲያው፣ ህብረተሰቡ፣ ስራ አስፈፃሚው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሁሉም አካላት ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውን ከገለፁ በኋላ በቡድን ነው እየተሰራ የነበረው ችግር ቢኖር ኖሮ ከሚዲያው በኩል ይጠቆመን ነበር ብዬ ነው አስብ የነበረው ብለዋል፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው አስተያየታቸውን ሲቀጥሉ ‹‹ከፅህፈት ቤቱ ተሰጥቶታል የተባለው ኮሚኒኬ ለአቶ ብርሃኑ ደርሶ ይሆናል፣ እኔ አልወሰድኩም፡፡ እሱ ባይደርሰው እኔ ከደረሰኝ መረጃው አለ ማለት ነው፡፡ በእንግሊዝኛ ቢፃፍም አነባለሁ፡፡ እንግሊዝኛ ማንበብ ባልችል ኖሮ ተተርጉሞ ይላክልኝ ነበር፡፡ ወረቀቱ አልደረሰኝም፡፡ ያ በመሆኑ እጅግ አዝናለሁ፡፡ ለአንዳችን ቢደርሰን ምናለበት፡፡ እኛ ወረቀቱም አንጠብቅም፡፡ ቢጫ ያዩትን ልጆች እናውቃቸዋለን፡፡ ምንያህል በደቡብ አፍሪካው ጨዋታ ያየው ቢጫ ካርድ አለ፣ ከዚያ በኋላ አፍሪካ ዋንጫ ተካሂዶ ከቦትስዋና ጋር ባደረግነው ጨዋታ ሁለተኛውን ቢጫ ካርድ አየ፡፡ ያንን የሚገልጽ ወረቀት ግን አልደረሰኝም፡፡

ከዚህ ውጭ የተቀጡ ልጆችን በሚደርሰን መረጃ መሰረት እንዳይሰለፉ እናሳርፋቸዋለን፡፡ ቢጫና ቀይ ያላቸው ተጨዋቾች ጋር እንነጋገራለን፡፡ ተጨዋቾችም ያለባቸውን ቅጣት በሜዳ ላይ ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ ጋር በማያያዝ ይነግሩናል፡፡›› በማለት አጠቃላይ ሁኔታውን ለማብራራት ሞክረዋል፡፡ ስህተቱን ሰርተን አንድ ደረጃ እንድደርስ የተፈጠረ ሁኔታ ይመስለኛል ያሉት ዋና አሰልጣኙ፤በምንሰራቸው ስራዎች ሁሉ በቂ ጥንቃቄና ትኩረት እንዲኖረን ያስተማረን ነው በማለት አሁንም ቡድናቸው የማለፍ ሰፊ ዕድል እንዳለው ለማስገንዘብ ጥረዋል፡፡ ‹‹የተሰደብንበት፣ ኢትዮጵያ የተሰደበችበት ውድድር ነው፣ በቢጫና ቀይ ጥፋት የምንተወው ነገር አይደለም፡፡ አንድ ታሪክ ሰርተን ቆመን በአደባባይ የምንናገርበት ስራ እኮ ነው፡፡ ማንም አሳልፎ የሚሰጠው ነገር የለም፡፡ በቃ 3 ነጥብ አጣን፣ ቦትስዋና ትወስደዋለች፡፡ ደቡብ አፍሪካን እንበልጣታለን፡፡ አስቀድሞ በነበረን እቅድ ከሴንትራል አፍሪካ ጋር ከምናደርገው ጨዋታ ሁለተኛውን ቡድን ለማሳለፍ ነበር፡፡ ያንን ማድረግ አንችልም፡፡ እስከመጨረሻው የማጣሪያ ጨዋታ ባለን ጊዜ ተጨዋቾችንን በሙሉ አቅም ሰብሰብ አድርገን አደራጅተን፣ በቂ ዝግጅት አድርገን መስከረም 6ቀን 2006 ዓ.ም ሴንተር አፍሪካን ገጥመን በማሸነፍ ለመጨረሻው የማጣሪያ ምዕራፍ እንገባለን፡፡

ለወደፊት የሚደገም ስህተት አይሆንም፡፡›› በማለትም ብሄራዊ ቡድኑ በውጤታማነት እንደሚቀጥልም በልበሙሉነት ተናግረዋል፡፡ ከአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ጋር በፌደሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ በሁለተኛ ደረጃ የተጠየቁት የቀድሞው የብሄራዊ ቡድን ረዳት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ እና የስራ አስፈፃሚው አባል እና በደቡብ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ ጨዋታ የቡድን መሪ የነበሩት አቶ አፈወርቅ አየለ ናቸው፡፡ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ፣ ባለህ የዳበረ ልምድ እንዲሁም ከኮምፒውተርና ከኢንተርኔት ጋር በነበረህ የተሻለ ቅርበት የደቡብ አፍሪካው ጨዋታ ላይ የነበረውን የቢጫ ካርድ ጥፋት እያወቅህ በቅንነት አልተናገርክም በሚል ተገምግሟል፡፡ የቡድን መሪ የነበሩት አቶ አፈወርቅ አየለ ደግሞ በ2014 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ሲጀመር፣ የቡድን መሪ ሆነው በሰሩበት ወቅት፣ የፊፋ የውድድር ህገ ደንብ ተሰጥቷቸው ለሚመለከታቸው ባለመስጠታቸውና ለተጨዋቾች በቂ ግንዛቤ እንዲፈጠር ባለመስራታቸው እንዲሁም ለተተኪው የቡድን መሪ መረጃዎችን ባለማስተላለፋቸው በቅንነት መጓደል ጥፋተኛ ተብለዋል፡፡

የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ በ3ኛ ደረጃ ተጠያቂ ያደረገው ምንያህል ተሾመን ነው፡፡ ምንም እንኳን በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ በርካታ ጋዜጠኞች በተጨዋቹ ተጠያቂነት ላይ ፌደሬሽኑ የደረሰበት ድምዳሜ የልጁን ድካምና አስተዋፅኦ ከግምት አላስገባም በሚል ውሳኔው በድጋሚ እንዲጤን ግፊት ቢያደርጉም የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ ተጨዋቹ ለተፈፀመው ጥፋት የኢትዮጵያ ህዝብን በግልፅ ይቅርታ ሊጠይቅ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት፡፡ ምንያህል ተሾመ ለስራ አስፈጻሚው ስብሰባ ተጠርቶ ሊገኝ አለመቻሉን በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የጠቆሙት የፌደሬሽኑ ፕሬዝዳንት፤ በተፈፀመው ጥፋት ተጨዋቹ በጣም ማዘኑንና መከፋቱን ከመገናኛ ብዙሃን መረዳታቸውን ገልፀው፣ ፌዴሬሽኑ ጥሪ ያደረገለት በጉዳዩ ላይ ለሚቀርብበት ጥያቄ ምላሽና ማብራሪያ እንዲሰጥ እንደነበረና እንደ ፕሮፌሽናል ተጨዋች ሙያውን አክብሮ ስህተቱ እንዳይፈፀም ባለመጠንቀቁ፣ እንዲሁም እኔ አይደለሁም ቢጫ ካርዱ የተሰጠኝ፣ አጠገቤ ለነበረው ለሌላ ተጨዋች ነው በማለት አሳማኝ ያልሆነ አስተያየት መስጠቱን ኮንነዋል፡፡ ዳኛ በቃሬዛ ለሚወጣ ተጨዋች እንኳን የካርድ ቅጣት ይሰጣል፡፡ አላወቅሁም አላስተዋልኩም ማለቱ አያሳምንም ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ማሰብ ያለበት ለብሔራዊ ቡድን፣ ለአገራዊ ኃላፊነትና ግዴታ ነበር፡፡ ያለበትን ኃላፊነት ስነምግባራዊ በሆነ መንገድ አልተወጣም፤ ስለዚህም ተጠያቂ ነው ብለዋል፡፡ የፌደሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ በ4ኛ ደረጃ ተጠያቂ ያደረገው ጽ/ቤቱ እና ዋና ፀሐፊውን አቶ አሸናፊ እጅጉ ነው፡፡

የፌዴሬሽኑ ዋና ፀሐፊ አቶ አሸናፊ እጅጉ፤ በጋዜጣዊ መግለጫ መጀመርያ ላይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫውን ማጣሪያ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ችግሩ እስከተፈጠረበት የቦትስዋና ጨዋታ ድረስ ያለውን የስራ ሂደት አስረድተው ነበር፡፡ “በማንኛውም ጊዜ በወንዶቹም በሴቶችም ብሔራዊ ቡድኖች የአፍሪካና የዓለም አቀፍ ውድድር በሚመጣበት ጊዜ ለፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት ኮሚኒኬ ይደርሰናል” ያሉት ዋና ፀሃፊው አቶ አሸናፊ እጅጉ፤ ኮሙኒኬዎች ሲደርሱ በቀጥታ የሚሰጣቸው አካላት አሉ፡፡ ኮሚኒኬዎች በተለያዩ የሰነድ ወረቀቶች ተደብቀው እንዳይቀሩ በአስቸኳይ ወዲያውኑ ለሚመለከተው አካል የምንሰጥበት አሰራር አለ በማለት ዝርዝር ማብራርያ አቅርበዋል፡፡ በአጠቃላይ ዋና ፀሐፊው የአራቱ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ግጥሚያዎች ኮሚኒኬዎች ከፊፋ ተልከው ወደ ፅህፈት ቤቱ በደረሱ ማግስት ለቡድን መሪዎች በማስፈረም፤ ኮሚኒኬው እንዲደርሳቸው መደረጉን በቀረን ማስረጃ አረጋግጠናል በማለት ለፅህፈት ቤቱ በኮፒ የቀሩ ማስረጃዎችንም አሳይተዋል፡፡

ጽ/ቤቱ ምን ማድረግ ሲገባው ምን እንዳላደረገ መግለጽ እንዳለበት የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ካሳሰቡ በኋላ፤ ዋና ፀሐፊው አሸናፊ ተጠያቂ ስለመሆናቸው በራሳቸው አንደበት እንዲናገሩ እድል በተሰጣቸው ጊዜ “ግዴታዬን በሚገባ ተወጥቻለሁ፣ ማስተዋል ነበረብህ ለሚባለው እያወቅሁ ያጠፋሁት አይደለም፡፡ ኮሙኒኬዎች ለቡድን መሪው በአስቸኳይ እንዲሰጥ አድርጌያለሁ፡፡ ተጨዋቹ ሁለት ቢጫ እንዳለበት አላየሁም፤ አለማስታወሴ ጥፋት ሊሆን ይችላል፡፡” በማለት አጠር ያለ ቃላቸውን ሲሰጡ፤ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ሳህሉ ዋና ፀሃፊው ለምን ተጠያቂ እንደሆኑ አብራርተዋል፡፡ ዋና ፀሐፊው ለፌደሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ሃላፊዎች ትኩረት በመስጠት ደብዳቤዎችን ማድረስ ሲገባው፤ በጽሕፈት ቤት በኩል ወይም በፀሐፊው አማካኝነት ደብዳቤው ይሰጠው በሚል መስራቱ ትክክል አልነበረም ያሉት ፕሬዝዳንቱ ፤ አቶ አሸናፊ እጅጉ ተገቢውን የአሰራር ስነምግባር እና ስነስርዓት በመጠበቅ በስልክ ጠርቶ በአካል ተገናኝቶ ደብዳቤዎችን ለሚመለከታቸው መስጠት ሲገባው ይህን ባለማድረጉ ተጠያቂ ነው፡፡

ለዋና አስልጣኙም ይህን አላደረገም፡፡ ስለዚህ ጽ/ቤቱ በነፈገው ትኩረት ተጠያቂ ነው፡፡ ተገቢ የሆነ ክብርና ስነምግባር ባለመከተል ለተፈጠረው ችግር አስተዋጽኦ እንደነበረው በግምግማችን አምኖ ተቀብሏል በማለት አስረድተዋል፡፡ የፌደሬሽኑ ቀጣይ ተስፋ በጋዜጣዊ መግለጫው ከበርካታ የስፖርት ጋዜጠኞች የተነሱ ጥያቄዎች የፌደሬሽኑን ስራ አስፈፃሚዎች ያስጨነቁ ነበሩ፡፡ የፌደሬሽኑ ስራ አስፋፃሚ በጋዜጣዊ መግለጫው የደረሰውን ጥፋት በወረቀት መጥፋት ማሳበቡ፤ በጠቅላላው ስራ አስፈፃሚው ሙሉ ለሙሉ ተጠያቂ መሆን ሲገባው ግለሰቦችን በተናጠል ተጠያቂ ማድረጉ ተገቢ አለመሆኑን፤ የፌደሬሽኑ አሰራር የተበላሸ እና በአማተሪዝም የወደቀ መሆኑ ለችግሩ መንስኤ እንደሚሆን እንዲሁም ፌደሬሽኑ በሀምሌ ወር መጨረሻ ጠቅላላ ጉባኤ ያደርጋል ተብሎ ሲጠበቅ ይሄው ቀነ ቀጠሮ እንዲራዘምለት ስፖርት ኮሚሽን መጠየቁን በተመለከተ በተነሱ አንኳር ጉዳዮች እና አጀንዳዎች ላይ የፌደሬሽኑ አመራሮች ምላሾችንም ሰጥተዋል፡፡ የተሳሳትነው በርካታ ፈታኝ የውድድር ምእራፎችን በማለፋችን በተደራራቢ የእድገት እና የለውጥ ምእራፎች ስንቀሳቀስ በመቆየታችን ነው ሲሉ የተናገሩት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ ‹‹በአጠቃላይ በውስጥ አካሎች ድክመት በፌዴሬሽኑ የተሰራው ስራ ሁሉ ጥላሸት ተቀብቷል፡፡ የኃላፊነትና ተጠያቂነት ስራ በየደረጃው ባለመፈፀሙ ለተፈጠረው ስህተት አዝነናል፡፡

በተጠያቂዎች ላይ ርምጃ ለመውሰድ ሰኞ የተደረገው የስራ አስፈፃሚ ስብሰባ በቂ ግዜ አልነበረም፡፡ ጊዜ ባለመኖሩ በተጠያቂዎች ላይ የሚተላለፈው ቅጣት አልተላለፈም፡፡ በተጠያቂዎች ላይ በየደረጃው በማድረጉ ስብሰባዎች የቅጣት ውሳኔዎችን እናስተላልፋለን›› ብለዋል፡፡ የፌደሬሽኑን አመራር በፕሮፌሽናሊዝም የአሰራር መዋቅር ለማጠናከር ስንቀሳቀስ ቆይተናል የሚሉት አቶ ሳህሉ ገብረወልድ፤ ባለፉት አራት አመታት የሰው ሃይል በማደራጀት፤ አሰራሮችን በማሻሻል የገቢ ምንጮችን በማስፋት ብዙ ተግባራት እንደተከነወኑ ገልፀው እውቀትና ችሎታ ያላቸውን ባለሙያዎች ከያሉበት አሰባስበን በእድገት እና ለውጥ ለመቀጠል በያዝነው እቅድ እንቀጥላለን ብለዋል፡፡ ፌደሬሽኑ ሃላፊነትን ወስዶ ተጠያቂነትን የሚሸሽበት ምንም ምክንያት የለም ያሉት የፌደሬሽኑ ዋና ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተካ አስፋው ሲሆኑ የምንሰራው በጋራ አመራር ስለሆነ ሃላፊነት አለብን ሁላችንም ጥፋት ፈፅመናል እንጅ ጥፋት ፈፅመዋል አላልንም ሲሉ አስረድተው የትም አገር ላይ ስህተት ይፈፀማል፤ አምስት አገር ተሳስቷል፡ ብቸኛዎቹ እኛ ብንሆን ምን ሊፈጠር ነበር፡፡

ስህተቱን ማሳነስ አይደለም ብሄራዊ ቡድኑ 3 ነጥብ አሳጥተነዋል ለዚህ ሁላችንም ተጠያቂ ነን፡፡ በህግ አነጋገር ሆን ተብሎ ወይም በቸልተኝነት ጥፋት አለ፡፡ እኛ የሰራነው ስህተት ግን ሁለቱንም አይደለም ›› በማለት የፌደሬሽኑን ተዓማኒነት ለመከላከል ሞክረዋል፡፡ የደረሰው ጥፋት የተቋሙ ውድቀትን አያሳይም ድክመት ግን እንዳለ ቢያመለክት ነው ያሉት አቶ ተካ፤ አስቀድመው ከነበሩት ፌዴሬሽኖች የተሻለ ሰርተናል ፤ ለውጦችም አሳይተናል፡፡ ከደቡብ አፍሪካው 29ኛው አፍሪካ ዋንጫ ስንመለስ ህዝብ በደማቅ አቀባበል ነው የተቀበለን፡፡ ዋንጫ ስላሸነፍን አይደለም ጥሩ ተሳትፎ ስለነበረን ነው፡፡ ህዝብ ዳኝነት ያውቃል፡፡ አሁን በተፈጠረው ስህተት ህዝቡ ፌደሬሽኑን አይንህን ላፈር ይለዋል ብለን አንጠብቅም፡፡ 4 ዓመታትን ሰርተናል፡፡ ለ12 አምስት ጉዳይ በተፈፀመ ስህተት መኮነን የለብንም፤ የሚሰራ ነው የሚሳተተው እኛስ መጥኔ ለሚመጣው ፌደሬሽን ነው የምንለው›› በማለትም ተጨማሪ ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡

በኢትዮጵያውያን የዲሞክራሲ እና የነፃነት ትግል ላይ ተንተርሶ የተፃፈው “የአሲምባ ፍቅር” መጽሐፍ ዛሬ እንደሚመረቅ ሜሮኢ መልቲሚዲያ አስታወቀ፡፡ 448 ገፅ ያለውን መጽሐፍ የደረሱት ካህሳይ አብርሃ ብስራት ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ እና ግንባር (ኢህአፓ/ኢህአሠ) ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ላይ ተመስርቶ የተፃፈው መጽሐፍ የሚመረቀው መስቀል አደባባይ በሚገኘው የቀይ ሽብር ሰማዕታት ብሔራዊ ሙዚየም ነው፡፡ “የአሲምባ ፍቅር” በ100 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ በሌላ በኩል “ውጥንቅጥ” የተሰኘው የግጥም መጽሐፍ ነገ እንደሚመረቅ ገጣሚው አስታወቀ፡፡ ባምቢስ አካባቢ በሚገኘው ትልቁ ዮርዳኖስ ሆቴል የሚመረቀውን የግጥም መጽሐፍ የፃፈው ዮርዳኖስ ፍቃዱ ተክለማርያም ነው፡፡

በአስራት አብርሃም የተሰናዳውና “ፍኖተ ቃየል” በሚል ርእስ “የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሽርፍራፊ ገፆች” የሚያሳየው መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ 199 ገፅ ያለው መጽሐፍ የተቃዋሚ ኃይሎችን አሰላለፍ፣ የርእዮተዓለማዊ ትግልን፣ ሕወሓትንና ሌሎችን የተመለከቱ ርእሰ ጉዳዮች አካቷል፡፡ የመጽሐፉ መሸጫ ዋጋ 45 ብር ነው፡፡ አዘጋጁ አቶ አስራት ካሁን ቀደም “መለስ እና ግብፅ”፣ “ከአገር በስተጀርባ” እና “ጎበዝ ተማሪ የመሆን ምስጢር” በተሰኙ መጻሕፍቶቻቸው ይታወቃሉ፡፡

“ኬሮ” የተሰኘው የድምፃዊት ቢጢቅ እምላዕሉ የሙዚቃ አልበም ለገበያ ቀረበ፡፡ አስራ አራት ዘፈኖች የተካተቱበት አልበም መጠርያ ወላይትኛ ሲሆን አስሩ ዘፈኖች የአማርኛ፣ አራቱ ዘፈኖች ደግሞ የእንግሊዝኛ ናቸው፡፡ ሉሽስ መልቲ ፕሮዳክሽን አሳትሞ አምባሰል ሙዚቃ ቤት እያከፋፈለ የሚገኘውን አልበም ግጥሞች ማትያስ ይልማ፣ ዲጄ ዊሽ፣ ቤቲ ሮክ፣ ዳዊት ወርቁና ሌሎችም የፃፉት ሲሆን ዜማው በማትያስ ይልማ ተዘጋጅቷል፡፡ ሙዚቃውን ያቀናበሩት ደግሞ አቤል ጳውሎስ እና ኬኒ አለን ናቸው፡፡

በአዲስ አበባ የሚገኙ ወጣቶች የሙዚቃ ምትን በመጠቀም መልእክት ማስተላለፍ በሚቻልበት መንገድ ሥልጠና ተሰጣቸው፡፡ ለሃያ ወጣቶች ለአስር ቀናት የተሰጠው ስልጠና በኢትዮጵያ ሲካሄድ የመጀመርያው መሆኑን ሥልጠናውን ያስተባበረው ኢንትራሄልዝ ኢንተርናሽናል - ኢትዮጵያ አስታውቋል፡፡ “ቢት ሜኪንግ ላብ” በተሰኘ በጀርባ ቦርሳ ሊያዝ የሚችል የሙዚቃ ስቱዲዮ በመጠቀም ስልጠናውን የሰጡት በአሜሪካ የሰሜን ካሮላይና ዩኒቨርሲቲ የሙዚቃ ፕሮፌሰሮች እና የተንቀሳቃሽ ስቱዲዮው መስራቾች ናቸው፡፡ በጤና ላይ የሚሠራው ኢንትራሄልዝ እና የዩኒቨርሲቲው የሙዚቃ ፕሮፌሰሮች ቀጣይነት ያለው ሥልጠና የወጣቶችን የሙዚቃ ክህሎት በማዳበር ወጣቱን በተዋልዶ ጤና፣ ኤችአይቪ/ኤድስ፣ በእናቶችና ሕፃናት ጤና እና በሌሎችም ማህበራዊ ዘርፎች የምት ሙዚቃ በመጠቀም ማስተማር እንደሚቻል ያሳየንበት ነው ብለዋል፡፡ ተማሪዎቹ ከትናንት ወዲያ ኮከበ ጽባሕ አካባቢ በሚገኘው የኢንትራሄልዝ ግቢ ሲመረቁ ለማስተማርያ የመጡት ተንቀሳቃሽ ስቱዲዮዎች ከወጣቶች ጋር ለሚሰሩት ለሚዩዚክ ሜይደይ ኢትዮጵያና “ሴቭ አወር ጀነሬሽን” ለተባለ ድርጅት ተለግሰዋል፡፡

  • የኢትዮጵያ ህዝብ ለእግር ኳስ ያለው ፍቅር የሚደንቅ ነው---
  • ዘፈኑ ለሚቀጥለው የእግር ኳስ ድል እንደሚደመጥ ተስፋ አለኝ--
  • ለህዝብ መንደርደሪያ እና ቀብድ ሰጥቼ ከአስር ቀን በኋላ እሄዳለሁ---

ኑሮውን በአሜሪካ ቨርጂኒያ ያደረገው ድምፃዊ ይሁኔ በላይ፣ ለዜማ ደራሲው አበበ መለሰ የመታከሚያ ገንዘብ ማሰባሰቢያ ኮንሰርት ላይ ለመሳተፍ ባለፈው ሰሞን ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጣው፡፡ የመጣበትን ጉዳይ ከፈፀመ በኋላ ያገኘችው የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው፣ ከድምፃዊው ጋር በሙያው በትምህርቱ፣ በአሜሪካ ኑሮውና በኢንቨስትመንቱ ዙሪያ ሰፊ ቃለምልልስ አድርጋለች፡፡
እንድታነቡት ተጋብዛችኋል;

 በህመም ላይ ለሚገኘው የዜማ ደራሲ አበበ መለሰ የመታከምያ ገንዘብ ለማሰባሰብ ባለፈው ቅዳሜ በላፍቶ ሞል በተዘጋጀው “ውለታ ኮንሰርት” ላይ ተሳትፈሃል፡፡ ቀደም ሲልም በአሜሪካ ከሌሎች ሙዚቀኞች ጋር ኮንሰርት እንደሰራችሁለት ሰምቻለሁ፡፡ እስቲ ጨዋታችንን በዚህ እንጀምር--- 

እስራኤል አገር ለኮንሰርት ሄጄ ነው ‹‹አቤ ታሟል›› የሚል ወሬ የሰማሁት፡፡ እኔ ካየሁት በኋላ የአቤን ጉዳይ ሌሎች አድናቂዎቹና የኢትዮጵያ አርቲስቶች እንዲሰሙና የአቅማቸውን እንዲያደርጉ ሚል እንደ ጓደኛም፣ እንደ ጋዜጠኛም አድርጎኝ --- በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ በቪዲዮ ቃለመጠይቅ አደረግንለትና በዩቲዩብ ለቀቅነው፡፡ ያኔ ነው እነ ሃይልዬ ለአቤ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ኮንሰርት ለማዘጋጀት ማሰባቸውን የነገሩኝ፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ለሚሹ ወገኖች የባንክ አካውንት ከፍተው ስለነበረም የአካውንቱን ቁጥር ከቃለምልልሱ ጋር አካተትኩት፡፡ ሌሎች ሚዲያዎችም መረጃውን እየወሰዱ ማስተላለፍ ጀመሩ፡፡
ከዛ በኋላ አሜሪካ ያሉትን አርቲስቶች አቀናጅተን ትንሽ ገንዘብ ማሰባሰብ ነበረብን፡፡ እዛ ያለው የስራ ጫናና ኑሮ ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ በአሜሪካ ከራስ አልፎ ጊዜን ለሰው መስጠት ትንሽ ይከብዳል፡፡ ሆኖም እንደምንም ብዬ አርቲስቶች በማሰባሰብ ኮሚቴ አቋቋምንና ተወያይተን ‹‹መዓዛ ሬስቶራንት›› ውስጥ የሙዚቃ ዝግጅት ለማቅረብ ተስማማን፡፡ አንዳንድ ጉዳዮች ሲኖሩን እዚያ ሬስቶራንት ውስጥ ነው የምንሰራው፡የሬስቶራንቱ ባለቤት እንደዚህ አይነት ጉዳዮች ሲኖሩ ትተባበራለች፡፡
በእዚህ ኮንሰርት ላይ የተሳተፉት እነማን ነበሩ? ምን ያህል ገቢስ ተገኘ?
የመግቢያ ዋጋው 25 ዶላር ነበር፡፡ እሱን ለመርዳት ብለው ትኬት ቆርጠው የገቡም በጥሪው ገንዘብ የሰጡም አሉ፡፡ አበበን ለመርዳት የተቻለውን ያህል ተረባርበናል፡፡ በዝግጅቱ አርቲስት መሃሙድ አህመድ ነበረበት፡፡ ሌሎችም በርካታ ሙዚቀኞች ተሳትፈዋል፡፡ ከኮሚቴው አባላት መካከል ገጣሚ አለምጸሃይ ወዳጆ፣ ጋዜጠኛ አበበ ፈለቀ፣ ፀሃይ ካሳ፣ ደሳለኝ መልኩ፣ ዳምጠው(ተወዛዋዥ) ወደ አስር ገደማ ይሆናሉ፡፡ ከቦታው ጥበት አንፃር ብዙ ታዳሚዎች አልነበሩም፡፡ ኮንሰርቱን ትልቅ አዳራሽ ውስጥ ብናደርገው ኖሮ …ችግሩ ግን አሜሪካ ሰፊ አዳራሽ ለመከራይት ክፍያው ብዙ ነው፡፡ እንደውም ገቢውን በሙሉ እንዳይወስደው በመፍራት ነው በዚያ መልኩ እንዲሆን የመረጥነው፡፡ ከኮንሰርቱ 12 ሺ 500 ዶላር (212 ሺ 500 ብር ያህል) ተገኝቷል። የገንዘብ ማሰባሰቢያ ኮንሰርቱ አሁንም ይቀጥላል። አበበ ህክምናውን ለማጠናቀቅ የሚያስችል ገንዘብ እስኪያገኝ ድረስ ህይወቱን ለመታደግ ጥረታችንን እንቀጥላለን፡፡ አርቲስቶች በዚህ ተስማምተን ነው የተለያየነው፡፡
ከሳምንት በፊት ደግሞ ከዚሁ አርቲስት ገንዘብ ማሰባሰቢያ በተዘጋጀው ‹‹ውለታ ኮንሰርት›› ላይ ለመሳተፍ ወደ ኢትዮጵያ መጣህ–
አዎ ስመጣ ሙዚቀኞች ጥናት ላይ ነበሩ። ፖስተር ሁሉ ተዘጋጅቷል፡፡ እኔ እንደምኖር ስላልታወቀ ለህዝብ አልተገለፀም ነበር፡፡ ሆኖም በሰዓቱ ደርሼበታለሁ፤ እናም ሙዚቀኞች የ‹‹ዘገሊላ ዕለት›› የሚለውን ሙዚቃዬን አጠኑልኝና ደስ ብሎኝ ኮንሰርቱ ላይ ተጫወትኩ፡፡
ከአሁኑ ኮንሰርት ውጪ ኢትዮጵያ ውስጥ ኮንሰርት ሰርተህ አታውቅም--- ለምንድን ነው?
በአሁኑ ኮንሰርት እንደ ሰርፕራይዝ ነው የቀረብኩት፡፡ ህዝቡ ናፍቆኝ ስለነበረ በዚያች አጭር ጊዜ ውስጥ ከእስክስታውና ከዘፈኑ ጋር ተዳምሮ ደስታዬን እጥፍ ድርብ አድርጎልኛል፡፡ በእውነቱ በጣም ነው የተደነቅሁት---እንዴት ደስ አለኝ መሰለሽ---የኢትዮጵያ ህዝብ ሰው ማዳን የሚችል..ፍቅር የሆነ… አንቺ ምን ዓይነት ህዝብ ነው፡፡ በጣም ነው የተደሰትኩ---.ለሙዚቃ ያለው ፍቅር..እንባዬ ሁሉ ነው የመጣው..ቦታው ጢም ብሎ ሞልቶ ነበር፡፡ ታዳሚው ይጫወታል --- ይጨፍራል-- ይደሰታል…ይሄ እንግዲህ በአዲስ አበባ የመጀመሪያዬ ኮንሰርት ነው፡፡ መቼም ያየሁት ድባብ ልዩ ነበር፡፡ ህዝቡ ከእኔ ጋር በጣም ሲዘል፣ ሲጨፍር ነው ያመሸው፡፡ አይተሽው አይደል--
አዎ አይቼዋለሁ፡፡ እኔ የምለው-- አበበ መለሰ ለአንተ ዜማ ሰጥቶሃል እንዴ?
አልሰጠኝም፡፡ ግን አበበ ይሄ ሲያንሰው ነው። ከዚህ በላይ ሊደረግለትና፣ ብዙ መስዋዕትነት ሊከፈልለት የሚገባው አርቲስት ነው፡፡..
እንግዲህ ‹‹ውለታ ኮንሰርት›› አስፈንድቆኛል ብለሃል፡፡ ወደፊትስ እዚህ መጥተህ ኮንሰርት ለማቅረብ አላሰብክም?
ለአዲስ አመት አዲሱን ሙሉ አልበሜን ለማድረስ ዝግጅቴን አጠናቅቄአለሁ፡፡ በአገኘሁት አጋጣሚ ቀን ማታ ሳልል ግጥምና ዜማዎችን እያሰባሰብኩ ነው፡፡ በነገርሽ ላይ ባለፈው እሁድ ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ ተመልክቼ በጣም ነበር ደስ ያለኝ፡፡ ከድሉ በኋላ ስቱዲዮ ገብቼ ከአዲሱ ስራዬ ውስጥ ለአንድ ጉዳይ ያዘጋጀሁት ዘፈን ነበር --- ከእርሱ ላይ ቆረጥ ቆረጥ አድርጌ ለኢትዮጵያ ህዝብ ‹‹የእንኳን ደስ ያላችሁ›› ዜማ ሰርቼአለሁ፡፡
እስኪ ከዘፈኑ ግጥም ቀንጨብ አድርገህ ንገረን--
‹‹ዛሬ ነው ዛሬ ፋሲካ ነው ደስታ ነው ዛሬ
እንኳን ደስ አለሽ ኢትዮጵያ ሃገሬ››
የሚልና ተጫዋቾቹን የሚያወድስ ነው፡፡ ይሄን ዜማ ሌሊቱን ስንሰራ አድረን ነው የጨረስነው፡፡ የሙዚቃ ባለሞያዎች እንቅልፍ አጥተው ከእኔ ጋር አድረዋል፡፡ ግጥሙ የፀጋዬ ደቦጭ ሲሆን ዜማው የእኔ ነው፡፡ እነ አበበ ብርሃኔ፣ ሄኖክና ሌሎች ጓደኞቼ አብረውኝ ነበሩ፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ለኳስ ያለው ፍቅር የሚደንቅ ነው፡፡ በባህላችን ደግሞ ድል ሲገኝ ‹‹እንኳን ደስ ያላችሁ ›› የመባባል ነገር ስላለ ነው ያንን ሙዚቃ የሰራሁት፡፡ እና ሌሊት ስንሰራ አድረን..ጠዋት ሲዲውን ለሚዲያ ልንሰጥ ስንል ግን ሌላ ነገር ተፈጠረ፡፡ አስደንጋጭ ዜና ሰማን። የእኛም ዘፈን ለጆሮ ለመብቃት ሳይታደል ቀረ፡፡ ዞሮ ዞሮ ውጤቱ ቡድናችን ለወደፊቱ ያለውን ተስፋ ጠቋሚ ነው፡፡ በተጨዋቾቻችንም እንኮራለን፡፡ ዘፈኑ ለሚቀጥለው ተመሳሳይ ድል እንደሚደመጥ ተስፋ አለኝ፡፡
አንድ ጊዜ ስትናገር--- ዘፈኖቼ ሳላስበው ከባህላዊ ወደ ዘመናዊነት እየወሰዱኝ ነው ብለህ ነበር፡፡ በአዲሱ ስራህስ?
በአዲሱ አልበም ባህላዊም ዘመናዊም ዘፈኖች ይካተታሉ፡፡ ‹‹የዘገሊላ እለት››፣ ‹‹አውማ››፣ ‹‹ዘንገና››--ሁሉም ነገሮች አሉበት፡፡ አቅሜ የፈቀደውን ያህል ጣፋጭ ዜማዎች ለህዝብ ለማድረስ እየሰራሁ ነው፡፡ ባህላዊ ነገሩ ቅድሚያ ተሰጥቶት ነው እየተሰራ ያለው.. አድማጮቼ በአዲሱ ስራዬ ትደሰታላችሁ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ስራዎቹ ባህላዊም ዘመናዊም ናቸው። ለአዲስ ዓመት የሚወጣ ሙሉ ካሴትና በቅርቡ የሚለቀቅ ነጠላ ዜማ አለኝ፡፡ መንደርደሪያ እና ቀብድ ሰጥቼ ከአስር ቀን በኋላ እሄዳለሁ፡፡
አባትህም ድምፃዊ ነበሩ ይባላል---እንደውም የአንድ ዘፈን ግጥም እንደሰጡህ ሰምቻለሁ---
አባቴ ከገጠር እየተመላለሰ ነበር የሚያየን፡፡ አባቴንም ሆነ ትልልቅ ሰዎች ወደ እኛ ቤት ሲመጡ መጠየቅ ደስ ይለኝ ነበር፡፡ አባቴንም እጠይቀው ነበር፡፡ ‹‹ለፍቅር…ለወደዳችኋት ልጅ፣ ለፋሲካም ሆነ ለገና በዓል ምን እያላችሁ ነው የምትዘፍኑት›› ብዬ ስጠይቀው፤
‹‹የዛሬን እኔ አለሁ አሳድርሻለሁ፣
ደግሞ ለነገው ይፈለጋል ሠው›› ነው የምንላት ብሎ ነገረኝ፡፡ ይሄንንም ‹‹እህና ናና ሆይና›› በሚለው ዘፈኔ ላይ ተጫውቼዋለሁ፡፡ በእኔ ሙዚቀኝነት ውስጥ የአባቴ ድርሻ ጉልህ ሥፍራ አለው። በአጠቃላይ የገጠሩ ህብረተሰብ አካል ነኝ። መሆን የምፈልገው፤ ይዤ የተነሳሁትም የአገሬን ባህል፣ቋንቋውን ማሳወቅ፣ ማስከበር ነው፡፡ ባህሌን ማሳወቅ የእኔ ግዴታ፣ ውዴታም ነው፡፡
እንደ ‹‹እህና ናና ሆይ እና››፣ ‹‹ሎጋው ሽቦ››፣ ‹‹የማይ ውሃ›› የመሳሰሉ የህዝብ ዜማዎች ትርጉማቸው ጠጠር ይላል የሚሉ ወገኖች አሉ----
በቃ እኮ ከህዝብ የሚፈልቅ ስሜት ነው፡፡ የፈጠራ፣ የጥበብ ሰው እኮ ነው ባላገር፡፡ የገጠሩ አካባቢ ሰው ሁሉም ዘፋኝ፣ አቀንቃኝ፣ ገጣሚ ነው፡፡ ቋንቋው የበሰለና ጥበብ የታከለበት ነው። በቃ ቅኔ ነው--- የህዝብ ህብረ ቀለም ያለው ቅኔ፣ የሚጣፍጥ--ከውስጥ ጥልቅ የሚል ቋንቋውና ፍሰቱ የሚያስደንቅሽ…ድንቅ ህዝብ፣ ድንቅ የባህልና የፈጠራ ባለቤት ነው ባላገር.. እኔ ይሄ ነኝ---የዚህ ህዝብ አካል፡፡
የአሜሪካ ኑሮህ እንዴት ነው?
አሜሪካ ስኖር ጎደለኝ የምለው ነገር የለም፤ እግዚአብሄር ይመስገን ሁሉ ሙሉ ነው፡፡ እኔ ደስ የሚለኝ በሃሳብ ወደ ኋላ ተመልሼ፣ የልጅነት ጊዜዬን፣ አገር ቤትን በትዝታ ስቃኝ ነው፡፡ በተለይ…ፍኖተ ሠላምን-- ያደኩበትን ሠፈር፣ጓደኞቼን አይቼ ስመለስ ስራዬን እንዴት እንደምሰራ አታውቂም! በተረፈ ግን..ብዙ ነገሮች ለእኔ ድግግሞሽ ናቸው። ልጆቼን ገጠር የአባቴ አገር ይዣቸው ሄጄ ደበሎ አልብሻቸዋለሁ፡፡ ሴትዋን ልጄን ባለገመዱን ቀሚስና መቀነት አልብሻታለሁ፡፡ ባህላቸውን አውቀው እንዲያድጉ ከከብቶች ጋር ፎቶ አንስቻቸዋለሁ፡፡ እንደውም ‹‹እምዬ ኢትዮጵያ አገረ ገነት›› የሚለው ዘፈኔ ቪድዮ ክሊፕ መፅሐፍ ቅዱስ እያነበብን ነው የሚጀምረው፡፡ ልጆቼ ይህን እንዲያገኙ፣ እንዲያውቁ፣ እንዲኮሩበት ስለምሻ ሁሌም አስተምራቸዋለሁ፡፡. ደበሎ ለብሰን አድገን በአሜሪካ የምንወልዳቸው ልጆች ባህላችንንና እኛን አያውቁንም፡፡ መሠረታችንን አመጣጣችንን አያውቁም… ብናግዛቸው መልካም ነው፡፡
ትምህርት እንደጨረስክ ነው ”ጊሽ ዓባይ” ኪነት ቡድንን የተቀላቀልከው?
ከዛ በፊት ለአንድ ወር በመሠረተ ትምህርት ዘመቻ ላይ ተሳትፌአለሁ፡፡ ባከል ገብርኤል ላይ ነበር የዘመትኩት፡፡ ገበሬው ደስ ይለው ነበር። ለአስተማሪ ትልቅ ክብር ስላለው ቤቱ አግብቶ ያበላል ያጠጣል… እንዴት ሰው ያከብራሉ መሰለሽ፡፡ በጣም ፍቅር ነው የገጠሩ ህብረተሰብ፡፡
ወደ “ጊሽ ዓባይ” እንግባ…
በ1979 ዓ.ም ነበር፡፡ ‹‹አንቱየዋ እነሱ እኮ ልጆች ናቸው ይጫወቱ በጊዜያቸው›› የሚለውን የሙዚቃ ፕሮግራም እኔ ነበርኩ ይዠው የሄድኩት፡፡ ፈጠራው የእኔ ነው፤ እኔ ነኝ የትርኢቱን ንድፍ (ስኬለተን የሰራሁት) ይሄ አለኝ ብዬ ስሰጣቸው የ “ጊሽ ዓባይ” ትርዒት ኃላፊ እሱባለው ጫኔ ..ሰማኸኝ በለው/አባት ፣ ሀብቱ/እረኛ፤ አለምወርቅ አስፋው/እናት፣ ብዙአየሁ ጎበዜ/ልጅ ሆኑና--ወዲያው ተቀነባበረ። እዛ ከደረሰ በኋላ እየተቀየረ መጣ..ሁሉም ሰው የራሱን ፈጠራ ይጨምራል..አንዱን ቀን የሰራነው ሌላ ቀን ሌላ ይጨመርበታል..እያደገ መጣ..ያን ከሰራን በኋላ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጠሩን፡፡ እድገቴ ፈጣን ነበር፡፡ በ1981 ዓ.ም ካሴት አወጣሁ..‹‹የአገሬ ልጅ ባለጋሜ ትውልደ ጎጃሜ›› የሚለውን፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ አበባ ስትመጣ ምን ዓይነት ስሜት ፈጠረብህ?
ከክፍለ ሃገር ለሚመጣ ሰው ደስ የምትል ከተማ ናት፡፡ መኪና ውስጥ ሆኜ--አዲስ አበባ ደረስን እስኪባል ድረስ አቀነቅን ነበር፡፡ የመጀመሪያው የህብረት ጉዞ ነበር፡፡ በየቦታው አብረን ነበር የምንቀሳቀሰው፡፡ ሁለተኛ ካሴት ለማሳተም ስመጣ ብቻዬን ስለመጣሁ--ትንሽ አደናግሮኝ ነበር፡፡ ከጎጃም የሚመጣ ሰው ማረፊያው ጎጃም በረንዳ ነው፡፡ ጎጃም በረንዳ ሆኜ በፊት ስመጣ ለተዋወቅኋቸው ጓደኞቼ ደወልኩላቸው፡፡ ማሲንቆ ተጫዋች አበበ ፈቃደ የሚባል አሁን ካናዳ ነው … ሁለት ቀን ከሆነኝ በኋላ ደወልኩለትና መጣ፡፡
‹‹ምን ሆነህ መጣህ›› አለኝ፡፡
‹‹ካሴት ላወጣ›› አልኩት፡፡
‹‹እና እዚህ ሆነህ ነው የምታወጣ›› አለኝ፡፡
የአዲስ አበባን የኑሮ ውድነት ስለሚያውቅ ነው እንደዚህ ያለኝ፡፡ ከዛ ይዞኝ ሄደ፡፡
የምሽት ክበብ ውስጥ አስቀጠረህ?
ጓደኛዬ ማታ ማታ ክለብ ውስጥ ይሰራ ነበር… እሱን ተከትዬ እሄድኩ ሲጫወት እሰማዋለሁ። ነገሮችን አጤናለሁ፡፡ ካሴት ካወጣሁ በኋላ ነው ካራማራ የተባለ ናይት ክለብ ውስጥ መስራት የጀመርኩት፡፡ ለአንድ ዓመት ከሰራሁ በኋላ አይቤክስ ሲከፈት፣ ሙዚቀኞችን አሰባስቤ ኮንትራት ወስጄ እየሰራሁ ሳለሁ ነው ወደ አሜሪካ የመሄድ እድል የገጠመኝ፡፡
አሜሪካ ከገባህ በኋላ በሙዚቃው ብቻ ሳይሆን በንግዱም ተሳክቶልሃል ይባላል…
አሜሪካ ሰፊ እድል አጋጥሞኛል፡፡ እንደሄድኩ ያላሰብኩት ጥሩ ፍቅር ገጠመኝ - ከአሁኗ ባለቤቴ ጋር። የባለቤቴ ራዕይና መልካም አቀራረብ ገዛኝና ጋብቻ መሰረትን፡፡ በትዳሬና በልጆቼ ደስተኛ ስለሆንኩ--በምሄድበት ቦታ ሁሉ ይቀናኛል። የመጀመሪያ ልጄ ፍቅር ይሁኔ ይባላል፡፡ ሴትዋ ሰላም ይሁኔ ትባላለች፡፡ ባለቤቴ ደግሞ የሺእመቤት ተስፋዬ፡፡ በአሜሪካ የሺእመቤት በላይ ነው የምትባለው፡፡ “ዘ በላይ ፋሚሊ” ተብለን ነው የምንጠራው፡፡ ባለቤቴ በቢዝነስ ነው የተመረቀችው---የእኔ ስራ እየዞሩ ኮንሰርት ማቅረብ ነው፡፡ በኋላ “ኢትዮጵያን የሎው ፔጅስ” የሚባል የመረጃ መጽሐፍ ማሳተም ጀመርን፡፡ እንደ ቢቢስ እና ሲኤንኤን ያሉ አለማቀፍ ሚዲያዎች ስለመጽሐፉ ብዙ ዘግበዋል፡፡ በዋሺንግተን ዲሲ የሎው ፔጅ በጣም የታወቀ ካምፓኒ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ጋር ጥብቅ ቁርኝት ፈጥሮልናል - ጥሩ መረጃ ነው የምንሰጣቸው፡፡ አሜሪካን አገር የሎው ፔጅ የሚባል ትልቅ የመረጃ መስጫ መፅሃፍ አለ - አሜሪካኖች በስፋት የሚጠቀሙበት፡፡ ባለቤቴ ያንን አይታ ነው ለምን ለኢትዮጵያ ተመሳሳይ ነገር አንጀምርም ብላ የጀመርነው፡፡ በየዓመቱ የሚወጣ ነው…በዚህ ስራ ላይ ለአስራ ዘጠኝ ዓመት ሰርተናል፡፡
በካምፓኒያችሁ አማካኝነት ከአሜሪካውያን ታዋቂ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ሙዚቀኞችና ተዋንያኖች ጋር ግንኙነት መፍጠር እንደቻላችሁ ሰምቼአለሁ--
አዎ--- ሂላሪ ክሊንተን፣ ጆን ማኬን፣ ዴንዝል ዋሽንግተን፣ ኤሪክ ቤኔ፣ ዳጊ ፍሬሽ/ራፐር/…እንዲሁም ከበርካታ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ሙዚቀኞችና ተዋንያኖች ጋር በሰፊው እንገናኛለን..በቅርቡ እንደውም አንዲት ኢትዮጵያዊት ከጥቁር አሜሪካዊ ጋር ተጋብታ እኔ ነበርኩ የሰርጉን ሙዚቃ የሰራሁላት፡፡
በፌስ ቡክ ፔጅህ ላይ የምርቃት ፎቶ አይቻለሁ። በምንድነው የተመረቅኸው?
ላለፉት ሁለት ዓመታት ትምህርት ቤት ነበርኩ፡፡ በኮምፒዩተር ቴክኖሎጂ ነው የተመረቅሁት፡፡ የኮምፒዩተር ጤንነትን በተመለከተ፣ ኮምፒዩተርን ቢዩልድ ማድረግ--ኔትዎርክ፣ ኢንተርኔት ሴኪዩሪቲ ተምሬአለሁ፡፡ ከአራት ወር በኋላ ደግሞ በ“አርት ኤንድ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ” እመረቃለሁ፡፡ ወደፊትም መማሬን እቀጥላለሁ፡፡
በአገር ውስጥስ ኢንቨስት ለማድረግ አላሰብክም?
ብዙ ሃሳቦች አለኝ፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት መጥቼ ፍኖተ ሠላምን ሳያት እየተለወጠች ነበር፡፡ አዳዲስ ግንባታዎች አሉ…በፍኖተ ሠላም ትልቅ ባዛር የተካሄደ ጊዜ “አንተም ልጃችን ነህ፤ የበኩልህን አስተዋፅዖ አድርግ” ተባልኩ፡፡ አፋጣኝ ምላሽ ነበር የሰጠሁት፡፡ ሁሉን ነገር ትቼ በሶስት ቀን ውስጥ ወደ አዲስ አበባ መጣሁ፡፡ ከዛም ወደ ፍኖተ ሠላም ሄድኩ፡፡ እንደ ጠዋት አዲስ አበባ ገብቼ ወዲያው በመኪና ተሳፍሬ ፍኖተ ሠላም ከምሽቱ አራት ሰዓት ነው የገባሁት፡፡
ህዝቡ፣ ከችኳንታ እስከ አውቶብስ፣ ባጃጁ ሳይቀር… ከፍኖተ ሠላም ተነስቶ ጅጋ የምትባል 12 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ቦታ ድረስ መጥቶ እንደ ሙሽራ አጅቦ፣ እየፎከረ እየሸለለ አጅቦ አስገባኝ---ይህን ሳይ በጣም ነው ያለቀስኩት፡፡ ስደርስ የባዛሩ መዝጊያ ደርሶ ነበር፤ ሁለት ቀን ኮንሰርት ሰርቼ ተመለስኩ፡፡ ምን ያህል ገቢ እንደተገኘ ባላውቅም ገቢው ለከተማዋ የሚውል ነበር፡፡ ኢንቨስትመንቱን በተመለከተ ግን የጀመርኩት ነገር ጥሩ ደረጃ ሲደርስ እነግርሻለሁ፡፡
በባዛሩ ኮንሰርት ላይ አንተን ይተካል ተብሎ የሚጠበቀው የአካባቢህ ልጅ ሰለሞን ደምሴ “ነይማ ላሳይስ ነይማ ጎጃም ፍኖተ ሠላም” እያለ ሲያቀነቅን የእጅ ሰዓትህን አውልቀህ ሸልመኸዋል ይባላል--
የሚገርም ድምፃዊ ነው፡፡ በጣም የሚያድግ ልጅ ነው፡፡ እኛም ድሮ እንደዚህ የሚያበረታታን ስናገኝ ደስ ይለን ነበር፡፡ ለዚህ ነው ሲጫወት ሳየው ስላስደሰተኝ የእጄን ሰዓት ፈትቼ የሸለምኩት፡፡
ቀረ የምትለው ካለ…
እግዚአብሄር ያክብራችሁ፡፡ ጎተራውን ሙሉ…አገሩን ጥጋብ ያድርግላችሁ..አይለየን..አለማችሁን ያሳያችሁ…ፍቅር፣ ሰላም፣ ደስታ ከእናተ ጋር ይሁን!

Saturday, 22 June 2013 11:04

ጭፈራችንን መልሱልን

ኩርማን መግቢያ
እግዜር ከሞላው ኩሬ ውስጥ ፣ እስቲ እንዋኝ ብለን ገብተን
ሳንጨርሰው ውሃው ደርቆ፣ መካከል ላይ ዋጋ ከፈልን!
ለኩሬ ዋናው ተጥፈን
በውቂያኖሱ ተቀጣን!
***
አለሥራችን ገብተን፣ አንጨቅጭቀው እግዜአብሔርን፤
ይቅርታ እንጠይቅ እንጂ፣ ስለመፈጠራችን፤
ለመኖሪያችንማ፣ “የቀን ውሎ - አበል” አልን!
ተጠባባቂ ቤንች እንጂ፣ ቋሚ ተሰላፊ አደለን!
የካምቦሎጆን ነገር፣ የቀመሰ ያቀዋል
ለካስ ኳስ ሳይሞቁት በፊት፣ ጨዋታው ብርድ - ብርድ ይላል፡፡
***
ጭፈራችንን መልሱልን
ያገር ብርድ ሲቆነድደን
ኳስ ሜዳውን አልቤርጐ አርገን
ድንጋይ ጠርዙን ተንተርሰን
የታክሲ ውስጥ አልጋ አንጥፈን
ሌት በዋዜማ አልመን፣ ነገን በዕውነት ልናበራ፤
ባንዲራ እንደደመራ
ከምረን በየኳስ ጐራ፤
ተውለብልበን አውለብልበን
ላንቃችን እስኪበጣጠስ፣ ሆ ብለን በማታ በቀን፤
በጭለማ ድል ጐስመን
አገር ላዕላይ ነው ብለን፤
የሰው እግር እንደጅረት፣ ጨርቅ ማሊያው እንደጐርፍ
ባንዲራውን እንደ ጅራፍ
ስናጮኸው መኪና አፋፍ፤
በጥሩምባ መለከት አፍ
የሳግ ጩኸት ሞታችንን
ስናንባርቅ ድላችንን፣
ያን መሳይ ዝማሬ ቃና፣ ያን ጭፈራ ታስነጥቁን?!
እግዜር ለድል እያበቃን፣ እኛው “የእግዜር ስተት” ከሆን
ከመዋል ከማደር በቀር፣ ለህይወትም ያው “ቤንች” ነን!!
አዬ መጥኔ ካምቦሎጆ
አድሮ የንፍገት ኮሮጆ!
በሠርግ አጋፋሪ ጥፋት፣ ከፈረሰ ድንኳን ዳሱ
ገና ሜዳ ሳንገባ፣ ከተነፈሰማ ኳሱ፤
ለምን ላገር ይትረፍ ጦሱ?
ጭፈራችንን መልሱ!!
እናንተው ተከሳሰሱ
ብቻ ሳትውሉ ሳታድሩ፣ ጭፈራችንን መልሱ!!
ሰኔ 11/2005 (ለምስኪኑ ህዝባችን)