Administrator

Administrator

ጥቃቱ ከአይሲስ ጋር ሊያያዝ ይችላል እየተባለ ነው
ባለፈው ረቡዕ ማለዳ በካናዳ ርዕሰ መዲና ኦትዋ በሚገኘው የአገሪቱ የጦርነት መታሰቢያ አደባባይና በፓርላማ ውስጥ በተከሰተውና ሁለት ሰዎችን ለህልፈት በዳረገው የተኩስ ጥቃት ዙሪያ የተጀመረው ምርመራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ሲ ኤን ኤን ዘገበ፡፡
ሚካኤል ዜሃፍ ቢቤው የተባለ የታጠቀ ግለሰብ፣  የአገሪቱን የጦርነት መታሰቢያ አደባባይ በመጠበቅ ላይ በነበሩ ሁለት ወታደሮች ላይ ተኩስ በመክፈት አንደኛውን የገደለ ሲሆን፣ ከሌሎች የጸጥታ ሃይሎች ጋር በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ሌሎች ሶስት ወታደሮችን ካቆሰለ በኋላ የግለሰቡ ህይወት ማለፉን ዘገባው ገልጧል፡፡
ጥቃቱ በተፈጸመበት ወቅት በአገሪቱ ፓርላማ ተገኝተው ለምክር ቤቱ አባላት ንግግር እያደረጉ የነበሩት የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ስቴፈን ሃርፐር ጉዳዩን በተመለከተ ረቡዕ ምሽት በሰጡት መግለጫ፣ አገሪቱ በመሰል ጥቃቶችና ነውጦች እንደማትሸበር ገልጸው፣ ጥቃቱ ካናዳ ከአጋሮቿ ጋር በመሆን ጽንፈኝነትን ለመዋጋት የያዘችውን አቋም የበለጠ እንድታጠናክር የሚያደርግ ነው፤ ጽንፈኞች እንደፈለጉ የሚፈነጩበት ምቹ ቦታ አያገኙም ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቃቱን የፈጸመው ሚካኤል ዜሃፍ ቢቤው የተባለ ግለሰብ መሆኑን ከመግለጽ ባለፈ ማንነቱንም ሆነ ድርጊቱን ለመፈጸም ያነሳሳውን ምክንያትና አላማውን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ ያልሰጡ ሲሆን፣ ስለአሸባሪው ተጨማሪ መረጃ ለማግኘትና ሌሎች ተባባሪዎች እንዳሉት ለማጣራት የተጀመረው ምርመራ በጥቂት ቀናት ውስጥ ውጤት ያስገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል፡፡በወሩ መጀመሪያ ላይም የካናዳ መንግስት በኢራቅ የሚገኙ የአይሲስ ታጣቂዎችን ለማጥቃት በሚደረገው ዘመቻ ላይ ለመሳተፍ እቅድ እንዳለው ማስታወቁን የጠቆመው ዘገባው፣ ባለፈው ሰኞ አንድ የአገሪቱ ወታደር አሸባሪ ተብሎ በተጠረጠረ ግለሰብ ሞንትሪያል ውስጥ በመኪና ተገጭቶ መገደሉን ተከትሎም፣ አገሪቱ ያለባትን የሽብር ስጋት መጠን ከዝቅተኛ ወደ መካከለኛ ደረጃ ከፍ ማድረጓን አስታውሷል፡፡
ካናዳ አይሲስ የተባለውን ጽንፈኛ ቡድን ለመዋጋት በተጀመረው አለማቀፍ እንቅስቃሴ እንደምትሳተፍ በይፋ ማስታወቋንና በቡድኑ ላይ ለሚደረገው የአየር ድብደባ ላይ የሚሳተፉ ስድስት ተዋጊ ጀቶችን ለመላክ መወሰኗን ተከትሎ ጥቃቱ መከሰቱ፣ ጉዳዩ ከአይሲስ ጋር ተያያዥ ሊሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ መፍጠሩን ዘገባው አስታውቋል፡፡አይሲስ ካናዳውያንን ለሽብር ጥቃት እየመለመለ እንደሆነ በቅርቡ ማስታወቁን ያስታወሰው ዘገባው፤ የአገሪቱ መንግስት ባለፈው ነሃሴ ወር ላይ ባወጣው ሪፖርትም፣ 130 ያህል ካናዳውያንም ወደሌሎች አገራት በመሄድ ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር መቀላቀላቸውንና ከእነዚህ ውስጥም 30 የሚሆኑት በሶርያ በሚካሄደው ጦርነት ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ ተብሎ እንደሚገመት ማስታወቁን ገልጧል፡፡
በአገሪቱ መሰል የሽብር ጥቃቶች በጂሃዲስቶች ሊሰነዘሩ እንደሚችሉ ይገመት እንደነበር የጠቆመው ሲ ኤን ኤን፤ አሜሪካም መረጃ አግኝቻለሁ በማለት በቅርቡ በካናዳ በሚገኘው ኤምባሲዋና ቆንስላዋ ላይ ያለውን የደህንነት ሁኔታ በጥብቅ መከታተል መጀመሯን አስታውሷል፡፡አይሲስም ሆነ ሌሎች ቡድኖች ለጥቃቱ ሃላፊነት አለመውሰዳቸውን የገለጸው ዘገባው፣ የአገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤትም አይሲስ ወይም ሌሎች የሽብር ቡድኖች ከጥቃቱ ጋር በቀጥታ እንደሚያያዙ የሰጠው መግለጫ በይፋ ባያስታውቅም፣ በጉዳዩ ላይ ጥብቅ ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ቢቢሲ በበኩሉ፤ በካናዳ የተለያዩ የጽንፈኛ ቡድኖች አባላትና ግለሰቦች አክራሪነትን መስበክ ከጀመሩ መቆየታቸውን በመጥቀስ፣ በአገር ውስጥና በውጭ አገራት ብጥብጦችን መፍጠር እንደሚገባ ብዙዎችን ማሳመን መቻላቸውን ዘግቧል፡፡ የአገሪቱ ፖሊስ 90 ተጠርጣሪዎችን ያሳተፉና ከሽብርተኝነት ጋር የተያያዙ 63 የብሄራዊ ደህንነት ጉዳዮችን በመመርመር ላይ እንደሚገኝ ባለፈው ሳምንት ማስታወቁንም አስታውሷል፡፡




* ተኩስ ሊያቆምና ያገተውን ሊፈታ ተስማምቷል የተባለው ቦኮ ሃራም፣ ግድያና ጠለፋውን ቀጥሏል

   ቦኮ ሃራም የተባለው የናይጀሪያ አሸባሪ ቡድን፣ በአገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የሸሪያ ህግ ተግባራዊ እንዲሆን የማስቻል አላማውን ለማሳካት ባለፉት አምስት አመታት፣ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ተደጋጋሚ የሽብር ጥቃቶችን እንደፈጸመና ከ5ሺህ በላይ ናይጀሪያውያንን እንደገደለ ይነገራል፡፡
ቡድኑ ባለፈው ሚያዝያ ወር ቺቦክ ወደተባለችው ከተማ ድንገት ብቅ ብሎ የፈጸመው ድርጊት ግን፣ ያልተጠበቀና ብዙዎችን ያስደነገጠ ነበር፡፡ የታጠቁ የቦኮ ሃራም ወታደሮች፣ አገር አማን ብለው ወደ ትምህርት ቤታቸው በመጓዝ ላይ የነበሩ 276 ልጃገረዶችን አፍነው፣ ወዳልታወቀ ስፍራ አጋዙ፡፡
ይህ ድርጊት የአገሪቱን መንግስት፣ የልጃገረዶቹን ወላጆችና የቺቦክ ከተማ ነዋሪዎችን ብቻ ሳይሆን፣ መላውን ናይጀሪያዊና አፍሪካውያንን ብሎም አለምን አስደነገጠ፡፡ መገናኛ ብዙሃን ጉዳዩን ትኩረት ሰጥተው አስተጋቡት፡፡ በአሸባሪው ቡድን የታገቱት ናይጀሪያውያን ልጃገረዶች ዕጣ ፋንታ ብዙዎችን አስጨነቀ፡፡
የተወሰኑ ልጃገረዶች ለማምለጥ ቢችሉም፣ እንደታገቱ ያሉት 219 ያህል ልጃገረዶች ጉዳይ ይህ ነው የሚባል እልባት ሳያገኝ ስድስት ወራት አለፉ፡፡ የአገሪቱ መንግስት ያሰረብኝን ታጣቂዎቼን ካልፈታ፣ ልጃገረዶቹን ለባርነት እሸጣለሁ በማለት ሲዝት የቆየው ቡድኑ፤ የሽብር ጥቃት መፈጸሙን አጠናክሮ እንደገፋበት ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡
“አላህ ልጃገረዶቹን መሸጥ እንዳለብኝ ነግሮኛል፡፡ እሸጣቸዋለሁ፡፡” ብሏል የቦኮ ሃራም መሪ ነኝ ያለ ግለሰብ ከሶስት ሳምንታት በፊት በይፋ፡፡የናይጀሪያ መንግስትም ለታገቱት ዜጎቹ ጉዳይ ተገቢውን ትኩረት አልሰጠም የሚል ትችት ሲሰነዘርበት ቆይቷል፡፡ የአገሪቱ የጦር ሃይል አባላት የሆኑ ወታደሮችም፣ መንግስት የቡድኑን ጥቃት በተገቢው ሁኔታ ለመመከት የሚያስችል ድጋፍ እያደረገላቸው አለመሆኑን መናገራቸውን የዘገበው ሲኤንኤን፣ የአሜሪካ መንግስት እገታው ከተፈጸመ ከአንድ ወር በኋላ፣ ልጃገረዶቹን የሚያፈላልጉ 80 አሜሪካውያን ወታደሮችን ወደ ቻድ መላኩን አስታውሷል፡፡በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ግን፣ የናይጀሪያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ተስፋ ሰጪ መግለጫ አወጡ፡፡ የአገሪቱ መንግስት ከአሸባሪው ቡድን ጋር ባለፈው ሳምንት በቻድ የተኩስ አቁም ስምምነት መፈጸሙንና ቡድኑ ያገታቸውን ልጃገረዶች ለመልቀቅ መስማማቱን አስታወቁ፡፡
በጀርመን መዲና በርሊን ይፋዊ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት የናይጀሪያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አሚኑ ዋሊ በበኩላቸው፤ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ ስምምነት ላይ መደረሱንና ልጃገረዶቹ በቅርብ ጊዜ ውስጥ እንደሚለቀቁ በእርግጠኝነት ተናግረዋል፡፡
“አሸባሪ ቡድኑ ልጃገረዶቹን እስከ መጪው ሰኞ ለመልቀቅ ተስማምቷል” ብለዋል፡፡ የናይጀሪያ መንግስት ቃል አቀባይ ማይክ ኦሜሪም፤ የታገቱት ልጃገረዶች በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
ሲኤንኤን እንደዘገበው፣ ቦኮ ሃራም በጉዳዩ ዙሪያ እስካሁን ድረስ የራሱን መግለጫ አለማውጣቱ ብዙዎችን አጠራጥሯቸዋል፡፡ የአለማቀፍ ፖለቲካ ተንታኞችም በሁለቱ ሃይሎች መካከል የተደረሰውን ስምምነት በጥርጣሬ እንደሚያዩት አስታውቀዋል፡፡
ቡድኑ እስላማዊ መንግስት የመመስረት ዓላማውን ለማሳካት በጦርነት ሊቀጥል ይችላል የሚሉት እነዚሁ ተንታኞች፣ ስምምነቱን ያደረገውም የበለጠ ለመደራጀትና ራሱን ለማጠናከር የሚሆን ጊዜ ለመግዛት ሲል እንደሚሆን ግምታቸውን ሰጥተዋል፡፡
መንግስት ከቡድኑ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት መፈጸሙን ቢያስታውቅም፣ የቦኮ ሃራም አባላት እንደሆኑ የተነገረላቸው ታጣቂዎች ግን በሁለት መንደሮችና በአንድ ከተማ ላይ በከፈቱት ተኩስ ስምንት ያህል ሰዎችን ሲገድሉ፣ ሌሎች ልጃገረዶችንም አግተዋል፡፡

Saturday, 25 October 2014 10:47

የፀሃፍት ጥግ

* ደራሲ ልብወለድ ሲፅፍ ህያው ሰዎችን መፍጠር አለበት፡፡ ገፀባህርያትን ሳይሆን ህያው ሰዎችን፡፡ ገፀባህርያት አስቂኝ ስዕሎች ናቸው፡፡
ኧርነስት ሄሚንግዌይ
* የፃፍኩት ነገር ፅሁፍ ከመሰለ ደግሜ እፅፈዋለሁ፡፡ በእንግሊዝኛ የድርሰት አፃፃፍ ትምህርት ላይ የተማርነው ነገር የታሪኩን ድምፀትና ዜማ እንዲረብሽ አልፈቅድም፡፡
ኢልሞር ሊኦናርድ
* መፃፍ፡፡ እንደገና መፃፍ፡፡ ሁለቱም ከሌሉ  ደግሞ ማንበብ፡፡ ሌላ አቋራጭ መንገድ አላውቅም፡፡
ላሪ ኤል ኪንግ
* ለረዥም ልብወለድ ህጎች የሉም፡፡ ኖረውም አያውቁም፡፡ ሊኖሩም አይችሉም፡፡
ዶሪስ ሌሲንግ
* ዘይቤ ማለት ዘይቤዎችን በሙሉ መርሳት ነው፡፡
ጁሌስ ሬናርድ
* ፀሐፍት ሁለት ጊዜ ነው የሚኖሩት፡፡
ናታሊ ጎልድበርግ
* የመጨረሻው ዓረፍተነገር እስካልተፃፈ ድረስ የመጀመሪያው ዓረፍተነገር ሊፃፍ አይችልም፡፡
ጆይስ ካሮል አትስ
* ምክርን ተጠንቀቅ - ይሄኛውንም ጭምር፡፡
ካርል ሳንድበርግ
* ቀስቃሽ ሰዓት አልፈልግም፡፡ ሃሳቦቼ ከእንቅልፍ ይቀሰቅሱኛል፡፡
ሬይ ብራድበሪ
* ፅሁፍ የተባለ ነገር ሁሉ ልክፍት ይመስለኛል፡፡ ልትገቱት አትችሉም፡፡
ዊሊያም ካርሎስ ዊልያምስ
* ሁልጊዜ መፃፍ የምጀምረው በንፁህ ወረቀትና በቆሻሻ አዕምሮ ነው፡፡
ፓትሪክ ዴኒስ
* መፅሐፍ የሃሳብ መያዣ ብቻ ነው - ልክ እንደጠርሙስ፡፡ ዋናው ጉዳይ መፅሃፉ ውስጥ ያለው ቁም ነገር ነው፡፡
አንጄላ ካርተር

Saturday, 25 October 2014 10:35

የፍቅር ጥግ

(ስለአማች)
አዎ፤ ህይወት የተሻለ ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን የከፋም ሊሆን ይችላል፡፡ አላመንሽኚም? እንግዲያውስ ከአማችሽ ጋር እንዳስተዋውቅሽ ፍቀጂልኝ፡፡
ጃሮድ ኪንትዝ
አማቴ በጣም ተናደውብኝ ሁለተኛ እንደማያናግሩኝ ምለው ተገዘቱ፡፡ እኔም ፈገግ አልኩና ፈጣሪ ላደረገልኝ ትንሽዬ ተዓምር ምስጋናዬን አቀረብኩ፡፡
ጃሮድ ኪንትዝ
ከአማቴ ጋር ምንም ዓይነት በጎ ግንኙነት ባይኖረንም “እማዬ” ብዬ እንድጠራቸው መወትወታቸውን አልተዉም፡፡
ጄምስ ሳንድሮ
የምታገባትን ሚስት በምናብህ ስትስል አማትህንም እንዳትዘነጋ፡፡
ያልታወቀ ሰው
ከእያንዳንዱ የተሳካለት ወንድ ጀርባ ተጠራጣሪ አማት ቆመዋል፡፡
ያልታወቀ ሰው
በማለዳ ጸዳልና በአማትሽ ፈገግታ እርግጠኛ አትሁኚ፡፡
የጃፓኖች አባባል
አዳም በዓለም ላይ ዕድለኛው ሰው ነበር - አማት አልነበረውም፡፡
ሾሎም አሊቼም
 ከአስደሳች ጉዞ መመለሴ ነው፡፡ አማቴን ኤርፖርት አድርሼ መጣሁ፡፡
ሔኒ ያንግማን
አማቴን ለሁለት ዓመት ያህል አላነጋገርኳቸውም፡፡ ከዝምታቸው ላናጥባቸው አልፈለግሁም፡፡
ኬን ዶድ -
ከእያንዳንዱ ስኬት ጀርባ የኮራች ሚስትና ተጠራጣሪ አማት አሉ፡፡
ብሩክ ሃይስ

        ሲንጋፖር ውስጥ የሚገኘው የናንያንግ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በ2 ደቂቃ ጊዜ ውስጥ ቻርጅ ተደርጎ 70 በመቶ ሃይል ማጠራቀም የሚችልና ለ20 አመታት ያህል አገልግሎት መስጠት የሚችል የተሻሻለ ዘመናዊ የሞባይል ባትሪ መስራታቸው ተዘገበ፡፡
 ሳይንስ ዴይሊ ድረገጽ እንዳስነበበው፣ ተመራማሪዎቹ ከዚህ ቀደም ይጠቀሙበት የነበረውን ግራፋይት የተባለ የባትሪ አካል ከቲታኒየም ዳይ ኦክሳይድ በተሰራ የተሻሻለ መሳሪያ በመተካት ነው፣ ሃይል የማጠራቀም አቅሙ ከፍተኛ የሆነ አዲስ የሞባይል ባትሪ የሰሩት፡፡
ይህ የባትሪው አካል የኬሚካል ኡደቱን የሚያፋጥን ሲሆን፣ ባትሪው ተደጋግሞ ቻርጅ መደረግ የሚችልበት መጠንም በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር አስችሎታል ተብሏል፡፡ መደበኛው ሊቲየም አይዎን ባትሪ በአገልግሎት ዘመኑ ሃይል የማጠራቀም አቅሙ ምንም ሳይቀንስ በተደጋጋሚ ቻርጅ ሊደረግ የሚችለው ለ500 ጊዜያት ያህል ብቻ ሲሆን፣ አዲሱ ባትሪ ግን እስከ 10 ሺህ ያህል ጊዜያት ቻርጅ ሊደረግ ይችላል፡፡ አዲሱ የሞባይል ባትሪ በሁለት አመታት ጊዜ ውስጥ በብዛት ተመርቶ ለገበያ እንደሚቀርብ ተነግሯል፡፡
ሳይንቲስቶቹ ከሞባይል ባትሪው በተጨማሪም በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰሩ መኪኖችን ባትሪዎች በተመሳሳይ ሁኔታ አሻሽለው የመስራት እቅድ እንዳላቸው ዘገባው ጨምሮ ገልጿል፡፡

አሜሪካዊው ቢሊየነር ዋረን ቡፌት 400 ሚሊዮን የአክሲዮን ድርሻ የያዙበትንና ከታላላቅ የኢንቨስትመን መስኮቻቸው አንዱ የሆነውን የኮኮካ ኮላ ኩባንያ ጨምሮ፣ በተለያዩ ኩባንያዎቻቸው በደረሰባቸው ኪሳራ በ2 ቀናት ውስጥ 2 ቢ. ዶላር ማጣታቸውን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡ ባለፈው ሰኞ የተከሰተው የ7 በመቶ የአክሲዮን ዋጋ ማሽቆልቆል፣ አይቢኤም ቴክ30 የተባለውን ኩባንያቸውን 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ያሳጣቸው ባለጸጋው ቡፌት፤  በነጋታው ደግሞ ኮካኮላ ኩባንያ ካቀደው ዕለታዊ ገቢ 6 በመቶ ቅናሽ በማሳየቱ 1 ቢሊዮን ዶላር አጥተዋል፡፡አመቱ ለቡፌት የኪሳራ ነበር ያለው ዘገባው፤ ቴስኮ የተባለው ኩባንያቸው አመታዊ ትርፍ 47 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን አስታውሷል፡፡
የአክሲዮን ገበያ ዋጋ እያሽቆለቆለ ቢመጣም ታዲያ፣ ዋረን ቡፌት ግን የአክሲዮን ድርሻ መግዛታቸውን እንደቀጠሉ በሰጡት መግለጫ  ማስታወቃቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡

Saturday, 25 October 2014 10:28

የህፃናት ጥግ

ሞቶ ገዳይ
እግሬን ዛሬ ወስዶ - እጄን እያስቀረ
እያማ ሊበላኝ - ማሰቡ ካልቀረ
የግፍ ጥርሱ ገጦ----
በኔ ጣር አጊጦ-----
ይኖራል እንዳይል የአዳኜ ሹል ስልጣን
አፈንድቼ እምጥል - ስለምሆን ቁንጣን
ቀስ በቀስ ስሞት እንዳይበዛ ነውሬ…፣
            ባንዴ እሚሰለቅጥ - እዘዝልኝ አውሬ፡፡
     ድኖ መግደል!
አምና የዛሬ አመት  - እሁድ አጠባብ ላይ
ሳይፈልጠው ሳይቆርጠው - ታዝዞበት ከላይ
በእለተ ፋሲካ - በሚዳንበት ቀን
ልጅ ሞቶብን ድንገት . . . ከአፈር ጋር አስታርቀን
ቀብረነው ስንመጣ . . . ቢሆነን ሰቀቀን
ይህን ብላቴና . . . ገና እሱ ተፈርቶ
እንዴት ይወስደዋል - ያለ ቀኑ ጠርቶ
አየ የሱ ነገር - አይገርመው እይጨንቀው
የእናትና ልጅን ነገር እያወቀው
ከቀንም ቀን መርጦ ያውም በፋሲካ
ይኸ የማርያም ልጅ . . .
እንዲያው ባል አያውቅም - ስራ አይፈታም ለካ
እያልን እያማን ሳል . . .  ፈጣሪን በትዝብት
መፅናናት ልንፈጥር ለሟቹ እናት አባት
ድንገት የልጁ አባት - ስሜቱ ገንፍሎ
በሚያባባ ዜማ - ጉሮሮውን ስሎ
ፈጣሪን ወቀሰው - አማው እንዲህ ብሎ
“እንደዚህ ያለ ፍርድ - የተገመደለ
በትንሳኤው ምድር - ስንት ቀን እያለ
ኧረ የጉድ አገር - እግዜር ተሳስቶ
ልጄን ገደለብኝ - የራሱን ተነስቶ”፡፡
(ለእየየ)

ስርዝ ድልዝ
ደም የሚፈሰው ልብ በሹል ጦር ተወግቶ
ከጎን ፅጌሬዳ . . .
እምቡጡ ፈንድቶ በቀይ እስክሪቢቶ …
ከሳለችበት ሉክ ከጥቅሱ ቀጥሎ
የላከችልኝን የፍቅር ደብዳቤ …
ሊያነብ እጄ ሲገልጥ እጥፋቱን ነጥሎ
ቁልጭ ካለው ፅሁፍ ከተደረደረው
ልቤ የጓጓለት ሊያነበው ያማረው
መቼ ዝርዝሩን ሆነ የፍቅሯን ሀተታ
ድልዙን ቃል እንጂ . . .
ያስቀረችብኝን ሰርዛ አመንትታ፡፡

(በቅርቡ ለንባብ ከሚበቃው “ቁመታም ጾም” የተሰኘው የአያሌው እውነቴ የግጥም መድብል)

ከእለታት አንድ ቀን አንድ ሚስቱ ላይ የሚኮራ የሚኩራራ ጉረኛ ባል ነበረ፡፡ አንድ ማታ ሲመጣ ክፉኛ ተፈንክቷል፡፡
“ምነው ውዴ! ምን ነካህ?” አለችው ሚስቱ፡፡
“ዛሬ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?” አለና ጀመረ፡፡
“ምን ሆነ የእኔ ጌታ?”
“አንዱ አጉል ልታይ ልታይ ባይ ጉራውን ሲነዛ አግኝቼው ‹እረፍ!› አልኩት”
“ማ? ማነው እሚያርፈው?” አለኝ፡፡
“አንተ ነሃ! ካንተ ሌላ ጉራ እሚነዛ አለ እንዴ?”
“አፍህ ካላረፈ እኔ ራሴ አሳርፍሃለሁ! አይለኝም?!”
‹በቃ ወጣ ብለን መተያየት ነዋ!› አልኩትና ቀድሜ ወጣሁ ከቡና ቤቱ፡፡”
ሚስትየውም “ከዛስ?” አለችው፡፡
ባል “እሱም ተከትሎኝ ወጣ!”
ሚስት “ከዛስ?”
ባል “ቀድሜ ቡጢ አቀመስኩት”
ሚስት “ከዛስ? ወደቀ?”
“አይ አልወደቀም”
“ታዲያ ምን ሆነ እሺ?”
“ተቀማመስን”
“ከዚያስ?”
“ከዚያማ እንደምታይኝ ተፈነከትኩ”
“ይሄማ ቡጢ አይደለም!... ዱላ ይዞ ነበር?”
“አይ አንቺ! ወንድ መስሎሻል? ዱላ ይዞ የሚዞር፣ የእኔኑ ነጥቆ ነው እንጂ!?”
*  *    *
የሀገራችን ታሪክ ይሄው ነው! ዱላ ያልያዘው መቺ ነው! ምነው ቢሉ፤ ባለ ዱላው ያቀብለዋልና! ተከራካሪው የሚያቀርበውን ሙግት ተፃራሪው ወስዶ ይሟገትበታል፡፡ “ከሞኝ ደጅ ሞፈር ይቆረጣልም” ነው፡፡ ያም ሆኖ የማታ ማታ ዱላ አቀብሎ ለመፈንከት አጉል መፎከር የቂል ቆንሲል መሆን ነው፡፡ ውስጠ - ሚስጥሩ ጥልቅ ነው፡፡ እነ ሆቺ ሚን በየዋሁ ዘመን “የመሣሪያ ምንጫችን ጠላታችን እራሱ ነው ይሉ ነበር!” ዛሬ ያ የሞኝነት መንገድ ይመስላል!
ችግር እያለብን ችግር የለብንም አንበል፡፡ “መንግስት ማለት የአገሩ አዕምሮ እንጂ የልቡ ሮሮ ብቻ አይደለም” ይላል የአገራችን ዋና ገጣሚ፡፡ ይህን አንርሳ!
“የአብራሄ - ህሊና፣ ዘመን  ፈላስፎች እነስፒኖዛ፣
ሎክ፣ ካንት፣ ሚል፣ ቮልቴር እና ዘመናዊዎቹ እነ ራሰልና ፐፐር … ሁሉም፡፡ ህይወት ማለት ችግር መፍታት ነው፤ ይላሉ፡፡ ምንም ፍፁም ነገር የለም! እድገት ሊመጣ የሚችለው ጥብቅና ኮስታራ እሳቤ ካለ ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ከጭንቀት ነፃ የሆነ ነፃነትና ለታላቅነት ዕውቅና የመስጠት ብቃት ሲኖር ነው፡፡ ግን ድክመትን ለማሳየት አለመፍራት! ካለ ነው!” ይላሉ፡፡ የተባለውን ማጣራት የእኛ ፈንታ ነው፡፡ ህይወት ማለት ችግር መፍታት ነውና፡፡ ይህን ያላስተዋለ በችግር ላይ ችግር ቢፈጥር ውጤቱን እሱና እሱ ብቻ ነው የሚያገኘው!!
ከትዕዛዝ አክባሪነት ይልቅ ምክን ሊመራን ይገባል (ስፒኖዛ)፡፡  ትዕዛዝ አለማክበር በፍፁም ግብረገብነት አኳያ ሲታይ እንደጥፋት ይቆጠር ይሆናል፡፡ እንደሎሌነት ሲታሰብ ግን ትዕዛዝን መበገር አግባብ ይሆናል፡፡ ጌታ የሚያዘው የጌትነቱን ልክ ማሳያ አድርጎ ነውና!! አንዳንዴ “ልጅነትን የመሰለ ንፅህና የለም” የሚባለውን ለመቀበል መገደድ አግባብ ነው”፡፡ ቅንነት ወሳኝ ነው ለማለት ነው! ከትላንት ለመማር ቅንነት ያስፈልጋል፡፡ ቂም በቀል ሆድ ውስጥ ካመቅን ነገ ተመልሰን ወደዚያው ስህተት እናመራለን፡፡ ያ ከሆነ ከድጡ ወደማጡ መሄድ ነው፡፡ በራሳችን የትላንት ንፍቀ ክበብ ታጥረን፣ ሌላ ለማየት ተገድበን ያለፈው መርግ ከተጫነን፤ አባዜው አልለቀቀንም ማለት ነው፡፡ ገጣሚው እንዳለው፡-
“ያለፈው አልፏል እያልን፣ ዛሬም ወደዚያው ከሄድን
ድግግሞሹ ካጫጨን፣ እኛስ ከትላንት ምን ተሻልን?!”
ከክፋት ወደ ክፋት፣ ከኋላ ቀርነት ወደ ኋላቀርነት፣ ከጥፋት ወደ ጥፋት እንዳንሄድ አስተዋይ ልቦና ይስጠን፡፡ በስራም ቦታ፣ በፖለቲካ ዳርትም ሥፍራ፣ በህዝብ መሰብሰቢያም ሸንጎ፣ በኮንፈረንስና በሴሚናርም፣ በማህበረሰብም፣ በቤተሰብም፣ መልካም ነገሮችን ካላቆየን፤ ከአንዱ ወደ አንዱ መሄድ ከውድቀት ወደ ውድቀት፤ ከድቀት ወደ ድቀት እንደ መጓዝ ነው፡፡ የሀገራችን ገጣሚና ፀሐፌ ተውኔት ፀጋዬ ገ/መድህን እንዳለው፤
“ያገሬ ሰው ነገር፤ አብረን ወደላይ እንብቀል ሲሉት፤ አሸብልቆ ወደታች ወደመሬት ማጎንቆል” ይሆናል፡፡ የዚህ ውጤቱ የአፍሪካው ተረት ነው - “ከክፉ በሬ ጋር ውለህ፣ ወደ ክፉ ሚስት አትሂድ!”


Saturday, 25 October 2014 10:15

የህፃናት ጥግ

የ4 ዓመት ህፃን ከእናቱ ጋር የፎቶ አልበም ሲመለከት ዓይኑ ነፍሰ ጡር ሆና የተነሳችው ፎቶ ላይ ያርፋል፡፡
ህፃን - ማሚ፤ ሆድሽ ለምን ትልቅ ሆነ?
እናት - አንተ ሆዴ ውስጥ ስለነበርክ፡፡
ህፃን - ያኔ ውጠሽኝ የነበረ ጊዜ?
***
ሴትየዋ የ3 ዓመት ዕድሜ ካለው የልጅ ልጃቸው ጋር በስልክ ሲያወሩ ህፃኑ የሚላቸው ስላልተሰማቸው አስሬ “ምን? ምናልከኝ?” እያሉ ያስቸግሩታል፡፡ ህፃን ሆዬም፤ “እማማ፤ ጮክ ብለሽ እያዳመጥሽኝ አይደለም?” አላቸው፡፡
***
አያት የ3 ዓመት ህፃን የሆነውችን የልጅ ልጃቸውን ለማጫወት ያስቡና፤ “ቶሎ ቶሎ እያደግሽ እኮ ነው፤ ትንሽ ቀስ ማለት አለብሽ” ይሏታል፤ እየሳቁ፡፡
ህፃኗ ኮስተር ብላ፤ “የእኔ ጥፋት እኮ አይደለም”
አያት ተገርመው፤ “ታዲያ የማነው?”
ህፃን፤ “የማሚ!”
አያት “እንዴት?”
ህፃን፤ “እሷ ናታ … ቶሎ ቶሎ ልደቴን እያከበረች”
* * *
የ8 ዓመት ህፃን ለእጅ ሥራዋ የሚሆን ጨርቅ ለመቆራረጥ እናቷን መቀስ እንዲሰጧት ትጠይቃለች፡፡ እናትም በአቅራቢያቸው የነበረውንና የወርቅ እጀታ ያለውን ውብ መቀስ አንስተው ሰጧትና፤ “በጥንቃቄ ተጠቀሚበት፤ ለእኔ ትልቅ ትርጉም አለው” ይሏታል፡፡
ህፃን፤ “ዕድሜው ብዙ ነው እንዴ?”
እናት ልጃቸው የመቀሱን ታሪክ የማወቅ ፍላጎት ያደረባት ስለመሰላቸው ማስረዳት ጀመሩ፤ “ከእናቴ ነው የወረስኩት፤ እሷ ደሞ ከእናቷ … እናቷም ….”
ህፃን፤ “ለዚህ ነዋ…”
እናት፤ “ምን የሆነው?”
ህፃን፤ “ዶልዱሞ የማይቆርጠው”

“ክቡር ጠ/ሚ አባታችንን ከሞት ያድኑልን”  የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ልጆች

የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን በእስር ላይ በሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ ከአምስት አመታት በፊት የተጣለው የሞት ፍርድ ተፈጻሚ እንዳይሆንና በቆንስላ ሰራተኞች መጎብኘት እንዲችሉ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በግላቸው በላኩት ደብዳቤ መጠየቃቸውን ዘ ኢንዲፔንደንት ከትናንት በስቲያ ዘገበ የአቶ አንዳርጋቸው ልጆች አባታቸውን ከሞት እንዲታደጉላቸውና ከእስር ተፈትተው ዳግም የሚገናኙበትን መንገድ በማመቻቸት በኩል ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው የሚጠይቅ ልብ የሚነካ ደብዳቤ እንደላኩላቸው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን፣ የልጆቹን ጥያቄ መነሻ በማድረግ ለጠቅላይ ሚንስትር ሃይለማርያም ደብዳቤ መላካቸውን አስታውቀዋል፡፡
የእንግሊዝ የስራ ሃላፊዎች በእስር ላይ የሚገኙትን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በቋሚነት መጎብኘት እንዲችሉ ግፊት ቢያደርጉም፣ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት በጎ ምላሽ እንዳልሰጡ ለልጆቹና ለእናታቸው በሰጡት ምላሽ የገለጹት ዴቪድ ካሜሩን፣ ከዚህ በፊት የተደረገው ጥረት ውጤታማ አለመሆኑን በማጤን በግላቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ደብዳቤ መላካቸውን አመልክተዋል፡፡የእንግሊዝ መንግስት የቆንስላ አባላት አንዳርጋቸው ጽጌን በቋሚነት መጠየቅና ማማከር የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻችና መንግስታቸው ሲቃወመው የቆየው የሞት ፍርድ ተፈጻሚ እንደማይሆን ማረጋገጫ እንዲሰጥ በላኩት ደብዳቤ መጠየቃቸውን የገለጹት ዴቪድ ካሜሩን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለ ማርያም ለደብዳቤያቸው በጎ ምላሽ እንደሚሰጧቸው ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል፡፡
የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ልጅ የሆነችው የ7 አመቷ ምናበ እና መንታ ወንድሟ ይላቅ፣ ለጠቅላይ ሚንስትር ዴቪድ ካሜሩን በላኩት ደብዳቤ፣ “አባታችን ልጆቹን የሚወድና የሚንከባከብ መልካም አባት ነው፡፡ አባታችንን ከእስር ለማስፈታት ምንድን ነው የሚያደርጉልን?” በማለት መጠየቃቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ የመጀመሪያ ል©cW የ15 አመቷ ህላዊት በበኩሏ፣ “አባታችን በጣም ናፍቆናል፡፡ እባክዎት በቅርብ ጊዜ መልሰው ወደ ቤታችን ያምጡልን” በማለት ስሜቷን እንደገለፀች ዘገባው ጠቁሟል፡፡