Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

Saturday, 10 September 2011 11:58

2ሺ30 ዓ.ም ትንቢታዊ ልቦለድ

መስከረም፣ 2030 ዓ.ም
አዲስ አበባ
አራት ኪሎ ጋዜጣ ተሳልጬ (ተከራይቼ) ለማንበብ ተራ በመጠበቅ ላይ ነኝ፡፡ የግል ጋዜጣ እና ጋዜጠኛ ተቀዶና ተሰዶ አልቋል፡፡ የአገሬዉን ህዝብ ለማቅናት ሀላፊነቱ ሙሉ በሙሉ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጫንቃ ላይ ወድቋል፡፡ ይህ ነባር ጋዜጣ የተጣለበትን ሰፊ የሕዝብ አደራ ለመወጣት ወርድና ቁመቱን በእጥፍ ከማሳደጉም በላይ ራሱን እንደ አሜባ በማብዛት አንድም ሦስትም ለመሆን ተገዷል፡፡ ዘመን ፖለቲካ፣ ዘመን ስፖርት፣ ዘመን ልማት - ሦስት ቤተሰብ መስርቷል፡፡ ..በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ ጋዜጦች ቁጥር ከአንድ ወደ ሶስት አሻቀበ.. የተባለውም አዲስ ዘመን ራሱን ሦስት በማድረጉ ነው፡፡

Saturday, 10 September 2011 11:51

የዓመቱ ድንቅ እና ቅዥት

የዓመቱ ድንቅ - በኢትዪጵያን አይዶል፣ የታዳጊ ሃና ግርማ ድምጽ
የዓመቱ እፎይታ - መብራት ብርት ጥፍት ማለቱ (ጠፍቶ አለመቅረቱ)
የዓመቱ ቅዠት - የዋጋ ቁጥጥርና የራሽን ወረፋ (ጓድ፣ጓድ - የኮሙኒዝም ፕሪቪው)
የዓመቱ ኅብረት - ፖርላማ፣ ቢዝነስ፣ ዘፈን፣ አትሌቲክስ፣ ኑሮ ወዘተ በጋራ መፍዘዛቸው

የዘንድሮ ነገር! ለህዳሴ ግድብ ግንባታ የመሰረት
ድንጋይ ከመተከሉ ጋር፤ በየጊዜው እልም
የሚለው ኤሌክትሪክም ሳይጠቀስ መታለፍ
አለበት? የተለመደ ነው ትሉ ይሆናል - የቧንቧ
ውሃምኮ፤ ሲመጣ ሲሄድ ከርሟል በማለት፡፡
እያማረርኩ መስሏችኋል፡፡ GN አይደለም፡፡

ከተቻላችሁ ደህና ደህናውን አውርሱን፤ ካልቻላችሁ ገለል!..
ኦሮቢንዶ የተባለ ህንዳዊ ፈላስፋ፤ ..ምንም ጠንካራ ብትሆን መጨረሻ ላይየምትሸነፍበት ጦርነት አትጀምር..
ይላል፡፡በአቦይ ስብሀትና በፕሮፌሰርመስፍን መካከል እንደዋዛ
የተጀመረው የጋዜጣ ላይ አስጥ አገባ
መጀመሪያ ላይ የወደድኩትን ያህል ሄዶ ሄዶ ወደ ዘር ፖለቲካ በመቀየሩ ማዘኔ አልቀረም፡፡ ትልቅ ሰው ድሮ ቀረ! ብዬ ዝም እንዳልል ደግሞ እነዚህ ራሳቸው የድሮ ሰዎች ሆኑብኝ! ከዚያና ከዚህ ሆነው እኛና እነርሱ እያሉ ይጠዛጠዙ ገቡ፡፡ ይኸው እኔንም ጎትተው አስገቡኝ፡፡

አሮጌውም ወደ ኋላ ቀረ፡፡ አዲሱ ዓመት አዲስ ተስፋ ይዞልን ስለመምጣቱ
አስረግጠን መናገር ባንችልም አሮጌው ዓመት ጭኖብን ያለፈውን የኑሮ ቀንበር ወደ ኋላ መለስ ብለን መታዘብ አይቸግረንም፤ አዲሱ ዓመት በአዲስ ተስፋ ሞሻሽሮ ከፊታችን የሳለብን የሚያጓጓ ህይወት ስለመኖሩ አፋችንን ሞልተን ለመናገር ቢገደንም፤ አሮጌው ዓመት በኑሮ ውጥንቅጥ አጨመላልቆ በወጉ ሳናጣጥመው የነጠቀንን፣ ድፍርስ ህይወት፣ እያሰብን አንዳንድ ነገሮችን መዘከር አያቅተንም፡፡ ነገን መተንበይ የሚያስችል የነቢይነት ዓቅም ባይኖረንም ትናንትን ቆም ብሎ ለመገርመም፣ ትዕግስት አያንሰንም፡፡

Saturday, 10 September 2011 11:38

|ሌባ እና ፖሊስ..

አንድ ኬንያዊ ህፃን ..ስታድግ ምን መሆን ትፈልጋለህ?.. ብላችሁ ብትጠይቁት እንደ እኛ ሀገር ህፃን ..ዶክተር.. ወይም ..ኢንጂነር.. ይላል ብላችሁ  እንዳትጠብቁ፤ ካለምንም ማመንታት ፖሊስ ሊላችሁ እንደሚችል እርግጠኛ ሁኑ፡፡ ናይሮቢ ሌላም ገድል አላት፡፡ ፖሊሶቹ ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ የማይወጥኑት ነገር የለም፡፡ አንድ ስደተኛ ገንዘብ አልከፍልም ካለ ድብደባ ይደርስበታል ብላችሁ እንዳትሰጉ፡፡ ወይም ደግሞ ሕገ ወጥ ስደተኛ ነው በሚል ፍርድ ቤት ይቀርባል ተብሎ አይታሰብም፤ ሌላ ዘዴ አለ፡፡

Saturday, 10 September 2011 11:34

ጉዱ ካሳ ናፈቀኝ!

ጋዜጠኛ፤ ሰዓሊና የጥበብ ታሪክ አጥኚ የነበሩት ስዪም ወልዴ ራምሴ ግለ-ታሪካቸውን በጻፉበት ..ኩረፊያ የሸፈነው ፈገግታ.. መጽሀፋቸው ላይ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ካሰፈሯቸው ትዝብቶች በአንዱ እንዲህ ..የህጉ ሰው በኢኮኖሚስቱ ሙያ ላይ ወይም ኢንጂነሩ በሕክምና ላይ ወይም ሐኪሙ በግብርና ላይ ወዘተ የመሰለወን ሀሳብ ከመስጠት የሚቆጠበውን ያህል በሌሎች መስኮች የተሰማሩ ባለሙያዎች በባህል ጥያቄ ላይ ሃሳብ ለመሰንዘር ቅንጣት ያህል አያቅማሙም፤ አሁን  በጋዜጣ፤ በመጽሔት፤ በሬድዮና ቴሌቭዥን ከዝነኛ ሰዎች አንደበት የሚባሉትን ነገሮች ላነበበና ለሰማ ስዩም ወልዴ ከአስርት አመታት በፊት የታዘቡት በባህልና ጥበብ ነክ ጉዳዮች ላይ የሚሰጡ ደፋርና ጥራዝ-ነጠቅ አስተያየቶች፣ በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ህክምና ኢኮኖሚክስ ግብርና በሚል መስክ መምረጥ  እንዳቆሙ ቢሰሙ ምን ይሉ ነበር

በጥንት ዘመን በፖላንድ አገር የኑሮውድነት በጣም ከፋና አሉ፤ ከባድ የሥጋ እጥረት ተፈጠረ፡፡ ህዝቡ በጣም ተማረረ፡፡ ዝቅተኛው የሠራተኛ መደብ ብዙ ብዙ ጥያቄ እያነሳ ምሬቱንይገልጽ ጀመር፡፡ በዚህ የፖላንድ የሥጋአጥረት ላይ በመመሥረት በርካታ ቀልዶች፣ ተረቶችና ዕንቆቅልሾች እንደጉድ ፈሉ፡፡ እንደማንኛውም አገር፡፡ እንደሚከተለው ያሉ፡-
ከዕለታት አንድ ቀን በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት፣ አለም በሁለት ጎራ ፍርጥም ብላ ተከፍላ በነበረች ጊዜ፤ ባንድ ፊት አሜሪካ፣ በሌላ ፊት ሩሲያ ነበሩ መሪ ተዋንያኑ፡፡ ታዲያ በአንድ የቴሌቪዥን የጥያቄ ፕሮግራም ላይ የመጨረሻውን ማጣሪያ አልፈው ለዋንጫ የደረሱት አገሮች በመወዳደር ላይ ናቸው፡፡ የህንድ ምሁር፣ የአሜሪካ ምሁርና የሩሲያ ምሁር ናቸው የመጨረሻ ተጋጣሚዎቹ፡፡
ጥያቄውን የሚያቀርበው የቴሌቪዥን ፕሮግራም መሪ፤ እንዲህ ሲል ጠየቀ፡-
Why is there a shortage of meat in Poland?
በፖላንድ የሥጋ እጥረት ለምን ኖረ፤ እንደማለት ነው፡፡

ኦሳማ ቢላደን በፓኪስታን አቡታባድ በተባለው ቦታ በአሜሪካ ልዩ ኮማንዶዎችከተገደለ በኋላ፣ አሜሪካ በየመንና በሶማሊያ የሚገኙ የአልቃይዳ ቡድኖችላይ በተመሳሳይ የተጠናከረ እርምጃ መውሰድ ጀምራለች፡፡ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በቢላደን ላይ ያገኙትን ስኬት በሌሎች የአልቃይዳ አባላትም ላይ አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ የአሜሪካ ልዩ ኮማንዶ ኃይሎች ሚስጢራዊ በሆነ የተራቀቀ የኤሌክትሮኒክስ መረጃ ልውውጥ በመታገዝ፣ የአልቃይዳን አከርካሪ ለመስበር በኤደን ባህረ ሰላጤ ኮሽታው የማይሰማ ጦርነት እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡ “Obama’s New Secret War” በሚል ርዕስ The Middle East የተባለው መጽሔት ባቀረበው ዘገባ፣ በኦባማ የበላይነት የሚመራው ጦርነት፣ ምንም ዓይነት የጦርነት ነጋሪት ሳይመታ በልዩ ኮማንዶዎችና ሰው አልባ በሆኑ የጦር አውሮፕላኖች (unmanned ariel vehicle) የሚደረግ ሲሆን፣ ፍንጭ ሳይተው የሚፈልጉትን የአልቃይዳ አባል በማጥመድ ግድያ ይፈጽማሉ፡፡

የቻይና የባህል ሚኒስትር የባህል ደህንነትን አደጋ ላይ ይጥላሉ ያላቸውን ከ100 በላይ ዘፈኖች በአገሪቱ እንዳይሰራጩ እገዳ መጣሉን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡  
የቻይና መንግስት በሳንሱር ያልታዩና በይፋ ምዝገባ ያልተደረገላቸው ዘፈኖች በቀጥታ ከኢንተርኔት የሚገበዩበትን ሁኔታ በመቃወም እገዳውን የጣለ ሲሆን ማዕቀቡ ዘፈኖቹ ከያዙት ጭብጥ ጋር የተገናኘ አለመሆኑን ገልጿል፡፡ በቻይና የባህል ሚኒስትር ከታገዱ 100 ዘፈኖች መካከል ታይዋን፣ ሆንግ ኮንግና ጃፓን የተለቀቁት አብዛኛውን ድርሻ ቢወስዱም የቢዮንሴ፣ የካናዬ ዌስት፣ የሌዲ ጋጋ እና የኬቲ ፔሪ የሙዚቃ ሥራዎች በዝርዝሩ መካተታቸውን የሲኤንኤን ዘገባ አመልክቷል፡፡

ኢትዮጵያዊቷ የሶል እና ጃዝ ሙዚቀኛ መክሊት ሃደሮ፤ ሰሞኑን በጉግል የሳምንቱ ምርጥ አርቲስት የተባለች ሲሆን 3ኛውን አዲስ የሙዚቃ አልበሟን እየሰራች መሆኑን ሳንፍራንሲስኮ ክሮኒል ዘገበ፡፡
ከሳምንት በፊት በአሜሪካዋ የናቫዳ ግዛት በሚገኘው ሴንተር ፎር አርትስ፣ የሙዚቃ ሥራዎቿን ያቀረበችው መክሊት፤ በድምፃዊነትና በዘፈን ግጥም ደራሲነቷ በካሊፎርንያ እየተወደሰች መሆኗንም ለማወቅ ተችሏል፡፡