Saturday, 24 June 2023 20:49

በስዊዘርላንድ ዳይፐር የሚያደርጉ ተማሪዎች መምህራንን አማርረዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ከማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በጨረፍታ

 

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ የቻይና አቻቸውን፣ “አምባገነን” መሪ ናቸው ማለታቸው ውዝግብ ፈጠረ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው አንቶኒ ብሊንከን፣ በቤጂንግ ከፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ምክክር ባደረጉ ማግስት የተሰማው አስተያየት ከምን የመነጨ እንደሆነ ግልጽ አይደለም። ፕሬዚዳንት ሺ እና ብሊንከን የሀገራቱን የተካረረ ግንኙነት የሚያለዝቡ ውይይቶች እንዲደረጉ መስማማታቸውን ማሳወቃቸው ይታወሳል።
ራሳቸው ባይደንም ሰኞ እለት የአሜሪካና ቻይና ግንኙነት ወደ ትክክለኛው መስመር እየተመለሰ መሆኑን ተናግረው ነበር። ፕሬዚዳንቱ ማክሰኞ  ምሽት በካሊፎርኒያ በተደረገ የገቢ ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ግን ብሊንከን ሰኞ እለት “ቢዘጋ” ይሻላል ያሉትን አጀንዳ አንስተዋል።
“ፕሬዚዳንት ሺ የቻይና እንደሆኑ የተጠረጠሩት ተንሳፋፊ የስለላ ፊኛዎች፣ በአሜሪካ የአየር ክልል ተመተው በመውደቃቸው ሀፍረት ተሰምቶታል“  ነው ያሉት ባይደን።
 “ሺ ጂንፒንግ በወቅቱ የተረበሸው በስለላ ቁሳቁሶች የተሞላው ተንሳፋፊ ፊኛን መትቼ ስጥለው የት እንዳለ እንኳን ስለማያውቅ ነው” ሲሉም ተናግረዋል።
“ይህ ለአምባገነኖች እጅግ አሳፋሪ ነገር ነው፤ ምን እየተካሄደ እንደሆነ ሳያውቁ ሲቀሩና ባልጠበቁት መንገድ ስንመታው (ፊኛውን) ተበሳጭተዋል” በማለትም አክለዋል።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ ባለፈው ረቡዕ በሰጡት መግለጫ፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት አስተያየት ”በእጅጉ አሳዛኝና ሃላፊነት የጎደለው” ነው ብለውታል፡፡
 ከመሰረታዊ እውነታ የሚጻረርና የዲፕሎማሲ ፕሮቶኮል በእጅጉ የሚጥስ  ነው ያሉት ቃል አቀባይዋ፤ ”ግልጽ የፖለቲካ ትንኮሳ ነው” ሲሉም  ተችተዋል፡፡
ቃል አቀባይዋ አክለውም፤ ”ቻይና ከፍተኛ ቅሬታዋንና ተቃውሞዋን ትገልጻለች” ብለዋል፡፡ ከአምስት አመት በኋላ ሰሞኑን ከፍተኛ ባለሥልጣኗን ወደ ቻይና የላከችው አሜሪካ፥ ውጥረቱ ረገበ ሲባል ዳግም ቁርሾ የሚቀሰቅስ ንግግር በፕሬዚዳንቷ በኩል መሰማቱ ብዙዎችን ግራ አጋብቷል። ዋሽንግተንና ቤጂንግ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማደስ ከስምምነት ላይ ይድረሱ እንጂ፣ አሁንም የልዩነት ምንጭ የሆኑ በርካታ ጉዳዮች አሏቸው።  የንግድ፣ የሰብአዊ መብትና የታይዋን ጉዳይ ሃያላኑን ሀገራት እንዳፋጠጡ ቀጥለዋል፡፡(አል-ዐይን)


Read 1562 times