Wednesday, 29 November 2023 08:07

ኢትዮጵያ የሁለት ቅርሶችን ሕጋዊ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ከዩኔስኮ ተረከበች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮጵያ የሁለት ቅርሶችን ሕጋዊ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ከዩኔስኮ ተረከበች
ኢትዮጵያ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክና የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር ሕጋዊ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ተረክባለች፡፡
የቅርሶቹን የምዝገባ ምስክር ወረቀት ኢትዮጵያ ከዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ማዕከል የአፍሪካ ቢሮ ሃላፊ ሙሃመድ ጁማ (ዶ/ር) መረከቧን በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡
በሳዑዲ ዓረቢያ ሪያድ በተካሄደው 45ኛው የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ኢትዮጵያ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክና የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ-ምድርን በዓለም ቅርስነት ማስመዝገቧ ይታወሳል፡፡

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

Read 1903 times