Administrator
አየር መንገዱ ከትኬት ሽያጭ የተሠበሠበ ገንዘቡን ከሦስት አገራት ማውጣት አለመቻሉን አስታወቀ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከትኬት ሽያጭ የሰበሰበውን ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሬ ከኤርትራ፣ ሞዛምቢክ እና ሩሲያ ማውጣት አለመቻሉን ገለጸ። የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የተቋሙን የሥራ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ በተለይም ከኤርትራ ያገኘውን ገንዘብ ለማስወጣት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካ ተናግረዋል።
አየር መንገዱ የተያዘበትን ገንዘብ ለማስመለስ በኤርትራ ፍርድ ቤት ክስ መስርቶ የነበረ ቢሆንም፣ ጉዳዩ በፖለቲካዊ ሁኔታዎች ምክንያት ሊሳካ እንዳልቻለ አቶ መስፍን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በአገራቱ የተያዘው ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሬ በአየር መንገዱ የፋይናንስ እንቅስቃሴ ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል።
አሜሪካ በ24 የአፍሪካ ከተሞች የቪዛ አገልግሎት ልታቋርጥ ነው
ዩናይትድ ስቴትስ ከነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአስመራ፣ ጁባ፣ ሃራሬ፣ ባማኮ እና ደርባን ጨምሮ በ24 የአፍሪካ ከተሞች በሚገኙ ኤምባሲዎቿና ቆንስላዎቿ የምትሰጠውን መደበኛ የቪዛ አገልግሎት እንደምትገታ አስታወቀች።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እንዳስታወቀው፣ ይህ ውሳኔ የደህንነት ፍተሻዎችን ለማጠናከር፣ የመንግሥት ወጪን ለመቀነስ እና የቪዛ አሰጣጥ ሂደቱን ወጥ ለማድረግ ያለመ ነው። በዚህም ምክንያት በእነዚህ አገራት የሚገኙ አመልካቾች ለቱሪስት፣ ለንግድ፣ ለሥራ እና ለቋሚ ነዋሪነት ቪዛዎች በተመደቡ ቀጠናዊ ማዕከላት ለመጠቀም ይገደዳሉ።
ሆኖም ውሳኔው የኤምባሲዎቹን መዘጋት የሚያስከትል ባለመሆኑና ቀደም ሲል የተሰጡ ጸንተው የሚሠሩ ቪዛዎች ላይ ተጽዕኖ የማያደርግ መሆኑ ተገልጿል። መደበኛ የቪዛ አገልግሎቶች በአዲስ አበባ፣ ሌጎስ፣ ናይሮቢ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ጆሃንስበርግ እና ጂቡቲን ጨምሮ በዋና ዋና ቀጠናዊ ማዕከላት ባልተቋረጠ ሁኔታ የሚቀጥሉ ይሆናል። ለምሳሌ ያህል በናይጄሪያ አቡጃ ይሰጥ የነበረው አገልግሎት ቢቋረጥም በሌጎስ የሚቀጥል በመሆኑ አመልካቾች ወደዚያ መጓዝ ይኖርባቸዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
የኩሪፍቱ ባለቤት በምሥራቅ አፍሪካ ግዙፉን የውሃ ፓርክ በኬንያ ሊገነቡ ነው
"ደብረጽዮን ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር በሚስጢር ተገናኝተዋል!"
በደቡብ ወሎ ገዳም ላይ በተፈጸመ ጥቃት መነኮሳይያት በግፍ መገደላቸውን ፓትርያርኩ አወገዙ
የትራምፕ አዲስ ታሪፍ ሰባት የአፍሪካ ሀገራትን ኢላማ አደረገ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በንግድ ፖሊሲው ላይ ባደረገው አዲስ ክለሳ ከዋና ዋና የንግድ አጋሮቹ በሚገቡ ምርቶች ላይ አዲስ የገቢ ንግድ ታሪፍ መጣሉን ይፋ አድርጓል።
በዚህ አዲስ ውሳኔ መሠረት 12.5 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ የተካተቱ ሲሆን፣ እርምጃው አሜሪካ የዓለም አቀፍ ንግድ ማዕቀፏን ዳግም ለመቅረጽ የምታደርገው ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ አዲስ አሰራር በተለይም የነዳጅ፣ የጨርቃጨርቅ እና የምግብ ምርቶችን ወደ አሜሪካ በሚልኩት በእነዚህ የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። ውሳኔው የአሜሪካን የአገር ውስጥ አምራቾች ለመጠበቅ እና የንግድ ሚዛን እጥረትን ለመቀነስ ያለመ ነው ቢባልም፣ በዓለም አቀፍ የንግድ ትስስር እና ኤክስፖርት ላይ አዲስ ፈተና ደቅኗል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

